BEMALEDANEK Telegram 2340
   እነሆም ከክፉ ጠባያት ዝርዝር የሚመደበው ሌሎችን መወንጀል የክፉ መናፍስት ማንነትና ሥራ ነው፡፡ ደጉ ባሕሪይ ከራሱ ውጪ ማንንም አይከስም፡፡ ዓይኖቹ ወደ ውስጥ እንጂ ወደ ውጪ አያዩም፡፡ እጆቹ የሚለቅሙት የሕይወቱን እንጂ የወገኖችን አረም አይደለም፡፡ "ስሕተቱን" እንጂ "ስሕተታቸውን" አያፋጥጥም፡፡ እንደውም በዚህ ባሕሪይ የሚገለጥ ስብዕና ልዕልናው ሲጨምር፤ የሌሎችን መጥፋት እያሰበ የሚያዝንና ስለ ኃጢአት ሥራቸው ንስሐ የሚገባላቸው ታላቅ ምዕመን ይሆናል፡፡

   እኛና ዘመናችን ግን ከዚህ ባሕሪይ በእጅጉ የራቅን ነን፡፡ የግላችንን ገመና አለባብሰን የሰዎችን ማጀት አደባባይ ማውጣት ያስደስተናል፡፡ በኃጢአታችን ከመጸጸት ይልቅ ኃጢአታቸውን ማውራት ይቀለናል፡፡ የወደቅንበት ጉድጓድ የቱን ያህል እንደሚጠልቅ ሳናውቅ የሌሎችን ውድቀት መለካት ይዳዳናል፡፡ አያችሁ? .. ረቂቁ ክፉ ባሕሪይ ከሥጋችን ውስጥ ተሰውሮ ሥራውን በብቃት ይመራል፡፡

  በንስሐ መንገድ ላይ የሚያራምድ ጸጸት ከኛ ውስጥ ሊገኝ የሚችለው፥ ነግቶ በመሸ ቁጥር እኛን አትኩረን የምንከታተል የሆነ እንደሆነ ነው፡፡ እንደ ሥጋ ዓይኖቻችን ደረቅ ግንባር ላይ ተለጥፈን ወደ ዓለም (ሰዎች) ብቻ የምናይ ከሆነ፤ ለንስሐ የሚያበቃ የመንፈስ ስብራት ከቶውኑ አይኖረንም፡፡

   እግዚአብሔር የሚቀበለው የዘወትር መሥዋዕት የሆነው የመንፈስ መሰበር እንዳይኖር፤ አሳቹ ባሕሪይ ራሳችንን ሳይሆን ሌሎችን የምንሰብር ደንዳናዎች ያደርገናል፡፡ ሰዎችን የሚሰብር ሰው ደግሞ የተወደደውን ቅዱስ ኃይል የሚያስቀምጥበት የልብ ስንጥቃት አይኖረውም፡፡

   ዲያቢሎስ ሁልጊዜ ሽንፈትን በጣሙን እንደታገላት ይኖራል፡፡ መጸጸት፣ ራስን መውቀስ፣ ስሕተትን ማመን፣ ጥፋትን መቀበል የሚባሉ ጠባያትን ሳያቋርጥ ይዋጋቸዋል፡፡ ይህንን ግንዛቤ እናድርግና እስቲ ዝምብለን ራሳችንንና ዙሪያችንን እንቃኘው፡፡ ንስሐን የሚከለክሉ ባሕሪያትን ስንከባከባቸውና በአደገኛ ቅጥር (በቁጣ፣ በስድብ፣ በሽሙጥ፣ በትዕቢት) አጥረን ስንጠብቃቸው እንታያለን፡፡

   መንፈስ የጸጸትን ኃይል ከልቦና ውስጥ በማዳከም፤ በንስሐ ጌጥ አማኞች ኑሮአቸው እንዳያምር ሲታገል፤ ተስፋ የሚያደርገው መድረሻ ዓላማው እንዲህ የሚለው የሐኪሙ ወንጌላዊ ጽሕፈት ነው፦

"ንስሐ ባትገቡ ሁላችሁ እንደዚሁ ትጠፋላችሁ።" (የሉቃስ ወንጌል 13፥5)

   በአምላክ የምሕረት መዳፍ ያልተጎበኘው ትውልዳችን በእርግጥም እንዲሁ እንደ ዘበት መጥፋቱን እንኳ ሳያውቀው ከጠፋ ከ40 ዓመታት በላይ አለፉ፡፡ እንዲሁ ያልጠፋ ምን አለ እስኪ? እንዲሁ ፍቅር ጠፋ፣ እንዲሁ ሰላም ጠፋ፣ እንዲሁ ጤና ጠፋ፣ እንዲሁ አንድነት ጠፋ፣ እንዲሁ አገራዊ ክብር ጠፋ፣ እንዲሁ የታሪክ በረከት ጠፋ፣ እንዲሁ ሰብአዊ እሴት ጠፋ፣ .. እንዲሁ!

