BEMALEDANEK Telegram 2364
በማለዳ ንቁ ቁጥር ! ፪
2•  ንስሐ    2.4•  ለንስሐ እንዴት እንዘጋጅ? ክፍል - ፯    የንስሐ መንገዳችን እነሆ ወደ መገባደዱ ደርሷል፡፡ ከ"ፍቅር" ተቀብሎ፤ ፍቅርንም በውስጡ ይዞ በራሱ ጎዳና ያንሸራሸረን "ንስሐ" እዚህ ድረስ ካመጣኋችሁ ለአሁኑ ይበቃል ብሎናል፡፡ ያላስጎበኘን ቦታዎች ስለሚኖሩ፤ ሌላም ጊዜ ወደርሱ መለስ እያልን እንድንጠይቀው የአደራ መልእክት አስቀምጦአል፡፡ የመጨረሻውን የጉዞአችንን ክፍሎች ያሳየንና፤…
2•  ንስሐ

   2.4•  ለንስሐ እንዴት እንዘጋጅ?

ክፍል - ፰

                 ✞ ለማንና እንዴት እንናዘዝ

   ከንስሐ ሂደት ውስጥ ወደ መጨረሻው አከባቢ የምናገኘው ክፍል "ኃጢአትን የመናዘዝ" ክፍል ነው፡፡ መናዘዝ በጥሬ ቃሉ አደራን መናገር፣ ሚስጢርን ማውጣት፣ ጥፋትን ማስረዳት፣ ስሕተትን መግለጥ ከሚሉ ግሶች ጋር አቻ ይገጥማል፡፡

   መናዘዝ የንስሐ መሠረታዊ አምድ ተደርጎ ቢወሰድ ትክክል ነው፡፡ ምክንያቱም ንስሐ ማለት የኃጢአት ሥርየት የሚገኝበት መንፈሳዊ ሕይወት በመሆኑ፤ በእግዚአብሔር ላይ ዓምፀን ያሳለፍናቸው ጊዜያት ሳይደበቁ ጥፋትነታቸውን መግለጥ ስንችል ነው ምሕረት የሚሰኘው ቀጣዩ የአምላክ ፍቅር የሚተረጎመው፡፡ ሆኖም ቀድሞውኑ በኃጢአታችን ተጸጽተን አውጥተን ልንጥላቸው ፈቃደኛ ካልሆንን፤ የይቅርታው መንፈስ በሕልውናችን ውስጥ ስፍራ የሚይይዝበትን ቦታ በማጣት ከኛ ለመራቅ ያለ አማራጭ ይገደዳል፡፡

   ስለመናዘዝ ስንነጋገር፤ አስፈላጊ ሆኖ የሚነሣው ጥያቄ "ኃጢአታችንን ለማን እንናዘዝ?" የሚለው ነው፡፡ እስቲ እንመልከተው፡፡

                  ሀ)  ለሰማያዊ ካህናት

"ንስሐ ከማያስፈልጋቸው ከዘጠና ዘጠኝ ጻድቃን ይልቅ ንስሐ በሚገባ በአንድ ኃጢአተኛ በሰማይ ደስታ ይሆናል።" (የሉቃስ ወንጌል 15፥7)

   በዕለተ እሁድ የተፈጠሩት ለባውያኑ ቅዱሳን መላእክት በሃይማኖታዊ አስተምህሮ ሰማያዊ ካህናት ተብለው ይጠራሉ፡፡ ምድር ላይ ሲሆን የምናየው ሁሉ የሰማዩን እውነት የተከተለ ነው፡፡ ይሄ መከተሉ ግን በሁለት አንጻር የሚገለጽ ነው፡፡ አንደኛ በጎ መንፈስ የሚመራው፤ የተቀደሰ ስብእና ባለቸው ሰዎች ውስጥ የሚገለጠው ቀጥተኛው መከተል ነው፡፡ ይሄኛው አንጻር "ፍቃድህ በሰማይ እንደሆነች እንዲሁ በምድርም ትሁን" ይላል፡፡ መለኮታዊው ኃይል በመላእክት ዘንድ የሚሠራውን ሥራ በእርሱም ላይ እንዲፈጽም ይለምናል፡፡ የአርያሙ ምስጋና በእርሱም አንደበት እንዲቀነቀን ይጠይቃል፡፡ መንፈሳዊው ሥርዓት በሕይወቱ ላይ እንዲታይለት ይማጸናል፡፡ ሁለተኛው ደግሞ የዘንዶው (ዲያቢሎስ) አካሄድ ነው፡፡

