BEMALEDANEK Telegram 2359
 በተጨማሪ ለራስ በመናዘዝ ውስጥ ምን ምን ክህሎቶችን ልናገኝ እንችላለን?

ሀ)  ራስን የመመርመር ክህሎት
ለ)  ስሕተትን የመቀበል ክህሎት (ቅን ስነ ልቦና)
ሐ)  ለራስ ፈቃድና ውሳኔ ኃላፊነት የመውሰድ ክህሎት
መ)  ኃጢአት ሰክኖ እንዳይቀመጥ የመከላከል ክህሎት
ሠ)  ትሕትናን የመላበስ ክህሎት
ረ)  ግድየለሽነትን የመዋጊያ ክህሎት
ሰ)  ጥፋቶችን የማረም ፍላጎትና ክህሎት
ሸ)  ታማኝነትን ለራስ የማረጋገጥ ከህሎት
ቀ)  በሰው ሕይወት ላይ ያለመፍረድን ክህሎት

                       ✞  በርዕስ መጸለይ ✞

   ኃጢአቶቻችን ሁሉ አውጥተን በመዘርዘር ለራሳችን ከተናዘዝን በኋላ ቀጣዩ ሂደታችን መጓዝ ያለበት ወደ ርዕስ ጸሎት ነው፡፡ አስቀድሞ እንደጠቅሰነው (ምዕራፍ 1፤ ክፍል 7) የርዕስ ጸሎት ማለት አንድ ጉዳይን ለብቻ በመለየት፤ ስለጉዳዩ የሚመጥን ልዩ ትኩረትና ጊዜ ሰጥቶ መጸለይ ማለት ነው፡፡ ስለዚህ ንስሐ ከመግባታችን አስቀድሞ ስለሚከተሉት መሠረታዊ ምክንያቶች "ንስሐ ስለመግባት" በሚል ርዕስ መጸለይ ይገባናል፡፡

1)  የእግዚአብሔርን ፈቃድ ለማስቀደም

   "ነገርን ሁሉ ውብ አድርጎ ሠራው" እንዲል መጽሐፍ፤ ንስሐ የምንገባበት ጊዜ በእግዚአብሔር ፈቃድ ተመርቶ ውብ ፍሬን እንዲያፈራ ስለ ንስሐ መግባት አስቀድመን መጸለይ አለብን፡፡ በተለይ "አምላክ ሰው ሆነ፥ ሰው አምላክ ሆነ" በሚል የተዋሕዶ ዶግማ የሚያምን ምዕመን፤ እግዚአብሔር ሰው ሆኖ ወገናችን ከሆነ ዘንዳ፥ እኛ ደግሞ የእርሱ ወገን ልንሆን ይገባናል በሚል መርህ ላይ ኑሮውን ይመሠርታል፡፡ በሌላ አባባል በሁለንተናው ላይ የእግዚአብሔር ፈቃድና ኃይል እንዲቀድም የራሱ የሆነውን ፈቃድና ውሳኔ አሳልፎ ይሰጣል፡፡ ሰው ንስሐ ልግባ ብሎ ሲወስን፤ ውሳኔው በራሱ የእግዚአብሔር መልካም ፈቃድ ሆኖ ሳለ፤ ይሄ ፈቃድ በምሪቱ ኃይል ታግዞ ወደ ተሳካ ፍጻሜ እንዲደርስ "አቤቱ አባት ሆይ፥ እኔ ስለንስሐ እንዲህ ወሰንኩ፤ አንተ ደግሞ ይህን እንዴት ታየዋለህ?" ብሎ መጠየቅ ያስፈልጋል፡፡ የእግዚአብሔርን ምሪት በነገር ሁሉ ማስቀደም፤ በውስጡ ራሱን የቻለ መለኮታዊ ክብር ይገለጥበታል፡፡ አምላክን እንደ አባት የማቅረብ የሐዲስ ኪዳን ተስፋ ይረጋገጥበታል፡፡ ፈጣሪ የሚገዛን ንጉሥ ብቻ ሳይሆን የሚያግዘን ወዳጅ ስለመሆኑ ይመሰከርበታል፡፡