   ጠፍቶ የሚያጠፋው ክፉው ባሕሪይ፤ ባለመታየትና ባለመደመጥ መንፈሳዊነቱ ተጠቅሞ የሚታይና የሚደመጥ ጥፋትን ለማምጣት ከባሕሪያችን ጠጋ ብሎ ሲመሳሰል፤ እኛ ጀምረው በሰጡን አቅጣጫ ላይ በሰመመን እየተጓዝን ወደ ጥልቅ ጥፋት በየቀኑ እንሄዳለን፡፡ ባላጋራው ኃይልም ማንነታችንን ተዋሕዶ ማንነቱን ስላለማመደን፤ እርሱ ካከበበልን የሕይወት ልምድ ርቀን ለመሄድ እንዳንችል የገዛ አካላችን ጉልበት አውጥቶ እየተናነቀን፤ የብርሃን ጥሪዎችን በመሸሽና በግዴየለሽነት በማለፍ ሰውነታችንን ተጭኖ ያለውን ግርዛዜ "አትንኩብኝ!" እያልን ብዙ ዘመናትን አቆራርጠን መጣን፡፡ ኦ.. ! ቃሉ ተናግሮአል  .. "እንደዚሁ ትጠፋላችሁ!"

   ሰው "ሰው" ከሚያሰኙት በጎ ባሕሪያት ርቆ ከተገኘ በቁም ሳለም ጠፍቷል ማለት ነው፡፡ በንስሐ ሕይወት በኩል የሚመጡ የመንፈስ ቅዱስ ገጸ በረከቶችን የሚሸሽ ማንነት በዓለም ገደል ጠልቆ ጠፍቷል ቢባል ልክ ይሆናል፡፡ ከእውነት ጋር ለመታረቅ የዕድሜ ቀጠሮ የሚያራዝም አስተሳሰብ ከሐሰት ማሳ ገብቶ የጠፋ ነው፡፡ ይህንንም ጽሑፍ እየተመለከተ ወደ ኑሮው አጠንጥኖ "እንዴት ነው ነገሬ ግን?" ሲል የማያምሰለስል፤ ውስጡ በጥሞና እንዲያስብ የማይፈቅድ ሕልውና፤ መድኃኒቱ እንዳለው እንደዚሁ ጥፍት ብሎ ሌላ መጥፋትን ደሞ ይጠባበቃል፡፡ መንፈሳዊ ትምህርቶችን አልፎ አልፎ የምንከታተል ሰዎችም፥ ጊዜያዊ መጸጸት በተሰማን ቁጥር "ለንስሐ ሞት አብቃኝ" እያልን፤ ለንስሐ የማያበቃ ዓለማዊ መጋረጃን ሳንቀድድ ቀናቶች በላያችን ሲረማመዱ ዝምብለን እናያለን፡፡

ነብዩ ኢዮኤል፦

"አሁንስ፥ ይላል እግዚአብሔር፥ በፍጹም ልባችሁ፥ በጾምም፥ በልቅሶና በዋይታ ወደ እኔ ተመለሱ። ልባችሁን እንጂ ልብሳችሁን አትቅደዱ፤ አምላካችሁም እግዚአብሔር ቸርና መሐሪ፥ ቁጣው የዘገየ፥ ምሕረቱም የበዛ፥ ለክፋትም የተጸጸተ ነውና ወደ እርሱ ተመለሱ (ንስሐ ግቡ)።"

   ልባችሁን እንጂ ልብሳችሁን አትቅደዱ ተብለን ነበር፡፡ እኛ ጂንሳችንን ጉልበቱ ላይ እየቀደድን "ፋሽን ነው!" ነው ከማለት ውጪ የልብ ሸካራነትን የሚቀድድ የንስሐ ጸጸት እስከ አሁን አልተሰማንም፡፡ ቢሰማንም፥ የተቀደዱ ልብሶችን የሚለብሱ መዝናኛዎችን በተከታተልን ጊዜ፥ በኃጢአት የመቆጨቱ ዕድሜ ወዲያው ያጥርብናል፡፡

