BEMALEDANEK Telegram 2365
  እግዚአብሔር በባሕሪይው ሕያው ነው፡፡ ከዚህ የተነሣ አሳቡም፣ ቃሉም፣ አነዋወሩም ሕያው ነው፡፡ ለአዳም የተናገረው ቃል እስከ ዓለም ፍጻሜ ድረስ የሚደመጥ ሕያው ቃል ነው፡፡ የእግዚአብሔር ነገር በቦታና በጊዜ የተወሰነ ቢሆን ኖሮ መጽሐፍ ቅዱስ ውድቅ ይሆን ነበር፡፡ በነ'አብርሃም ሕይወት የሆነው የአምላክ ሥራ በኛ ላይ የማይሆን ከሆነ፤ ታሪካቸውን ማወቅ ብቻ ምን ይጠቅማል?

   ይህንንም ጉዳይ መድኃኒቱ ለደቀመዛሙርቱ ሲያረጋግጥላቸው እንዲህ ይላቸዋል፤ "እነሆም እኔ እስከ ዓለም ፍጻሜ ድረስ ሁልጊዜ ከእናንተ ጋር ነኝ።" (የማቴዎስ ወንጌል 28፥19-20)

   እስከ ምፅዓት ድረስ ከእናንተ ጋር አለሁ ካለ፤ የተናገራቸውና የሰጣቸውም ሥልጣን በባሕሪይ ሕያው ሆኖ ይቀጥላል ማለት ነው፡፡ እነ ጴጥሮስ በሥጋ ቢሞቱም፤ በነርሱ ባሕሪይ የተጻፈው ክህነት መንፈሳዊውን ሰንሰለት ጠብቀው በሚቀጥሉ ሰዎች ላይ መነበቡን ይቀጥላል፡፡ መድኃኒቱ በሐዋሪያቱ ላይ እፍ ያለው ሕያው እስትንፋስ የሚሠርጽበት ሰማያዊ ሥርዓት እስካልተቋረጠ ድረስ በካህናት ላይ ያለው ሥልጣን የመንፈስ ቅዱስ ሥልጣን ነው፡፡

  እዚህ ጋር አንድ ነገር እናንሣ፡፡ በባሕሪይ የሚቀጥለው የነ'ጴጥሮስ ክህነት ብቻ አይደለም፡፡ የነ'ሐና (የኦሪቱ ሊቀ ካህን) ሥልጣንም እንደቀጠለ አለ፡፡ ክርስቶሳዊውን የመገለጥ ስብእና የሚያሳድዱ ከእውነተኞቹ አንጻር የቆሙ የብሉይ ካህናት እንደሚኖሩ ማስተዋል መልካም ነው፡፡ በዘልማድነት የሚታወቅ፤ አገልጋዮችን ክፉ መንፈስ አያጠቃም የሚል አስተሳሰብ፤ በብዙ ምዕመናን ላይ አለ፡፡ ግን ልብ እንበል፤ እንኳን "በሥጋቸው ቄሣር፥ በነፍሳቸው ዲያቢሎስ" የተቆራኛቸውን የብሉይ አገልጋዮች ቀርቶ፤ የሰማይ በሮች መክፈቻ የተሰጠውን ደቀመዝሙርም ሰይጣን እንዳሳተው መጽሐፍ ቅዱስ ይናገራል፡፡ (የማርቆስ ወንጌል 8፥33)

   ስለዚህም ነው ሰማያዊ ካህናትን ከጎን ማድረጉ ተገቢ ነው የሚያሰኘው፡፡ ዲያቢሎስ በአገልጋዮችም በኩል ሥጋዊ ምክንያትን፣ የእውቀት መጋረጃንና ድብቅ አጀንዳን ተገን አድርጎ ብዙ ፈተና ሊያመጣ ይችላል፡፡ ይህንን ፈተና የምናልፈው ደግሞ በሰማያውያኑ እርዳታ ነው፡፡

  እንዲህ ሲባል ካህናትን የመናቅ፣ አሳንሶ የማየትና የመራቅ አዝማሚያ በአእምሮ ምናብ እንዳይቀረጽ በማጤን አንብቡ እላለሁ፡፡ ካህናትን መሳደብና ማብጠልጠል የዚህ ዘመን አንድ "የማወቅ ፋሽን" መገለጫ ሆኗል፡፡ ይሄ ፍጹም ስሕተት ነው፡፡ ሲያልፍም የዲያቢሎስ ስልታዊ ምሪት ነው፡፡