   ባሳለፉት ክፍሎች እንዳወሳነው፤ ክፉው መንፈስ ከሰማዩ ሥራ ፊት ይቆማል፡፡ ጻድቅ ነፍስ ያላቸው ሰዎች የሚፈጽሙትን እያየ የርሱን ሥራ ይሠራል፡፡ በእግዚአብሔር በኩል ሲተገበር ያስተዋለውን በራሱ አቅጣጫ ለውጦ በማከናወን "እኔ ፈጥርሁ" ይላል፡፡ ሐሳዊ መሲሕ ማለት ነው (መሲሑ የሠራውን ሥራ በራሱ የሐሰት መንገድ ተርጉሞ ይሠራና "የእኔ ነው" ይላል)፡፡

   ወደ ነጥባችን ስንመለስ፤ በቤተክርስቲያን የመቅደስ አገልግሎት ሲፈጸም የምናየው የክህነት ሥራ የሰማዩ ዓለም ነጸብራቅ ነው፡፡ በሌላ አባባል በጎው መንፈስ በሰማይ ያለውን ፈቃዱን በምድር በመግለጡ ነው፤ ቅዳሴን፣ ምስጋናን፣ ማኅሌትን፣ ኪዳንንና ሌሎች መንፈሳዊ ሥርዓቶችን በቤተክርስቲያን እንድንፈጽም የሆነው፡፡ ወይንም እዚህ በምድር የምንካፈላቸው መንፈሳዊ ሥርዓቶች የሰማዩ እውነት ምሳሌዎች ናቸው፡፡ ስለዚህ በምድር የምናያቸው ካህናት (የነፍስ አባቶቻችን) በሰማይ ያሉትን ካህናት (መላእክት) የሚወክሉ ናቸው፡፡ አክሲማሮስ አሳባችንን ያጸናልናል፦

"ሁለተኛም ዐሥሩን ነገድ ስማቸውን ኪሩቤል አላቸው፤ እነዚህም ካህናት ናቸው፤ የቀሳውስት አምሳል ናቸው"
"ሦስተኛም ዐሥሩን ነገድ ስማቸውን ሱራፌል አላቸው፤ የዲያቆናት አምሳል ናቸው፤ እነዚህም ዛሬ ዲያቆናት ተንሥኡ ለጸሎት ብለው እንዲጀምሩ ሁሉ የምስጋና ነቅዕ፣ የምስጋና ምንጭ በነዚያ ይጀመራል"

                                               መጽሐፈ አክሲማሮስ ዘእሑድ

የመላእክት መልክአ ጸሎት ደግሞ የሚከተለውን ይጨምራል፦

፴፫• ለከርሥከ፡፡ ... ሰማያዊው ካህን ሆይ በሰባተኛው ሰማይ የመሠዊያ አዳራሽ ቆመህ በጸሎትህ ኃጢአቴን ታስተሠርይ ዘንድ እኔ አጋልጋይህ ካህኑ ሚካኤል እያልኩ እማልድሃለሁ፡፡
                                                  መልክአ ሚካኤል

፭• ለገጽከ፡፡ ... ገብርኤል ሆይ በንጽሕና ልብሰ ተክህኖ የተሰየምክ አንተ በፍርድ ያይደለ በክርስቶስ ቸርነት እድን ዘንድ የነግሁንና የሠርኩን መሥዋዕት በምታሣርግበት ጊዜ የእኔን የኃጥኡን ኃጢአት አስተሠርይ፡፡
                                                  መልክአ ገብርኤል

፲፭• ለእመትከ፡፡ ... ሩፋኤል ሆይ የአምላክ ካህን ሚስጢረ ቅዳሴ ቀዳሽ አንተ ነህ፡፡
                                                   መልክአ ሩፋኤል

   ለምሳሌ ያህል ይህንን ካልን ይበቃል፡፡ ለማለት የተፈለገው መላእክትም እንደ ነፍስ አባት የሚያገለግሉን ሰማያዊ ካህናት ናቸው ነው፡፡ ስለዚህ ኃጢአታችንን ለእነርሱም በጸሎት መልክ መናዘዝ እንችላለን፡፡