2)  የመናፍስትን ቅደመ ዝግጅት ለማፍረስ

    በአካላዊ ገጽታ የማይዳሰሱት መናፍስት በሥጋ ስለማይጨበጡልን፤ በየዕለት የሕይወታችን ደቂቃ ውስጥ ጣልቃ ሊገቡ እንደሚችሉ ብዙዎቻችን እንዘነጋለን፡፡ በተለይ ደግሞ ምሽጋቸውን አፍርሶ ለሚጥለው እንደ ንስሐ ላለው መንፈሳዊ ሕይወት በቀላሉ እንደማይተኙልን አናስተውልም፡፡ ስለዚህ ንስሐ ለመግባት በወሰንን ጊዜ፤ ውሳኔያችን ወደ መሬት እንዳይወርድ በተለያየ ስልት (እንደ ጠባያችንና ኑሮአችን ሁኔታ) እንደሚዋጉ ስለማይገባን፤ እቅዳችንን ከዳር አድርሰን የኃጢአት ሥርየትን ማግኘት አልሆነልንም፡፡

   እንደ ዓይነጥላ ያሉ ከሩቅ የመመልከት ችሎታ ያላቸው መናፍስት በንስሐ መንገዳችን ላይ ከፊት ቀድመው ዕንቅፋት ያስቀምጣሉ፡፡ በኑሮ ምሳሌ ስናመጣው፤ ንስሐ ስለመግባት መወሰናችንን የሰሙ በዙሪያችን ያሉ ሰዎች ላይ በመሆን (ሠራዊት በመሳሳብ፣ ከውስጥ ወደ ውጪ በመናበብ)፤ ተቃራኒ ግፊት የሚያሳድር ተጽዕኖን ይፈጥራል፡፡ "ምንድነው በዚህ ዕድሜ ንስሐ የምትለው? መነኩሴ መሆን አማረሽ ወይ? ትንሽ ያካበድከው አልመሰለህም?" የሚሉ ይዘቶች ያሏቸውን አሳቦች ንግግር እያደረገ፤ በሰው እውቀትና ጠባይ ልክ እንደግለሰቡ ሆኖ ይዋጋል፡፡ ውሳኔን የሚሸረሽሩ፣ ሞራልን የሚያደቅቁ፣ የእምነትን ኃይል የሚያቃልሉ፣ መንፈሳዊነትን የሚያጣጥሉ፣ ሥጋዊ ብልጽግናን መለኪያ የሚያደርጉ፣ ነባራዊ ድርጊቶችን እንደ ምስክር የሚያቀርቡ ፈተናዎችን ያመጣል፡፡ አጠቃላይ የዚህ አይነት መልክ ያላቸው መሰናክሎች ሊታለፉ የሚችሉት በርዕስ ጸሎት ነው፡፡

    "ሊቀ ካህን ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ፥ ንሰሐዬን ጠብቅ፤ እኔ ያንተ እርሻ ነኝና ጠላት በእኔ እንርክርዳድ እንዳይዘራ ዙሪያዬን እጠረው፤ በምክንያትና በሰዎች ጀርባ እየተከለለ ክፉው እንዳያስታጉለኝ መንገዴን ምራኝ፤ ነፍሳት ሁሉ ይድኑና እውነቱን ወደማወቅ ጥግ ይደርሱ ዘንድ ሕያው ፈቃድ አለህና የመዳኔን ጉዞ አንተ ተረከብ፡፡ እውነትን ለማወቅ ስነሣ እውነት የመሰለ ሐሰት እንዳያታልለኝ በረድኤትህ ጋርደኝ፡፡ ሰማያዊ ባሕሪያትህን እውቀት አድርገህ አስተምረኝ፡፡ ወዳንተ የምመለስበትን ጎዳና ጠላት እንዳያጠፋብኝ፤ ከነፍስም ከሥጋዬም በኩል አብራልኝ" እያልን ስለ ንስሐ የተመለከተ አደራ ወደ አርያም መቅደስ ብንልክ፤ የውሳኔያችን ማሳ በዝንጀሮዎች እንዳይበዘበዝ "መልካሙ እረኛ" ኃላፊነቱን ይወስዳል (በነገራችን ክፉ መናፍስት በሕልም እይታ ዝንጀሮ ሆነው ብዙ ጊዜ ይገለጣሉ)፡፡