   በተገቢው ሥርዓትና አካሄድ የሐዲስ ኪዳንን ሥልጣን የተቀበሉ ካህናትን ሁሉ ማክበር መንፈስ ቅዱስን ማክበር ነው፡፡ ምንም አይነት የግል ሕይወት ይኑራቸው፤ ለክህነታቸው ተገቢውን ቦታ መስጠት የክርስቲያኖች ኃላፊነት ነው፡፡ በኃጢአት ውስጥም እየተመላለሱ ሳለ፤ ሥልጣን የሰጣቸውን መንፈሳዊ እውነት እስካልከዱ ድረስ በንጹሑ ልቦና "ከኃጢአት ማሠሪያ ይፍታህ" ሲል የጸለዩለት ነፍስ ሁሉ ነጻ ይወጣል፡፡ ላጠፉት ጥፋታቸው ክህነታቸው ሳይሆን ራሳቸው በግል ይጠየቃሉ፡፡ ሲጠቃለል አገልጋዮች በተሰማሩበት መንፈሳዊ ሥራ ላይ ሁሉ ልበ ቀና ድጋፍን፣ ትሕትናን፣ ክብርንና መታዘዝን መሥዋዕት አድርጎ መግለጥ ታላቅ አስተዋይነትና ምዕመናዊ ድርሻም ጭምር ነው፡፡

   ይህን የማስተዋል ኃይል ይዘን ሳለ፤ የሴረኛውን መንፈስ ወጥመድ ለማክሸፍ ሰማያዊ ካህናትን ማሰለፍ ደግሞ ብልህነት ነው፡፡ ስለ ክፉ መንፈስ ባሕሪይና ውጊያ በቂ መረጃ የሌላቸውን ሰዎች ከለላ ያደረገ መሰናክልን ለመሻገር ረቂቃኑን ቀሳውስት መያዝ የማይታየውን ፍልሚያ የማየት ክህሎት ነው፡፡ ከዚያም በላይ ልበ ንጹሕ (በጎቹ) የሆኑ የነፍስ አባቶችን (እረኞችን) ምናልባት የገባንን ያህል የውጊያ ሕይወት ለማሳየት ዕድል የሚሰጥ አጋጣሚን ለመጠቀምም መላእክቱ ያስፈልጉናል፡፡ ፍቅር ተዓምረኛ ነው፤ የማይሠራው ሥራ የለም!

       ✞ ኃጢአትን እንዴት እናዘዝ ? ✞

  ግልጽ ነው፤ ለሰማያዊያን ካህናት የምንናዘዘው በንስሐ ጸሎት በኩል ነው፡፡ በነገራችን ላይ ቅዱሳንም የረቂቁ መቅደስ ተሳታፊዎች እስከሆኑ ድረስ የንስሐ ጸሎታችንን ተቀብለው ሊያግዙን ይችላሉ፡፡ የመናዘዝ እንዴትነት ዝርዝር የሚያስፈልገው ለምድራዊያን ካህናት ነው፡፡ የሚከተሉትን የመናዘዝ መሥፈርቶች ማወቅ ተገቢ ነው፦
  
ሀ)  ኃጢአትን ሁሉ ሳይደብቁ መናገር

  የንሰሐውን ጸሎት በግል ስናደርስ በሥጋ የምናየው አካል ስለሌለ፤ አእምሮአችን በግዙፍ መልክ የማያየውን ሕልውና እንደሌለ አድርጎ ስለሚወስድ፤ "የሚያሳፍሩ" የምንላቸውን ኃጢአቶቻችንን አውጥተን ለመናገር አንቸገር ይሆናል፡፡ ግን በሥጋ የምናያቸው ካህናት አጠገብ ስንሆን የማፈር፣ የመሸማቀቅና ምን ይሉኛል የማለት አሳብ ማመላለሳችን የሚጠበቅ ነው፡፡ አንድም ምድራዊ የነፍስ አባቶች ያስፈለጉት ለዚህ ነው፡፡

  አንድ አማኝ ሰው በኃጢአቱ ሊያፍር በእርግጥም ይገባዋል፡፡ የፈጸመው ጽድቅ አይደለምና ስሕተቱን ቢያዝንበት ተገቢ ነው፡፡ ይህ የሐፍረት ስሜት ንጹሕ መሆንን ከማመንና ከመፈለግ ጋር ተያያዥነት አለው፡፡ ስለዚህ አባቶች ፊት ኃጢአትን ሲናገሩ ማፈር ጤናማ ሰዋዊ ስሜት ነው፡፡