   ባሳለፍነው ክፍል ላይ ኃጢአትን ለራስ መናዘዝና ስለ ንሰሐ በርዕስ መጸለይ ስንል ያነሣውን አሳብ እዚህ ከጠቀስነው የሰማያውያን ካህናት አገልግሎት ጋር ማያያዝ እንችላለን፡፡ ማለትም ራሳችንን የምንወቅስበትን ጸሎትና ስለ ንስሐ የምናቀርበውን ልመና አድራሻውን ወደ አንድ የተወደደ መልአክ ብናደርገው ብዙ እንጠቀማለን፡፡ (በነገራችን መጋቢ ሐዲሱ የኔ ነፍስ አባት ነው)

   መላእክትን እንደ ንስሐ አባቶች አድርገን ጸሎተ ኑዛዜን ማቅረብ በዋነኝነት ሁለት ጥቅም ይሰጠናል፡፡ አንደኛ መድኃኒቱ እንደተናገረው በአንድ ኃጥእ ነፍስ መመለስ በደስታ የሚሞሉት መላእክት፤ የንስሐ ጉዞአችንን አሳልፈን ስንሰጣቸው፤ በተሰጣቸው የተራድኦ አገልግሎትና በመንፈሳዊ ድጋፍ ንሰሐችንን በሰላም ጀምረን እንድንጨርስ ያግዙናል፡፡ ሁለተኛው ደግሞ የክፋት ካህን የሆኑት ክፉ መላእክት ከንስሐ ጎዳናችን ላይ ጋሬጣ ሊሆኑ መቆማቸው የማይቀር በመሆኑ፤ እነርሱን ይዋጉልናል፡፡

   እንደ ማሳሰቢያ የምትይዙልኝ፤ መላእክትን የነፍስ አባት አድርገን የመያዝ መንፈሳዊ ልምምድን ስንማር ምድራዊያን ካህናት አያስፈልጉንም ወደሚለው አሳብ በጭራሽ እንዳይመጣ፡፡ ምክንያቱም የረቂቃኑንም የግዙፋኑም ካህናት ሊቅ የሆነው ተወዳጁ፤ በሥጋ በተገለጠ ጊዜ ኃጢአትን የማስተሠረይ ሥራን በተጨባጭ ይሠራ ነበር፡፡ ይህንንም ሥልጣኑን ለተማሪዎቹ በመንፈስ ቅዱስ በኩል አቀብሏቸዋል፡፡ ስለዚህ የሥጋ አባቶች አያስፈልጉኝም የሚል ማንኛውም ሰው ይህንን የሐዲስ ኪዳኑን ሥርዓት እየከዳ ነው፡፡ እሰቲ ወደ ምድራዊያን ካህናቶች ደግሞ እንምጣ፡፡

                ለ)  ለምድራዊ ካህናት

"ኃጢአታቸውን ይቅር ያላችኋቸው ሁሉ ይቀርላቸዋል፤ የያዛችሁባቸው ተይዞባቸዋል አላቸው።" (የዮሐንስ ወንጌል 20፥23)

   መድኃኒቱ ክርስቶስ በሐዲስ ኪዳን የምሕረት ዘመን ከሰጠን አንዱ ሥርዓት መካከል የክህነቱ አገልግሎት ይገኝበታል፡፡

    መሲሑ ተሰቅሎ ከሞተ በኋላ ምስክሮቹ ሐዋሪያት ያስተማራቸውን የትንሣኤ ትምሕርት ዘንግተው፥ በፍርሃት የተነሣም ደጆችን ዘግተው፥ ሳሉ ሞትን ድል ያደረገው ጌታ በተዘጋ በር አልፎ በመግባት "ሰላም ለእናንተ ይሁን" አላቸው፡፡ ለጥቆም አስትንፋሱን በነርሱ ላይ አሳረፈና "መንፈስ ቅዱስን ተቀበሉ፤ በምድር የፈታችሁት ሁሉ በሰማይ የተፈታ ይሁን፤ በምድር ያሠራችሁት በሰማይም የታሠረ ይሁን" ሲል ቀደም ሲል በጴጥሮስ በኩል ሰጥቶአቸው የነበረውን ሥልጣነ ክህነት አጸደቀላቸው፡፡



tgoop.com/bemaledanek/2364
Create:
Last Update:

2•  ንስሐ

   2.4•  ለንስሐ እንዴት እንዘጋጅ?