3)  ለንስሐ የምንሰጠውን ትኩረትና መሥዋዕት ይጨምራል

   የሰው ልጅ "ጉዳዬ" ብሎ ለይቶ የሚይዘው አጀንዳ ላይ ከፍተኛ ፍላጎትን፣ አስፈላጊ ጥረትን፣ የማይነዋወጥ ጽናትንና ተስፋ የማይቆርጥ ተጋድሎን ከባሕሪይው ውስጥ ለማንቃት አይቸገርም፡፡ ንስሐን እንደ ልዩ ጉዳይ በርዕስ ማክበር ያስፈለገው እንግዲህ ለዚህ ነው፡፡

   የንስሐችን ጊዜ ሥጋ ለብሶ በተጨባጭ እስኪሳካ ድረስ፤ በዕለት የግል ጸሎታችን ውስጥ ስለ ንስሐ እያነሱ በልዩ ትኩረት መጸለይ፤ ንስሐን አክብረን እንድንጠብቅ የሚያደርግ ስሜትን ይፈጥራል፡፡ መድኃኒቱ ባስተማረን ታላቁ ጸሎት ውስጥ "እኛ የሌሎችን በደል ይቅር እንደምንል፥ አቤቱ ኃጢአታችንን ይቅር በለን" በሉ ሲል ያሳሰበን አንድም ይሄንን ነው፡፡ በደልን የመሰረዝ፣ ኃጢአትን የመቃወም፣ ይቅርታን የመውደድ፣ ንስሐን የማክበር መንፈሳዊ አቋም እንዲኖረን ዘወትር እንዲህ ጸልዩ አለን፡፡

   ርዕስ አድርገን በተደጋጋሚ የምናነሳው የጸሎት ጉዳይ ሕልውናችን ውስጥ ዘልቆ የመዋሐድ ዕድሉ ሰፊ ነው፡፡ ወይንም በምናባችን ላይ እየተመላለሰ ከልቦናችን ርቆ የማይሄድ የአሳባችን አንድ ክፍል ይሆናል፡፡ እንዲህ ሲሆን ደግሞ፤ የንስሐን ዳገት (መቼም ኃጢአት ቀልቁለት ነው፤ አንዴ ከወረዱበት ቀሪውን እርምጃ ራሱ ይገፋፋል) ለመውጣት ጉልበት ማውጣት ስንጀምር ኃይል እየሆነ የሚያስቀጥለን ተስፋ ይሄ በልቦናችን የሚዋሐድ የንስሐ ርዕስ ነው፡፡ በሌላ አነጋገር ንስሐ የምንገባበትን በሮች ሁሉ ዲያቢሎስ ጠርቅሞ ቢዘጋም፤ በተለሰነ ግድግዳ እንደማለፍ የሚተረጎም፥ በቀጭን መስመር ላይ ሳይንገዳገዱ የመራመድን ወኔ የምናገኘው ውስጣችን በሚመላለስ ብርቱ አሳብ ነው፡፡ ይህን አሳብ ለማስገኘት፣ ለማጠንከርና በእምነት ማኅተም ለማጽናት እንዲቻለን ነው የርዕስ ጸሎት ያስፈልጋል የተባለው፡፡


[በመጨረሻዎቹ ክፍሎች ንስሐን ለካህናት በመናዘዝ ጊዜና ከመናዘዝ በኋላ ምን እናድርግ፤ መቼ መቼስ እንናዘዝ የሚለውን ተመልከተን ምዕራፋችንን እንጠቀልላለን]

ወደ ሥጋና ደሙ መጓዛችንን እንቀጥላለን. . .
#ጸባኦት_ይከተላችሁ
@bemaledanek



tgoop.com/bemaledanek/2359
Create:
Last Update:

 በተጨማሪ ለራስ በመናዘዝ ውስጥ ምን ምን ክህሎቶችን ልናገኝ እንችላለን?