  ነገር ግን ይህ ስሜት ድንበሩን ጥሶ፤ ኃጢአቱን እስከ መሸሸግ የሚያድረስ ልክ ላይ ከደረሰ፤ በስሜት ውስጥ ገብቶ ጭንቅላት ላይ አሉታዊ ድምፅ እየሆነ ያለ የመንፈስ አሠራር  ስለመኖሩ ግንዛቤ ልናገኝ ያስፈልገናል፡፡

  የቱን ያህል አሳፋሪ ብለን ያስቀመጥናቸው የኃጢአት ታሪኮች ይኑሩን፤ ሁሉንም በመዘርዘር ለካህኑ መናዘዝ ይጠበቅብናል፡፡ ዲያቢሎስ ኃጢአትን እንደ ምሽግ አድርጎ ይቀመጥበታል ያለውን ትምሕርት እዚህ እናስታውስ፡፡ ባልተናዘዝነው ኃጢአት ውስጥ ገብቶ ለመደበቅ፤ መናገር ያለብንን እንዳንናገር የሐፍረትን ነገር ምክንያት አድርጎ ይፈታተናል፡፡

  ስለሆነ ካህን ፊት ቀርቦ ኃጢአትን ከመናዘዝ አስቀድሞ፤ የምናዘዛቸውን ሁሉ በሚገባ አሰታውሶና እንዳይጠፉም በወረቀት መዝግቦ መዘጋጀት፤ በኑዛዜ ጊዜ ያለውን የመንፈስ ውጊያ ያሸንፍልናል፡፡

ለ)  እግዚአብሔር ፊት እንደሚናገሩ ማሰብ

  ከላይ ባሉት አንቀጾች እንዳወጋነው፤ ኃጢአትን የመፍታት ሥልጣን በመድኃኒቱ እፍታ በኩል ለሰዎች ተሰጥቶአል፡፡ ማለትም መንፈስ ቅዱስ በካህናት ሥልጣን ላይ ሆኖ ኃጢአታችንን የሚያስተሠርይበት ሥርዓት ነው የተሠራው፡፡

  እንዲህ ከሆነ፤ ከካህናት ፊት ሆነን ስንናዘዝ፤ ከእግዚአብሔርም ፊት ቆመን ንስሐ እየገባን እንደሆነ ማመን ይገባል፡፡

  አንዳንድ ጊዜ ሰዎች በዓይን ሲመለከቱ የሚያዩት እንደነርሱ ያለን ሰው ስለሆነ፤ በካህኑ ሥልጣን ላይ የሚገኘውን መንፈስ ቅዱስ በመዘንጋት በቸልተኝነት "እንደ ነገሩ" ይናዘዛሉ፡፡ በሌላ አባባል ንስሐ እየገቡ እንደሆነ አምነው ሳይሆን የአዘቦት ቀን ጭውውት እያደረጉ እንደሆነ ያህል ለኑዛዜው የሚሠዋውን የእምነት ክብርና ቦታ ግዴለሸ ይሆኑበታል፡፡ ይሄ ደግሞ ለኃጢአቱ ሥርየት የሚታዘዘውን ቀኖና በአስፈላጊ ትጋትና ድካም እንዳንፈጽም ለክፉው በር የሚከፈት ጠባይ ነው፡፡

  "እንኳንስ ዘንቦብሽ.." የሚለው አባባል ለዲያቢሎስም ይሠራልና፤ እንኳንስ ግዴለሽ የመሆንን ጠባይ አግኝቶ አይደለም በንቃትና በቁርጠኝነት እየታገልነውም ሳለ፤ ጥቃቅን ስሕተቶችን ሰብስቦ ትልቅ ክምር የሚያህል ፍልሚያን የሚያመጣብን አደገኛ ፍጡር ነው፡፡ በመሆኑም ከካህናት ጋር ስንነጋገር፤ ለአምላክ መንፈስ በሚገባ "የአቤል መሥዋዕት" ልክ ትኩረት ሰጥተን ቢሆን መልካም ነው፡፡

ወደ ሥጋና ደሙ መጓዛችንን እንቀጥላለን. . .
@bemaledanek



tgoop.com/bemaledanek/2365
Create:
Last Update:

  እግዚአብሔር በባሕሪይው ሕያው ነው፡፡ ከዚህ የተነሣ አሳቡም፣ ቃሉም፣ አነዋወሩም ሕያው ነው፡፡ ለአዳም የተናገረው ቃል እስከ ዓለም ፍጻሜ ድረስ የሚደመጥ ሕያው ቃል ነው፡፡ የእግዚአብሔር ነገር በቦታና በጊዜ የተወሰነ ቢሆን ኖሮ መጽሐፍ ቅዱስ ውድቅ ይሆን ነበር፡፡ በነ'አብርሃም ሕይወት የሆነው የአምላክ ሥራ በኛ ላይ የማይሆን ከሆነ፤ ታሪካቸውን ማወቅ ብቻ ምን ይጠቅማል?