ክፍል - ፰

                 ✞ ለማንና እንዴት እንናዘዝ

   ከንስሐ ሂደት ውስጥ ወደ መጨረሻው አከባቢ የምናገኘው ክፍል "ኃጢአትን የመናዘዝ" ክፍል ነው፡፡ መናዘዝ በጥሬ ቃሉ አደራን መናገር፣ ሚስጢርን ማውጣት፣ ጥፋትን ማስረዳት፣ ስሕተትን መግለጥ ከሚሉ ግሶች ጋር አቻ ይገጥማል፡፡

   መናዘዝ የንስሐ መሠረታዊ አምድ ተደርጎ ቢወሰድ ትክክል ነው፡፡ ምክንያቱም ንስሐ ማለት የኃጢአት ሥርየት የሚገኝበት መንፈሳዊ ሕይወት በመሆኑ፤ በእግዚአብሔር ላይ ዓምፀን ያሳለፍናቸው ጊዜያት ሳይደበቁ ጥፋትነታቸውን መግለጥ ስንችል ነው ምሕረት የሚሰኘው ቀጣዩ የአምላክ ፍቅር የሚተረጎመው፡፡ ሆኖም ቀድሞውኑ በኃጢአታችን ተጸጽተን አውጥተን ልንጥላቸው ፈቃደኛ ካልሆንን፤ የይቅርታው መንፈስ በሕልውናችን ውስጥ ስፍራ የሚይይዝበትን ቦታ በማጣት ከኛ ለመራቅ ያለ አማራጭ ይገደዳል፡፡

   ስለመናዘዝ ስንነጋገር፤ አስፈላጊ ሆኖ የሚነሣው ጥያቄ "ኃጢአታችንን ለማን እንናዘዝ?" የሚለው ነው፡፡ እስቲ እንመልከተው፡፡

                  ሀ)  ለሰማያዊ ካህናት

"ንስሐ ከማያስፈልጋቸው ከዘጠና ዘጠኝ ጻድቃን ይልቅ ንስሐ በሚገባ በአንድ ኃጢአተኛ በሰማይ ደስታ ይሆናል።" (የሉቃስ ወንጌል 15፥7)

   በዕለተ እሁድ የተፈጠሩት ለባውያኑ ቅዱሳን መላእክት በሃይማኖታዊ አስተምህሮ ሰማያዊ ካህናት ተብለው ይጠራሉ፡፡ ምድር ላይ ሲሆን የምናየው ሁሉ የሰማዩን እውነት የተከተለ ነው፡፡ ይሄ መከተሉ ግን በሁለት አንጻር የሚገለጽ ነው፡፡ አንደኛ በጎ መንፈስ የሚመራው፤ የተቀደሰ ስብእና ባለቸው ሰዎች ውስጥ የሚገለጠው ቀጥተኛው መከተል ነው፡፡ ይሄኛው አንጻር "ፍቃድህ በሰማይ እንደሆነች እንዲሁ በምድርም ትሁን" ይላል፡፡ መለኮታዊው ኃይል በመላእክት ዘንድ የሚሠራውን ሥራ በእርሱም ላይ እንዲፈጽም ይለምናል፡፡ የአርያሙ ምስጋና በእርሱም አንደበት እንዲቀነቀን ይጠይቃል፡፡ መንፈሳዊው ሥርዓት በሕይወቱ ላይ እንዲታይለት ይማጸናል፡፡ ሁለተኛው ደግሞ የዘንዶው (ዲያቢሎስ) አካሄድ ነው፡፡

   ባሳለፉት ክፍሎች እንዳወሳነው፤ ክፉው መንፈስ ከሰማዩ ሥራ ፊት ይቆማል፡፡ ጻድቅ ነፍስ ያላቸው ሰዎች የሚፈጽሙትን እያየ የርሱን ሥራ ይሠራል፡፡ በእግዚአብሔር በኩል ሲተገበር ያስተዋለውን በራሱ አቅጣጫ ለውጦ በማከናወን "እኔ ፈጥርሁ" ይላል፡፡ ሐሳዊ መሲሕ ማለት ነው (መሲሑ የሠራውን ሥራ በራሱ የሐሰት መንገድ ተርጉሞ ይሠራና "የእኔ ነው" ይላል)፡፡

