BEMALEDANEK Telegram 2371
3•  ቅዱስ ቁርባን

     3.1•  ቅዱስ ቁርባን ምንድነው ?

ክፍል - ፩

          ✞ በልተን እንደወጣን በልተን እንመለሳለን

   "ለአዳም ሦስት ዕፅዋት ተሰጥተውት ነበር፤ አንዱን ሊጠብቀው፣ አንዱን ሊመገበው፣ አንዱን ሺሕ ዓመት ኖሮ ሊታደስበት፣ አትብላ ያለውን ዕፀ በለስ በበላ ጊዜ የሚታደስበት ዕፅ ተነሥቶታል፡፡ በሚታደስበት ዕፅ ሕይወትም ፈንታ ዛሬ ሥጋውና ደሙ ገብቶልናል፤ ሥጋውን ደሙን ተቀብለን፤ በልጅነት ታድሰን መንግሥተ ሰማያት የምንገባ ሆነናል፡፡"

                             (ኦሪት ዘልደት አንድምታ)


በአባት ዘንድ ታስበን ተፈጥረናል፡፡ የመጀመሪያው ሰው አዳም በእግዚአብሔር ልቦና ተጸንሶ፤ ሰው የተባለ ፍጥረት ሊሆን ሲወለድ፤ የባሕሪይ ዕድገቱን እንዲጨርስ ዔድን ገነት በተባለች ቦታ ገብቶአል፡፡ ማለት አዳም የተባለ እግዚአብሔር በፈቃዱ ጸንሶ ያስገኘው ልጅ፤ ገነት በተባለች ማኅፀን ውስጥ በባሕሪይ ያድግ ነበር፡፡

አዳም አካሉና ባሕሪዩ ከተፈጠረባት ጊዜ አንስቶ፤ እግዚአብሔር አስቀድሞ ወዳዘጋጀለት ከፍታ በባሕሪዩ ያድግ ነበር፡፡ ይሄ የዕድገት ቆይታ ደግሞ በገነት ሥርዓት አንድ ቀን ያህል ይፈጃል፡፡ በምድር (ከፀሐይ በታች ባለ ሥርዓት) ሲሆን አንድ ሺሕ ያህል ዓመት ይሆናል (2ኛ የጴጥሮስ መልእክት 3፥8)፡፡

አዳም በስድስተኛው ቀን አጋማሽ (አርብ 6:00) ላይ ተጸንሶ በመቀጠል ወደሚያድግበት ቦታ ወደ ገነት ገብቶአል፡፡ (ኦሪት ዘፍጥረት 2፥8) በገነትም አንዱን ቀን (ሺሕውን ዓመት) ቆይቶ ሲጨርስ ከዕፀ ሕይወት ዛፍ ይበላና ይታደሳል፡፡ በሌላ አነጋገር ሰባተኛው ቀን (ቅዳሜ) ሲገባ፤ አዳም ዕድገቱን ጨርሶ ሕያው በመሆን በእውቀትና በጥበብ ይወለዳል፡፡ ወደ ፍጹም የባሕሪይ ልዕልና ይደርሳል፤ ይረቃል፤ ወደ ቀጣዩ ቀን ሥርዓት ይሄዳል፡፡

እግዚአብሔር እንደዚህ አስቦ፥ አዳምም በታሰበለት ውስጥ እየሄደ ሳለ፤ የገነቱን ሥርዓት የሚረብሽ አንድ ድምፅ ወደ ሔዋን መጣ፡፡ መጥቶም የባሕሪይ ዕድገታችሁን ሳትጨርሱ እንዳትነኩት የተባሉትን የዛፍ ፍሬ ያለ ቀኑ እንዲነኩት አግባባቸው፡፡ በሴቲቱ አሳቦች መካከል አማራጭ የሚሆንን "ባዕድ አሳብ" ዲያቢሎስ አጫወተ፡፡ ተቀበለቺው፤ በላች፤ ለአዳምም ሰጠቺውና በላ፡፡ ከበሉም በኋላ፤ ከአትብሉ ሕግ የወጣው የሰው ልጅ ባሕሪይ ከአምላኩ ፈቃድ ተለይቶ መጓዝ በመጀመሩ፤ አዳምና ሔዋን ከዚህ በፊት ተስምቶአቸው የማይታወቅ ሌላ ስሜት ተሰማቸው፡፡ ፍርሃት፣ ባዶነትና ጭንቀት ውስጣቸውን አገኘው፡፡ የጸጋ ብርሃናቸውን አጡ፡፡