   ይህንንም ጉዳይ መድኃኒቱ ለደቀመዛሙርቱ ሲያረጋግጥላቸው እንዲህ ይላቸዋል፤ "እነሆም እኔ እስከ ዓለም ፍጻሜ ድረስ ሁልጊዜ ከእናንተ ጋር ነኝ።" (የማቴዎስ ወንጌል 28፥19-20)

   እስከ ምፅዓት ድረስ ከእናንተ ጋር አለሁ ካለ፤ የተናገራቸውና የሰጣቸውም ሥልጣን በባሕሪይ ሕያው ሆኖ ይቀጥላል ማለት ነው፡፡ እነ ጴጥሮስ በሥጋ ቢሞቱም፤ በነርሱ ባሕሪይ የተጻፈው ክህነት መንፈሳዊውን ሰንሰለት ጠብቀው በሚቀጥሉ ሰዎች ላይ መነበቡን ይቀጥላል፡፡ መድኃኒቱ በሐዋሪያቱ ላይ እፍ ያለው ሕያው እስትንፋስ የሚሠርጽበት ሰማያዊ ሥርዓት እስካልተቋረጠ ድረስ በካህናት ላይ ያለው ሥልጣን የመንፈስ ቅዱስ ሥልጣን ነው፡፡

  እዚህ ጋር አንድ ነገር እናንሣ፡፡ በባሕሪይ የሚቀጥለው የነ'ጴጥሮስ ክህነት ብቻ አይደለም፡፡ የነ'ሐና (የኦሪቱ ሊቀ ካህን) ሥልጣንም እንደቀጠለ አለ፡፡ ክርስቶሳዊውን የመገለጥ ስብእና የሚያሳድዱ ከእውነተኞቹ አንጻር የቆሙ የብሉይ ካህናት እንደሚኖሩ ማስተዋል መልካም ነው፡፡ በዘልማድነት የሚታወቅ፤ አገልጋዮችን ክፉ መንፈስ አያጠቃም የሚል አስተሳሰብ፤ በብዙ ምዕመናን ላይ አለ፡፡ ግን ልብ እንበል፤ እንኳን "በሥጋቸው ቄሣር፥ በነፍሳቸው ዲያቢሎስ" የተቆራኛቸውን የብሉይ አገልጋዮች ቀርቶ፤ የሰማይ በሮች መክፈቻ የተሰጠውን ደቀመዝሙርም ሰይጣን እንዳሳተው መጽሐፍ ቅዱስ ይናገራል፡፡ (የማርቆስ ወንጌል 8፥33)

   ስለዚህም ነው ሰማያዊ ካህናትን ከጎን ማድረጉ ተገቢ ነው የሚያሰኘው፡፡ ዲያቢሎስ በአገልጋዮችም በኩል ሥጋዊ ምክንያትን፣ የእውቀት መጋረጃንና ድብቅ አጀንዳን ተገን አድርጎ ብዙ ፈተና ሊያመጣ ይችላል፡፡ ይህንን ፈተና የምናልፈው ደግሞ በሰማያውያኑ እርዳታ ነው፡፡

  እንዲህ ሲባል ካህናትን የመናቅ፣ አሳንሶ የማየትና የመራቅ አዝማሚያ በአእምሮ ምናብ እንዳይቀረጽ በማጤን አንብቡ እላለሁ፡፡ ካህናትን መሳደብና ማብጠልጠል የዚህ ዘመን አንድ "የማወቅ ፋሽን" መገለጫ ሆኗል፡፡ ይሄ ፍጹም ስሕተት ነው፡፡ ሲያልፍም የዲያቢሎስ ስልታዊ ምሪት ነው፡፡