   ወደ ነጥባችን ስንመለስ፤ በቤተክርስቲያን የመቅደስ አገልግሎት ሲፈጸም የምናየው የክህነት ሥራ የሰማዩ ዓለም ነጸብራቅ ነው፡፡ በሌላ አባባል በጎው መንፈስ በሰማይ ያለውን ፈቃዱን በምድር በመግለጡ ነው፤ ቅዳሴን፣ ምስጋናን፣ ማኅሌትን፣ ኪዳንንና ሌሎች መንፈሳዊ ሥርዓቶችን በቤተክርስቲያን እንድንፈጽም የሆነው፡፡ ወይንም እዚህ በምድር የምንካፈላቸው መንፈሳዊ ሥርዓቶች የሰማዩ እውነት ምሳሌዎች ናቸው፡፡ ስለዚህ በምድር የምናያቸው ካህናት (የነፍስ አባቶቻችን) በሰማይ ያሉትን ካህናት (መላእክት) የሚወክሉ ናቸው፡፡ አክሲማሮስ አሳባችንን ያጸናልናል፦

"ሁለተኛም ዐሥሩን ነገድ ስማቸውን ኪሩቤል አላቸው፤ እነዚህም ካህናት ናቸው፤ የቀሳውስት አምሳል ናቸው"
"ሦስተኛም ዐሥሩን ነገድ ስማቸውን ሱራፌል አላቸው፤ የዲያቆናት አምሳል ናቸው፤ እነዚህም ዛሬ ዲያቆናት ተንሥኡ ለጸሎት ብለው እንዲጀምሩ ሁሉ የምስጋና ነቅዕ፣ የምስጋና ምንጭ በነዚያ ይጀመራል"

                                               መጽሐፈ አክሲማሮስ ዘእሑድ

የመላእክት መልክአ ጸሎት ደግሞ የሚከተለውን ይጨምራል፦

፴፫• ለከርሥከ፡፡ ... ሰማያዊው ካህን ሆይ በሰባተኛው ሰማይ የመሠዊያ አዳራሽ ቆመህ በጸሎትህ ኃጢአቴን ታስተሠርይ ዘንድ እኔ አጋልጋይህ ካህኑ ሚካኤል እያልኩ እማልድሃለሁ፡፡
                                                  መልክአ ሚካኤል

፭• ለገጽከ፡፡ ... ገብርኤል ሆይ በንጽሕና ልብሰ ተክህኖ የተሰየምክ አንተ በፍርድ ያይደለ በክርስቶስ ቸርነት እድን ዘንድ የነግሁንና የሠርኩን መሥዋዕት በምታሣርግበት ጊዜ የእኔን የኃጥኡን ኃጢአት አስተሠርይ፡፡
                                                  መልክአ ገብርኤል

፲፭• ለእመትከ፡፡ ... ሩፋኤል ሆይ የአምላክ ካህን ሚስጢረ ቅዳሴ ቀዳሽ አንተ ነህ፡፡
                                                   መልክአ ሩፋኤል

   ለምሳሌ ያህል ይህንን ካልን ይበቃል፡፡ ለማለት የተፈለገው መላእክትም እንደ ነፍስ አባት የሚያገለግሉን ሰማያዊ ካህናት ናቸው ነው፡፡ ስለዚህ ኃጢአታችንን ለእነርሱም በጸሎት መልክ መናዘዝ እንችላለን፡፡

   ባሳለፍነው ክፍል ላይ ኃጢአትን ለራስ መናዘዝና ስለ ንሰሐ በርዕስ መጸለይ ስንል ያነሣውን አሳብ እዚህ ከጠቀስነው የሰማያውያን ካህናት አገልግሎት ጋር ማያያዝ እንችላለን፡፡ ማለትም ራሳችንን የምንወቅስበትን ጸሎትና ስለ ንስሐ የምናቀርበውን ልመና አድራሻውን ወደ አንድ የተወደደ መልአክ ብናደርገው ብዙ እንጠቀማለን፡፡ (በነገራችን መጋቢ ሐዲሱ የኔ ነፍስ አባት ነው)