ሀ)  ራስን የመመርመር ክህሎት
ለ)  ስሕተትን የመቀበል ክህሎት (ቅን ስነ ልቦና)
ሐ)  ለራስ ፈቃድና ውሳኔ ኃላፊነት የመውሰድ ክህሎት
መ)  ኃጢአት ሰክኖ እንዳይቀመጥ የመከላከል ክህሎት
ሠ)  ትሕትናን የመላበስ ክህሎት
ረ)  ግድየለሽነትን የመዋጊያ ክህሎት
ሰ)  ጥፋቶችን የማረም ፍላጎትና ክህሎት
ሸ)  ታማኝነትን ለራስ የማረጋገጥ ከህሎት
ቀ)  በሰው ሕይወት ላይ ያለመፍረድን ክህሎት

                       ✞  በርዕስ መጸለይ ✞

   ኃጢአቶቻችን ሁሉ አውጥተን በመዘርዘር ለራሳችን ከተናዘዝን በኋላ ቀጣዩ ሂደታችን መጓዝ ያለበት ወደ ርዕስ ጸሎት ነው፡፡ አስቀድሞ እንደጠቅሰነው (ምዕራፍ 1፤ ክፍል 7) የርዕስ ጸሎት ማለት አንድ ጉዳይን ለብቻ በመለየት፤ ስለጉዳዩ የሚመጥን ልዩ ትኩረትና ጊዜ ሰጥቶ መጸለይ ማለት ነው፡፡ ስለዚህ ንስሐ ከመግባታችን አስቀድሞ ስለሚከተሉት መሠረታዊ ምክንያቶች "ንስሐ ስለመግባት" በሚል ርዕስ መጸለይ ይገባናል፡፡

1)  የእግዚአብሔርን ፈቃድ ለማስቀደም

   "ነገርን ሁሉ ውብ አድርጎ ሠራው" እንዲል መጽሐፍ፤ ንስሐ የምንገባበት ጊዜ በእግዚአብሔር ፈቃድ ተመርቶ ውብ ፍሬን እንዲያፈራ ስለ ንስሐ መግባት አስቀድመን መጸለይ አለብን፡፡ በተለይ "አምላክ ሰው ሆነ፥ ሰው አምላክ ሆነ" በሚል የተዋሕዶ ዶግማ የሚያምን ምዕመን፤ እግዚአብሔር ሰው ሆኖ ወገናችን ከሆነ ዘንዳ፥ እኛ ደግሞ የእርሱ ወገን ልንሆን ይገባናል በሚል መርህ ላይ ኑሮውን ይመሠርታል፡፡ በሌላ አባባል በሁለንተናው ላይ የእግዚአብሔር ፈቃድና ኃይል እንዲቀድም የራሱ የሆነውን ፈቃድና ውሳኔ አሳልፎ ይሰጣል፡፡ ሰው ንስሐ ልግባ ብሎ ሲወስን፤ ውሳኔው በራሱ የእግዚአብሔር መልካም ፈቃድ ሆኖ ሳለ፤ ይሄ ፈቃድ በምሪቱ ኃይል ታግዞ ወደ ተሳካ ፍጻሜ እንዲደርስ "አቤቱ አባት ሆይ፥ እኔ ስለንስሐ እንዲህ ወሰንኩ፤ አንተ ደግሞ ይህን እንዴት ታየዋለህ?" ብሎ መጠየቅ ያስፈልጋል፡፡ የእግዚአብሔርን ምሪት በነገር ሁሉ ማስቀደም፤ በውስጡ ራሱን የቻለ መለኮታዊ ክብር ይገለጥበታል፡፡ አምላክን እንደ አባት የማቅረብ የሐዲስ ኪዳን ተስፋ ይረጋገጥበታል፡፡ ፈጣሪ የሚገዛን ንጉሥ ብቻ ሳይሆን የሚያግዘን ወዳጅ ስለመሆኑ ይመሰከርበታል፡፡