   በተገቢው ሥርዓትና አካሄድ የሐዲስ ኪዳንን ሥልጣን የተቀበሉ ካህናትን ሁሉ ማክበር መንፈስ ቅዱስን ማክበር ነው፡፡ ምንም አይነት የግል ሕይወት ይኑራቸው፤ ለክህነታቸው ተገቢውን ቦታ መስጠት የክርስቲያኖች ኃላፊነት ነው፡፡ በኃጢአት ውስጥም እየተመላለሱ ሳለ፤ ሥልጣን የሰጣቸውን መንፈሳዊ እውነት እስካልከዱ ድረስ በንጹሑ ልቦና "ከኃጢአት ማሠሪያ ይፍታህ" ሲል የጸለዩለት ነፍስ ሁሉ ነጻ ይወጣል፡፡ ላጠፉት ጥፋታቸው ክህነታቸው ሳይሆን ራሳቸው በግል ይጠየቃሉ፡፡ ሲጠቃለል አገልጋዮች በተሰማሩበት መንፈሳዊ ሥራ ላይ ሁሉ ልበ ቀና ድጋፍን፣ ትሕትናን፣ ክብርንና መታዘዝን መሥዋዕት አድርጎ መግለጥ ታላቅ አስተዋይነትና ምዕመናዊ ድርሻም ጭምር ነው፡፡

   ይህን የማስተዋል ኃይል ይዘን ሳለ፤ የሴረኛውን መንፈስ ወጥመድ ለማክሸፍ ሰማያዊ ካህናትን ማሰለፍ ደግሞ ብልህነት ነው፡፡ ስለ ክፉ መንፈስ ባሕሪይና ውጊያ በቂ መረጃ የሌላቸውን ሰዎች ከለላ ያደረገ መሰናክልን ለመሻገር ረቂቃኑን ቀሳውስት መያዝ የማይታየውን ፍልሚያ የማየት ክህሎት ነው፡፡ ከዚያም በላይ ልበ ንጹሕ (በጎቹ) የሆኑ የነፍስ አባቶችን (እረኞችን) ምናልባት የገባንን ያህል የውጊያ ሕይወት ለማሳየት ዕድል የሚሰጥ አጋጣሚን ለመጠቀምም መላእክቱ ያስፈልጉናል፡፡ ፍቅር ተዓምረኛ ነው፤ የማይሠራው ሥራ የለም!

       ✞ ኃጢአትን እንዴት እናዘዝ ? ✞

  ግልጽ ነው፤ ለሰማያዊያን ካህናት የምንናዘዘው በንስሐ ጸሎት በኩል ነው፡፡ በነገራችን ላይ ቅዱሳንም የረቂቁ መቅደስ ተሳታፊዎች እስከሆኑ ድረስ የንስሐ ጸሎታችንን ተቀብለው ሊያግዙን ይችላሉ፡፡ የመናዘዝ እንዴትነት ዝርዝር የሚያስፈልገው ለምድራዊያን ካህናት ነው፡፡ የሚከተሉትን የመናዘዝ መሥፈርቶች ማወቅ ተገቢ ነው፦
  
ሀ)  ኃጢአትን ሁሉ ሳይደብቁ መናገር

  የንሰሐውን ጸሎት በግል ስናደርስ በሥጋ የምናየው አካል ስለሌለ፤ አእምሮአችን በግዙፍ መልክ የማያየውን ሕልውና እንደሌለ አድርጎ ስለሚወስድ፤ "የሚያሳፍሩ" የምንላቸውን ኃጢአቶቻችንን አውጥተን ለመናገር አንቸገር ይሆናል፡፡ ግን በሥጋ የምናያቸው ካህናት አጠገብ ስንሆን የማፈር፣ የመሸማቀቅና ምን ይሉኛል የማለት አሳብ ማመላለሳችን የሚጠበቅ ነው፡፡ አንድም ምድራዊ የነፍስ አባቶች ያስፈለጉት ለዚህ ነው፡፡

  አንድ አማኝ ሰው በኃጢአቱ ሊያፍር በእርግጥም ይገባዋል፡፡ የፈጸመው ጽድቅ አይደለምና ስሕተቱን ቢያዝንበት ተገቢ ነው፡፡ ይህ የሐፍረት ስሜት ንጹሕ መሆንን ከማመንና ከመፈለግ ጋር ተያያዥነት አለው፡፡ ስለዚህ አባቶች ፊት ኃጢአትን ሲናገሩ ማፈር ጤናማ ሰዋዊ ስሜት ነው፡፡

  ነገር ግን ይህ ስሜት ድንበሩን ጥሶ፤ ኃጢአቱን እስከ መሸሸግ የሚያድረስ ልክ ላይ ከደረሰ፤ በስሜት ውስጥ ገብቶ ጭንቅላት ላይ አሉታዊ ድምፅ እየሆነ ያለ የመንፈስ አሠራር  ስለመኖሩ ግንዛቤ ልናገኝ ያስፈልገናል፡፡