በመለኮት ቤት ውስጥ ብርሃን ብቻ ነው ያለው፡፡ ጨለማ የለም፡፡ ስለዚህ ከብርሃን ኃይል ጠፍተው የጨለሙት እነ አዳም ከእግዚአብሔር ጋር መገናኘት አልቻሉም፤ እርሱ ወዳለበት መሄድ አቃታቸው፡፡ ከላይ በተነሣንበት አንቀጽ ስናወራ፤ የሰው ልጅ ባሕሪይ አምላክ አስቦ ወዳዘጋጀለት ከፍታ ማደግ መቀጠል አልቻለም፡፡ እንኪያስ እኛ ወደርሱ "አሳብ" (አባት) መሄድ እንዳቃተን ሲያይ፤ እርሱ ወደኛ "በቃሉ" (በልጁ) መጣ፡፡ አዳምና ሔዋን ጠፍተው ወዳሉበት ቦታ ሰኮና ብእሲ (የሰው ኮቴ) እያሰማ መጣና "አዳምን ጠርቶ። ወዴት ነህ? አለው፡፡" (ኦሪት ዘፍጥረት 3፥9)

ተርጓሚዎች የእግዚአብሔር ቃል (ወልድ) "ወዴት ነህ?" ሲል መናገሩ አዳም ያለበት ጠፍቶት አልነበረም፤ "በኋላ ዘመን ሥጋን ተዋሕጄ አድንሃለው" ሲለው ነው ይላሉ፡፡ ይሄ ማለት "ወዴት ነህ" የምትለዋ የፍለጋ ጥሪ በአዳም ባሕሪይ ውስጥ የተጻፈች ረቂቅ ተስፋ ሆና ተቀምጣለች፡፡ በሆነ ጊዜ በሆነ ቦታ ላይ አዳም ከጠፋበት ስፍራ ላይ መጥቶ የሚያገኘው አንድ ኃይል እንዳለ እዛው በገነት ሳለ በውስጡ (በባሕሪዩ) አውቆታል፡፡

ባሕሪያችን ተስፋ እንደሰነቀ አልቀረም፡፡ ራሱን "የሰው ልጅ" እያለ የሚጠራ የእግዚአብሔር ልጅ "የጠፋውን ልፈልግ መጥቼያለሁ" ሲል በገነት የጠራን መለኮታዊ ቃል እርሱ እንደነበረ ተናገረ፡፡ (የማቴዎስ ወንጌል 18፥11) ወዴት ነህ ያለ ያ "ቃል ሥጋ ሆነና"፤ ሕልውናችን ጠፍቶ የነበረበትን ነጥብ አገኘው፡፡ ከአባቱ (ከአሳቡ) ተለይተን በመውጣታችን ምክንያት የመጡብንን ባዕድ ስሜቶች፣ ጠባያቶችና የክፉ መንፈስ እውቀቶች እያጠፋና የእርሱን እያስተማረ በመካከላችን ተመላለሰ፡፡ አገልግሎቱ ወደ ዋናው ክፍል ላይ የሚደርስበት ደረጃ ላይ ሲቃረብም በአይሁድ ምኩራብ ሳለ የሚከተለውን ተናገረ ፦