2)  የመናፍስትን ቅደመ ዝግጅት ለማፍረስ

    በአካላዊ ገጽታ የማይዳሰሱት መናፍስት በሥጋ ስለማይጨበጡልን፤ በየዕለት የሕይወታችን ደቂቃ ውስጥ ጣልቃ ሊገቡ እንደሚችሉ ብዙዎቻችን እንዘነጋለን፡፡ በተለይ ደግሞ ምሽጋቸውን አፍርሶ ለሚጥለው እንደ ንስሐ ላለው መንፈሳዊ ሕይወት በቀላሉ እንደማይተኙልን አናስተውልም፡፡ ስለዚህ ንስሐ ለመግባት በወሰንን ጊዜ፤ ውሳኔያችን ወደ መሬት እንዳይወርድ በተለያየ ስልት (እንደ ጠባያችንና ኑሮአችን ሁኔታ) እንደሚዋጉ ስለማይገባን፤ እቅዳችንን ከዳር አድርሰን የኃጢአት ሥርየትን ማግኘት አልሆነልንም፡፡

   እንደ ዓይነጥላ ያሉ ከሩቅ የመመልከት ችሎታ ያላቸው መናፍስት በንስሐ መንገዳችን ላይ ከፊት ቀድመው ዕንቅፋት ያስቀምጣሉ፡፡ በኑሮ ምሳሌ ስናመጣው፤ ንስሐ ስለመግባት መወሰናችንን የሰሙ በዙሪያችን ያሉ ሰዎች ላይ በመሆን (ሠራዊት በመሳሳብ፣ ከውስጥ ወደ ውጪ በመናበብ)፤ ተቃራኒ ግፊት የሚያሳድር ተጽዕኖን ይፈጥራል፡፡ "ምንድነው በዚህ ዕድሜ ንስሐ የምትለው? መነኩሴ መሆን አማረሽ ወይ? ትንሽ ያካበድከው አልመሰለህም?" የሚሉ ይዘቶች ያሏቸውን አሳቦች ንግግር እያደረገ፤ በሰው እውቀትና ጠባይ ልክ እንደግለሰቡ ሆኖ ይዋጋል፡፡ ውሳኔን የሚሸረሽሩ፣ ሞራልን የሚያደቅቁ፣ የእምነትን ኃይል የሚያቃልሉ፣ መንፈሳዊነትን የሚያጣጥሉ፣ ሥጋዊ ብልጽግናን መለኪያ የሚያደርጉ፣ ነባራዊ ድርጊቶችን እንደ ምስክር የሚያቀርቡ ፈተናዎችን ያመጣል፡፡ አጠቃላይ የዚህ አይነት መልክ ያላቸው መሰናክሎች ሊታለፉ የሚችሉት በርዕስ ጸሎት ነው፡፡

    "ሊቀ ካህን ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ፥ ንሰሐዬን ጠብቅ፤ እኔ ያንተ እርሻ ነኝና ጠላት በእኔ እንርክርዳድ እንዳይዘራ ዙሪያዬን እጠረው፤ በምክንያትና በሰዎች ጀርባ እየተከለለ ክፉው እንዳያስታጉለኝ መንገዴን ምራኝ፤ ነፍሳት ሁሉ ይድኑና እውነቱን ወደማወቅ ጥግ ይደርሱ ዘንድ ሕያው ፈቃድ አለህና የመዳኔን ጉዞ አንተ ተረከብ፡፡ እውነትን ለማወቅ ስነሣ እውነት የመሰለ ሐሰት እንዳያታልለኝ በረድኤትህ ጋርደኝ፡፡ ሰማያዊ ባሕሪያትህን እውቀት አድርገህ አስተምረኝ፡፡ ወዳንተ የምመለስበትን ጎዳና ጠላት እንዳያጠፋብኝ፤ ከነፍስም ከሥጋዬም በኩል አብራልኝ" እያልን ስለ ንስሐ የተመለከተ አደራ ወደ አርያም መቅደስ ብንልክ፤ የውሳኔያችን ማሳ በዝንጀሮዎች እንዳይበዘበዝ "መልካሙ እረኛ" ኃላፊነቱን ይወስዳል (በነገራችን ክፉ መናፍስት በሕልም እይታ ዝንጀሮ ሆነው ብዙ ጊዜ ይገለጣሉ)፡፡