   የተሳካ ንስሐ እንገባ ዘንድ ልባችን (ለማንም የማንገልጠው አመለካከታችን) ግብዝነትን ለራሱ ታማኝ ሆኖ መፋለም አለበት፡፡ ማስመሰልን መናቅ አለብን፡፡ ፍቅርን ባከበረ መግፍኤ እየተመራን እውነትን መቀበል ይገባናል፡፡ ብዙዎች እንደሚሆኑት ላለመሆን መጀገን ይጠበቅብናል፡፡ የትክክልን መሥፈርት በመጠበቅ "አንበሳነት" ራስን ማክበር ይኖርብናል፡፡ ክርስትናን ከአሳብ፣ ከቃልና ከሕይወት በማዋሐድ፤ የንጉሥ ልጅነትን ከአንገት ክር በዘለለ በኑሮ ማዕረግ ማሳየት ያስፈልገናል፡፡ የነጠላ ያይደለ የልብ ንጽሕናን መጠበቅ ራሱን የቻለ ድንቅ ሰማእትነት ነው፡፡

   ተወዳጁ ቸርና መሐሪ፥ ከቁጣም የዘገየ ባሕሪይ ነው፡፡ የልብ እውነትን እጅ መንሻ አድርገን እስክናሳልፍ ድረስ ምሕረቱን እያበዛ ይጠብቀናል፡፡ በኃጢአት ጽሕፈት ያጠራቀምነውን የዓመፃ ወረቀት ከልባችን እንድንቀድድ በየአጋጣሚው ሳያርፍ "ተመለሱ" ይላል፡፡ እርሱ አብዝቶ የሚፈልገውና ሊቀበለው የሚወደው ከልብ ተነሥቶ የወጣውን ነው፡፡ ምክንያቱም የማንነት መዝገብ ተቀምጦ ያለው በልብ ውስጥ ነውና፡፡

   እግዚአብሔር ልባችንን አጥብቆ ፈለገው ማለት፤ እንደ እግዚአብሔር ለመሆን የሚደክመው መንፈስም ልባችንን ፍለጋ ይኳትናል ማለት ነው፡፡ በሌላ አገላለጽ "ዘንዶው ከሴቲቱ ፊት" ይቆማል፡፡ (የዮሐንስ ራእይ ምዕ. 12) ሐሰትን የሚኖረው ኃይል ከእውነት አንጻር ይታያል፡፡ ውድቀትን የሚከተለው ባሕሪይ ከምዕመናን ትይዩ ይገለጻል፡፡ ጥፋትን የሚመራው ዲያቢሎስ እግዚአብሔር ከሚሰጠን ማንኛውም ጎን መሽጎ አይጠፋም፡፡ ወዳጄ በደንብ አስብበት! ትኩረት የሰጠኸው፣ ዘወትር የምትገሰግሰው፣ ፈቅደህ የምትጋብዘው፣ ወደህ የምትመርጠው ሁሉ ሲጠቀለል የአንተነትህን መጽሐፍ ያትማልና፤ እንደገና መለስ በልና፥ የመጣህበትን፣ አካሄድህንና የምትሄድበትን ሰክነህ መርምር!


(በአብ ምሳሌ ተፈጥረናልና እናስባለን፥ ስለዚህ ስታነቡ በተለይ የተሰመሩባቸውን ለብቻቸው በሌላ ቦታ ላይ ጻፏቸውና፥ አንድ በአንድ አምሰልስሏቸው፡፡ ስለ እውነት በእውነት ስናስብ፥ እውነት ከልባችን ይነቃል፡፡ በሌላ አነጋገር እግዚአብሔር በነፍስ ደምፅ በኩል ያስተምረናል!)
ወደ ሥጋና ደሙ መጓዛችንን እንቀጥላለን. . .
#ጸባኦት_ይከተላችሁ
@bemaledanek



tgoop.com/bemaledanek/2340
Create:
Last Update:

   እነሆም ከክፉ ጠባያት ዝርዝር የሚመደበው ሌሎችን መወንጀል የክፉ መናፍስት ማንነትና ሥራ ነው፡፡ ደጉ ባሕሪይ ከራሱ ውጪ ማንንም አይከስም፡፡ ዓይኖቹ ወደ ውስጥ እንጂ ወደ ውጪ አያዩም፡፡ እጆቹ የሚለቅሙት የሕይወቱን እንጂ የወገኖችን አረም አይደለም፡፡ "ስሕተቱን" እንጂ "ስሕተታቸውን" አያፋጥጥም፡፡ እንደውም በዚህ ባሕሪይ የሚገለጥ ስብዕና ልዕልናው ሲጨምር፤ የሌሎችን መጥፋት እያሰበ የሚያዝንና ስለ ኃጢአት ሥራቸው ንስሐ የሚገባላቸው ታላቅ ምዕመን ይሆናል፡፡

   እኛና ዘመናችን ግን ከዚህ ባሕሪይ በእጅጉ የራቅን ነን፡፡ የግላችንን ገመና አለባብሰን የሰዎችን ማጀት አደባባይ ማውጣት ያስደስተናል፡፡ በኃጢአታችን ከመጸጸት ይልቅ ኃጢአታቸውን ማውራት ይቀለናል፡፡ የወደቅንበት ጉድጓድ የቱን ያህል እንደሚጠልቅ ሳናውቅ የሌሎችን ውድቀት መለካት ይዳዳናል፡፡ አያችሁ? .. ረቂቁ ክፉ ባሕሪይ ከሥጋችን ውስጥ ተሰውሮ ሥራውን በብቃት ይመራል፡፡

  በንስሐ መንገድ ላይ የሚያራምድ ጸጸት ከኛ ውስጥ ሊገኝ የሚችለው፥ ነግቶ በመሸ ቁጥር እኛን አትኩረን የምንከታተል የሆነ እንደሆነ ነው፡፡ እንደ ሥጋ ዓይኖቻችን ደረቅ ግንባር ላይ ተለጥፈን ወደ ዓለም (ሰዎች) ብቻ የምናይ ከሆነ፤ ለንስሐ የሚያበቃ የመንፈስ ስብራት ከቶውኑ አይኖረንም፡፡

   እግዚአብሔር የሚቀበለው የዘወትር መሥዋዕት የሆነው የመንፈስ መሰበር እንዳይኖር፤ አሳቹ ባሕሪይ ራሳችንን ሳይሆን ሌሎችን የምንሰብር ደንዳናዎች ያደርገናል፡፡ ሰዎችን የሚሰብር ሰው ደግሞ የተወደደውን ቅዱስ ኃይል የሚያስቀምጥበት የልብ ስንጥቃት አይኖረውም፡፡

   ዲያቢሎስ ሁልጊዜ ሽንፈትን በጣሙን እንደታገላት ይኖራል፡፡ መጸጸት፣ ራስን መውቀስ፣ ስሕተትን ማመን፣ ጥፋትን መቀበል የሚባሉ ጠባያትን ሳያቋርጥ ይዋጋቸዋል፡፡ ይህንን ግንዛቤ እናድርግና እስቲ ዝምብለን ራሳችንንና ዙሪያችንን እንቃኘው፡፡ ንስሐን የሚከለክሉ ባሕሪያትን ስንከባከባቸውና በአደገኛ ቅጥር (በቁጣ፣ በስድብ፣ በሽሙጥ፣ በትዕቢት) አጥረን ስንጠብቃቸው እንታያለን፡፡

   መንፈስ የጸጸትን ኃይል ከልቦና ውስጥ በማዳከም፤ በንስሐ ጌጥ አማኞች ኑሮአቸው እንዳያምር ሲታገል፤ ተስፋ የሚያደርገው መድረሻ ዓላማው እንዲህ የሚለው የሐኪሙ ወንጌላዊ ጽሕፈት ነው፦

"ንስሐ ባትገቡ ሁላችሁ እንደዚሁ ትጠፋላችሁ።" (የሉቃስ ወንጌል 13፥5)

   በአምላክ የምሕረት መዳፍ ያልተጎበኘው ትውልዳችን በእርግጥም እንዲሁ እንደ ዘበት መጥፋቱን እንኳ ሳያውቀው ከጠፋ ከ40 ዓመታት በላይ አለፉ፡፡ እንዲሁ ያልጠፋ ምን አለ እስኪ? እንዲሁ ፍቅር ጠፋ፣ እንዲሁ ሰላም ጠፋ፣ እንዲሁ ጤና ጠፋ፣ እንዲሁ አንድነት ጠፋ፣ እንዲሁ አገራዊ ክብር ጠፋ፣ እንዲሁ የታሪክ በረከት ጠፋ፣ እንዲሁ ሰብአዊ እሴት ጠፋ፣ .. እንዲሁ!