  የቱን ያህል አሳፋሪ ብለን ያስቀመጥናቸው የኃጢአት ታሪኮች ይኑሩን፤ ሁሉንም በመዘርዘር ለካህኑ መናዘዝ ይጠበቅብናል፡፡ ዲያቢሎስ ኃጢአትን እንደ ምሽግ አድርጎ ይቀመጥበታል ያለውን ትምሕርት እዚህ እናስታውስ፡፡ ባልተናዘዝነው ኃጢአት ውስጥ ገብቶ ለመደበቅ፤ መናገር ያለብንን እንዳንናገር የሐፍረትን ነገር ምክንያት አድርጎ ይፈታተናል፡፡

  ስለሆነ ካህን ፊት ቀርቦ ኃጢአትን ከመናዘዝ አስቀድሞ፤ የምናዘዛቸውን ሁሉ በሚገባ አሰታውሶና እንዳይጠፉም በወረቀት መዝግቦ መዘጋጀት፤ በኑዛዜ ጊዜ ያለውን የመንፈስ ውጊያ ያሸንፍልናል፡፡

ለ)  እግዚአብሔር ፊት እንደሚናገሩ ማሰብ

  ከላይ ባሉት አንቀጾች እንዳወጋነው፤ ኃጢአትን የመፍታት ሥልጣን በመድኃኒቱ እፍታ በኩል ለሰዎች ተሰጥቶአል፡፡ ማለትም መንፈስ ቅዱስ በካህናት ሥልጣን ላይ ሆኖ ኃጢአታችንን የሚያስተሠርይበት ሥርዓት ነው የተሠራው፡፡

  እንዲህ ከሆነ፤ ከካህናት ፊት ሆነን ስንናዘዝ፤ ከእግዚአብሔርም ፊት ቆመን ንስሐ እየገባን እንደሆነ ማመን ይገባል፡፡

  አንዳንድ ጊዜ ሰዎች በዓይን ሲመለከቱ የሚያዩት እንደነርሱ ያለን ሰው ስለሆነ፤ በካህኑ ሥልጣን ላይ የሚገኘውን መንፈስ ቅዱስ በመዘንጋት በቸልተኝነት "እንደ ነገሩ" ይናዘዛሉ፡፡ በሌላ አባባል ንስሐ እየገቡ እንደሆነ አምነው ሳይሆን የአዘቦት ቀን ጭውውት እያደረጉ እንደሆነ ያህል ለኑዛዜው የሚሠዋውን የእምነት ክብርና ቦታ ግዴለሸ ይሆኑበታል፡፡ ይሄ ደግሞ ለኃጢአቱ ሥርየት የሚታዘዘውን ቀኖና በአስፈላጊ ትጋትና ድካም እንዳንፈጽም ለክፉው በር የሚከፈት ጠባይ ነው፡፡

  "እንኳንስ ዘንቦብሽ.." የሚለው አባባል ለዲያቢሎስም ይሠራልና፤ እንኳንስ ግዴለሽ የመሆንን ጠባይ አግኝቶ አይደለም በንቃትና በቁርጠኝነት እየታገልነውም ሳለ፤ ጥቃቅን ስሕተቶችን ሰብስቦ ትልቅ ክምር የሚያህል ፍልሚያን የሚያመጣብን አደገኛ ፍጡር ነው፡፡ በመሆኑም ከካህናት ጋር ስንነጋገር፤ ለአምላክ መንፈስ በሚገባ "የአቤል መሥዋዕት" ልክ ትኩረት ሰጥተን ቢሆን መልካም ነው፡፡

ወደ ሥጋና ደሙ መጓዛችንን እንቀጥላለን. . .
@bemaledanek

BY በማለዳ ንቁ ቁጥር ! ፪


Share with your friend now:
tgoop.com/bemaledanek/2365

View MORE
Open in Telegram


Telegram News

Date: |

Matt Hussey, editorial director of NEAR Protocol (and former editor-in-chief of Decrypt) responded to the news of the Telegram group with “#meIRL.” best-secure-messaging-apps-shutterstock-1892950018.jpg Telegram Channels requirements & features A new window will come up. Enter your channel name and bio. (See the character limits above.) Click “Create.” “Hey degen, are you stressed? Just let it all out,” he wrote, along with a link to join the group.
from us


Telegram በማለዳ ንቁ ቁጥር ! ፪
FROM American