   መላእክትን እንደ ንስሐ አባቶች አድርገን ጸሎተ ኑዛዜን ማቅረብ በዋነኝነት ሁለት ጥቅም ይሰጠናል፡፡ አንደኛ መድኃኒቱ እንደተናገረው በአንድ ኃጥእ ነፍስ መመለስ በደስታ የሚሞሉት መላእክት፤ የንስሐ ጉዞአችንን አሳልፈን ስንሰጣቸው፤ በተሰጣቸው የተራድኦ አገልግሎትና በመንፈሳዊ ድጋፍ ንሰሐችንን በሰላም ጀምረን እንድንጨርስ ያግዙናል፡፡ ሁለተኛው ደግሞ የክፋት ካህን የሆኑት ክፉ መላእክት ከንስሐ ጎዳናችን ላይ ጋሬጣ ሊሆኑ መቆማቸው የማይቀር በመሆኑ፤ እነርሱን ይዋጉልናል፡፡

   እንደ ማሳሰቢያ የምትይዙልኝ፤ መላእክትን የነፍስ አባት አድርገን የመያዝ መንፈሳዊ ልምምድን ስንማር ምድራዊያን ካህናት አያስፈልጉንም ወደሚለው አሳብ በጭራሽ እንዳይመጣ፡፡ ምክንያቱም የረቂቃኑንም የግዙፋኑም ካህናት ሊቅ የሆነው ተወዳጁ፤ በሥጋ በተገለጠ ጊዜ ኃጢአትን የማስተሠረይ ሥራን በተጨባጭ ይሠራ ነበር፡፡ ይህንንም ሥልጣኑን ለተማሪዎቹ በመንፈስ ቅዱስ በኩል አቀብሏቸዋል፡፡ ስለዚህ የሥጋ አባቶች አያስፈልጉኝም የሚል ማንኛውም ሰው ይህንን የሐዲስ ኪዳኑን ሥርዓት እየከዳ ነው፡፡ እሰቲ ወደ ምድራዊያን ካህናቶች ደግሞ እንምጣ፡፡

                ለ)  ለምድራዊ ካህናት

"ኃጢአታቸውን ይቅር ያላችኋቸው ሁሉ ይቀርላቸዋል፤ የያዛችሁባቸው ተይዞባቸዋል አላቸው።" (የዮሐንስ ወንጌል 20፥23)

   መድኃኒቱ ክርስቶስ በሐዲስ ኪዳን የምሕረት ዘመን ከሰጠን አንዱ ሥርዓት መካከል የክህነቱ አገልግሎት ይገኝበታል፡፡

    መሲሑ ተሰቅሎ ከሞተ በኋላ ምስክሮቹ ሐዋሪያት ያስተማራቸውን የትንሣኤ ትምሕርት ዘንግተው፥ በፍርሃት የተነሣም ደጆችን ዘግተው፥ ሳሉ ሞትን ድል ያደረገው ጌታ በተዘጋ በር አልፎ በመግባት "ሰላም ለእናንተ ይሁን" አላቸው፡፡ ለጥቆም አስትንፋሱን በነርሱ ላይ አሳረፈና "መንፈስ ቅዱስን ተቀበሉ፤ በምድር የፈታችሁት ሁሉ በሰማይ የተፈታ ይሁን፤ በምድር ያሠራችሁት በሰማይም የታሠረ ይሁን" ሲል ቀደም ሲል በጴጥሮስ በኩል ሰጥቶአቸው የነበረውን ሥልጣነ ክህነት አጸደቀላቸው፡፡

BY በማለዳ ንቁ ቁጥር ! ፪


Share with your friend now:
tgoop.com/bemaledanek/2364

View MORE
Open in Telegram


Telegram News

Date: |

How to Create a Private or Public Channel on Telegram? Today, we will address Telegram channels and how to use them for maximum benefit. Select “New Channel” The main design elements of your Telegram channel include a name, bio (brief description), and avatar. Your bio should be: "Doxxing content is forbidden on Telegram and our moderators routinely remove such content from around the world," said a spokesman for the messaging app, Remi Vaughn.
from us


Telegram በማለዳ ንቁ ቁጥር ! ፪
FROM American