   ጠፍቶ የሚያጠፋው ክፉው ባሕሪይ፤ ባለመታየትና ባለመደመጥ መንፈሳዊነቱ ተጠቅሞ የሚታይና የሚደመጥ ጥፋትን ለማምጣት ከባሕሪያችን ጠጋ ብሎ ሲመሳሰል፤ እኛ ጀምረው በሰጡን አቅጣጫ ላይ በሰመመን እየተጓዝን ወደ ጥልቅ ጥፋት በየቀኑ እንሄዳለን፡፡ ባላጋራው ኃይልም ማንነታችንን ተዋሕዶ ማንነቱን ስላለማመደን፤ እርሱ ካከበበልን የሕይወት ልምድ ርቀን ለመሄድ እንዳንችል የገዛ አካላችን ጉልበት አውጥቶ እየተናነቀን፤ የብርሃን ጥሪዎችን በመሸሽና በግዴየለሽነት በማለፍ ሰውነታችንን ተጭኖ ያለውን ግርዛዜ "አትንኩብኝ!" እያልን ብዙ ዘመናትን አቆራርጠን መጣን፡፡ ኦ.. ! ቃሉ ተናግሮአል  .. "እንደዚሁ ትጠፋላችሁ!"

   ሰው "ሰው" ከሚያሰኙት በጎ ባሕሪያት ርቆ ከተገኘ በቁም ሳለም ጠፍቷል ማለት ነው፡፡ በንስሐ ሕይወት በኩል የሚመጡ የመንፈስ ቅዱስ ገጸ በረከቶችን የሚሸሽ ማንነት በዓለም ገደል ጠልቆ ጠፍቷል ቢባል ልክ ይሆናል፡፡ ከእውነት ጋር ለመታረቅ የዕድሜ ቀጠሮ የሚያራዝም አስተሳሰብ ከሐሰት ማሳ ገብቶ የጠፋ ነው፡፡ ይህንንም ጽሑፍ እየተመለከተ ወደ ኑሮው አጠንጥኖ "እንዴት ነው ነገሬ ግን?" ሲል የማያምሰለስል፤ ውስጡ በጥሞና እንዲያስብ የማይፈቅድ ሕልውና፤ መድኃኒቱ እንዳለው እንደዚሁ ጥፍት ብሎ ሌላ መጥፋትን ደሞ ይጠባበቃል፡፡ መንፈሳዊ ትምህርቶችን አልፎ አልፎ የምንከታተል ሰዎችም፥ ጊዜያዊ መጸጸት በተሰማን ቁጥር "ለንስሐ ሞት አብቃኝ" እያልን፤ ለንስሐ የማያበቃ ዓለማዊ መጋረጃን ሳንቀድድ ቀናቶች በላያችን ሲረማመዱ ዝምብለን እናያለን፡፡

ነብዩ ኢዮኤል፦

"አሁንስ፥ ይላል እግዚአብሔር፥ በፍጹም ልባችሁ፥ በጾምም፥ በልቅሶና በዋይታ ወደ እኔ ተመለሱ። ልባችሁን እንጂ ልብሳችሁን አትቅደዱ፤ አምላካችሁም እግዚአብሔር ቸርና መሐሪ፥ ቁጣው የዘገየ፥ ምሕረቱም የበዛ፥ ለክፋትም የተጸጸተ ነውና ወደ እርሱ ተመለሱ (ንስሐ ግቡ)።"

   ልባችሁን እንጂ ልብሳችሁን አትቅደዱ ተብለን ነበር፡፡ እኛ ጂንሳችንን ጉልበቱ ላይ እየቀደድን "ፋሽን ነው!" ነው ከማለት ውጪ የልብ ሸካራነትን የሚቀድድ የንስሐ ጸጸት እስከ አሁን አልተሰማንም፡፡ ቢሰማንም፥ የተቀደዱ ልብሶችን የሚለብሱ መዝናኛዎችን በተከታተልን ጊዜ፥ በኃጢአት የመቆጨቱ ዕድሜ ወዲያው ያጥርብናል፡፡