3)  ለንስሐ የምንሰጠውን ትኩረትና መሥዋዕት ይጨምራል

   የሰው ልጅ "ጉዳዬ" ብሎ ለይቶ የሚይዘው አጀንዳ ላይ ከፍተኛ ፍላጎትን፣ አስፈላጊ ጥረትን፣ የማይነዋወጥ ጽናትንና ተስፋ የማይቆርጥ ተጋድሎን ከባሕሪይው ውስጥ ለማንቃት አይቸገርም፡፡ ንስሐን እንደ ልዩ ጉዳይ በርዕስ ማክበር ያስፈለገው እንግዲህ ለዚህ ነው፡፡

   የንስሐችን ጊዜ ሥጋ ለብሶ በተጨባጭ እስኪሳካ ድረስ፤ በዕለት የግል ጸሎታችን ውስጥ ስለ ንስሐ እያነሱ በልዩ ትኩረት መጸለይ፤ ንስሐን አክብረን እንድንጠብቅ የሚያደርግ ስሜትን ይፈጥራል፡፡ መድኃኒቱ ባስተማረን ታላቁ ጸሎት ውስጥ "እኛ የሌሎችን በደል ይቅር እንደምንል፥ አቤቱ ኃጢአታችንን ይቅር በለን" በሉ ሲል ያሳሰበን አንድም ይሄንን ነው፡፡ በደልን የመሰረዝ፣ ኃጢአትን የመቃወም፣ ይቅርታን የመውደድ፣ ንስሐን የማክበር መንፈሳዊ አቋም እንዲኖረን ዘወትር እንዲህ ጸልዩ አለን፡፡

   ርዕስ አድርገን በተደጋጋሚ የምናነሳው የጸሎት ጉዳይ ሕልውናችን ውስጥ ዘልቆ የመዋሐድ ዕድሉ ሰፊ ነው፡፡ ወይንም በምናባችን ላይ እየተመላለሰ ከልቦናችን ርቆ የማይሄድ የአሳባችን አንድ ክፍል ይሆናል፡፡ እንዲህ ሲሆን ደግሞ፤ የንስሐን ዳገት (መቼም ኃጢአት ቀልቁለት ነው፤ አንዴ ከወረዱበት ቀሪውን እርምጃ ራሱ ይገፋፋል) ለመውጣት ጉልበት ማውጣት ስንጀምር ኃይል እየሆነ የሚያስቀጥለን ተስፋ ይሄ በልቦናችን የሚዋሐድ የንስሐ ርዕስ ነው፡፡ በሌላ አነጋገር ንስሐ የምንገባበትን በሮች ሁሉ ዲያቢሎስ ጠርቅሞ ቢዘጋም፤ በተለሰነ ግድግዳ እንደማለፍ የሚተረጎም፥ በቀጭን መስመር ላይ ሳይንገዳገዱ የመራመድን ወኔ የምናገኘው ውስጣችን በሚመላለስ ብርቱ አሳብ ነው፡፡ ይህን አሳብ ለማስገኘት፣ ለማጠንከርና በእምነት ማኅተም ለማጽናት እንዲቻለን ነው የርዕስ ጸሎት ያስፈልጋል የተባለው፡፡


[በመጨረሻዎቹ ክፍሎች ንስሐን ለካህናት በመናዘዝ ጊዜና ከመናዘዝ በኋላ ምን እናድርግ፤ መቼ መቼስ እንናዘዝ የሚለውን ተመልከተን ምዕራፋችንን እንጠቀልላለን]

ወደ ሥጋና ደሙ መጓዛችንን እንቀጥላለን. . .
#ጸባኦት_ይከተላችሁ
@bemaledanek

BY በማለዳ ንቁ ቁጥር ! ፪


Share with your friend now:
tgoop.com/bemaledanek/2359

View MORE
Open in Telegram


Telegram News

Date: |

A new window will come up. Enter your channel name and bio. (See the character limits above.) Click “Create.” The main design elements of your Telegram channel include a name, bio (brief description), and avatar. Your bio should be: Select “New Channel” The initiatives announced by Perekopsky include monitoring the content in groups. According to the executive, posts identified as lacking context or as containing false information will be flagged as a potential source of disinformation. The content is then forwarded to Telegram's fact-checking channels for analysis and subsequent publication of verified information. A vandalised bank during the 2019 protest. File photo: May James/HKFP.
from us


Telegram በማለዳ ንቁ ቁጥር ! ፪
FROM American