   የተሳካ ንስሐ እንገባ ዘንድ ልባችን (ለማንም የማንገልጠው አመለካከታችን) ግብዝነትን ለራሱ ታማኝ ሆኖ መፋለም አለበት፡፡ ማስመሰልን መናቅ አለብን፡፡ ፍቅርን ባከበረ መግፍኤ እየተመራን እውነትን መቀበል ይገባናል፡፡ ብዙዎች እንደሚሆኑት ላለመሆን መጀገን ይጠበቅብናል፡፡ የትክክልን መሥፈርት በመጠበቅ "አንበሳነት" ራስን ማክበር ይኖርብናል፡፡ ክርስትናን ከአሳብ፣ ከቃልና ከሕይወት በማዋሐድ፤ የንጉሥ ልጅነትን ከአንገት ክር በዘለለ በኑሮ ማዕረግ ማሳየት ያስፈልገናል፡፡ የነጠላ ያይደለ የልብ ንጽሕናን መጠበቅ ራሱን የቻለ ድንቅ ሰማእትነት ነው፡፡

   ተወዳጁ ቸርና መሐሪ፥ ከቁጣም የዘገየ ባሕሪይ ነው፡፡ የልብ እውነትን እጅ መንሻ አድርገን እስክናሳልፍ ድረስ ምሕረቱን እያበዛ ይጠብቀናል፡፡ በኃጢአት ጽሕፈት ያጠራቀምነውን የዓመፃ ወረቀት ከልባችን እንድንቀድድ በየአጋጣሚው ሳያርፍ "ተመለሱ" ይላል፡፡ እርሱ አብዝቶ የሚፈልገውና ሊቀበለው የሚወደው ከልብ ተነሥቶ የወጣውን ነው፡፡ ምክንያቱም የማንነት መዝገብ ተቀምጦ ያለው በልብ ውስጥ ነውና፡፡

   እግዚአብሔር ልባችንን አጥብቆ ፈለገው ማለት፤ እንደ እግዚአብሔር ለመሆን የሚደክመው መንፈስም ልባችንን ፍለጋ ይኳትናል ማለት ነው፡፡ በሌላ አገላለጽ "ዘንዶው ከሴቲቱ ፊት" ይቆማል፡፡ (የዮሐንስ ራእይ ምዕ. 12) ሐሰትን የሚኖረው ኃይል ከእውነት አንጻር ይታያል፡፡ ውድቀትን የሚከተለው ባሕሪይ ከምዕመናን ትይዩ ይገለጻል፡፡ ጥፋትን የሚመራው ዲያቢሎስ እግዚአብሔር ከሚሰጠን ማንኛውም ጎን መሽጎ አይጠፋም፡፡ ወዳጄ በደንብ አስብበት! ትኩረት የሰጠኸው፣ ዘወትር የምትገሰግሰው፣ ፈቅደህ የምትጋብዘው፣ ወደህ የምትመርጠው ሁሉ ሲጠቀለል የአንተነትህን መጽሐፍ ያትማልና፤ እንደገና መለስ በልና፥ የመጣህበትን፣ አካሄድህንና የምትሄድበትን ሰክነህ መርምር!


(በአብ ምሳሌ ተፈጥረናልና እናስባለን፥ ስለዚህ ስታነቡ በተለይ የተሰመሩባቸውን ለብቻቸው በሌላ ቦታ ላይ ጻፏቸውና፥ አንድ በአንድ አምሰልስሏቸው፡፡ ስለ እውነት በእውነት ስናስብ፥ እውነት ከልባችን ይነቃል፡፡ በሌላ አነጋገር እግዚአብሔር በነፍስ ደምፅ በኩል ያስተምረናል!)
ወደ ሥጋና ደሙ መጓዛችንን እንቀጥላለን. . .
#ጸባኦት_ይከተላችሁ
@bemaledanek

BY በማለዳ ንቁ ቁጥር ! ፪


Share with your friend now:
tgoop.com/bemaledanek/2340

View MORE
Open in Telegram


Telegram News

Date: |

Clear Members can post their voice notes of themselves screaming. Interestingly, the group doesn’t allow to post anything else which might lead to an instant ban. As of now, there are more than 330 members in the group. Select: Settings – Manage Channel – Administrators – Add administrator. From your list of subscribers, select the correct user. A new window will appear on the screen. Check the rights you’re willing to give to your administrator. Each account can create up to 10 public channels Joined by Telegram's representative in Brazil, Alan Campos, Perekopsky noted the platform was unable to cater to some of the TSE requests due to the company's operational setup. But Perekopsky added that these requests could be studied for future implementation.
from us


Telegram በማለዳ ንቁ ቁጥር ! ፪
FROM American