   "የላከኝ አብ ከሳበው በቀር ወደ እኔ ሊመጣ የሚችል የለም፥ እኔም በመጨረሻው ቀን አስነሣዋለሁ። ሁሉም ከእግዚአብሔር የተማሩ ይሆናሉ ተብሎ በነቢያት ተጽፎአል፤ እንግዲህ ከአብ የሰማ የተማረም ሁሉ ወደ እኔ ይመጣል። አብን ያየ ማንም የለም፤ ከእግዚአብሔር ከሆነ በቀር፥ እርሱ አብን አይቶአል። እውነት እውነት እላችኋለሁ በእኔ የሚያምን የዘላለም ሕይወት አለው፡፡ የሕይወት እንጀራ እኔ ነኝ፡፡ አባቶቻችሁ በምድረ በዳ መና በሉ ሞቱ፤ ሰው ከእርሱ በልቶ እንዳይሞት ከሰማይ አሁን የወረደ እንጀራ ይህ ነው። ከሰማይ የወረደ ሕያው እንጀራ እኔ ነኝ፤ ሰው ከዚህ እንጀራ ቢበላ ለዘላለም ይኖራል፤ እኔም ስለ ዓለም ሕይወት የምሰጠው እንጀራ ሥጋዬ ነው

                        (የዮሐንስ ወንጌል 6፥44-51)

ሺሕውን ዓመት በመጨረስ ወደ ሰባተኛው ቀን በመግባት፤ በነፍስና በሥጋችን ላይ የምትሠርፅ የሕይወት ዕፅን በልተን ከገነት ማኅፀን መወለድ ሲገባን፤ ነገር ግን ያለ ቀኑና ያለ ሥርዓቱ ከእውቀት ዛፍ በልተን ያለ ጊዜያችን ተወለድን፡፡ በተለመደው የመጽሐፍ አገላለጽ ከገነት ተባረርን፡፡ በእናቱ ማኅፀን ያለ ጽንስ እውቀትን ከውጪ መቀበል ከጀመረ ተወልዷል ማለት ነው፡፡ ያለ ጊዜው የተወለደ ልጅ ደግሞ ይሞታልና፤ በአካል ወደ አፈር፥ በባሕሪይ ከእግዚአብሔር አሳብ ወደ መለየት፥ በነፍስ አድራሻው ወደማይታወቅ ጨለማ መውረድ ጀመርን፡፡ ይሄ ወደታች የመውረድ ጉዞ ጠቅለል ባለ ቃል "ሞት" ይባላል፡፡

በመብል የተነሣ ሞት የሚባለው ውድቀት ወደ ተፈጥሮአችን መጣ፡፡ ከወደቅንበት ለመነሣት ብዙ ብንጥርም ሊሳካልን አልቻለም፡፡ አለመሞትን ብንፈልግም እንደምንፈልገው ግን አልሆነልንም፡፡ ውስጣችን ማደግ፣ መርቀቅና ከፍ ከፍ ማለትን ይመኛል፡፡ ሆኖም አካላችን ወደተፈጠረበት አፈር ይጓዛል፡፡ ከእርሱነቱ ተክፍላ በእኛ ውስጥ ያለች ነፍስ ወደ ፈጣሪ ፈቃድ መሄድን ትፈቅዳለች፤ ሥጋ ግን ወደ ራሱ ፈቃድ ያዘነብላል፡፡ በአጭሩ ከራሳችንም ከእግዚአብሔርም ተጣላን፡፡

ስለዚህ? እርቅ ያስፈልጋል፡፡ እርቁ እንዲኖር ደግሞ በመጀመሪያ ከጠፋንበት መገኘት ይኖርብናል፡፡ ስለዚህ የእግዚአብሔር ቃል ይፈልገን ዘንድ ተሰደን ወደሄድንበት ምድር ተከትሎን መጣ፡፡ ባገኘንም ጊዜ ከወገናችን እንደ አንዱ ሆነና በሥጋ ተዛመደን፡፡ ጉድለታችንን እየሞላ፣ ጥያቄያችንን እየመለሰ፣ መንገዳችንን እያቀና ውስጣችንን እየገነባ ቆየና፤ ወደኛ የመጣበትን ዋናውን ሥራ አከናወነልን፡፡ ከራቅነው እግዚአብሔር የምንቀርብበትን መንገድ ሰጠን፡፡ እንዴት?

ቁርባን በቁሙ የሱርስት (የሶርያ ቋንቋ) ቃል ነው፡፡ አምኃ ወይንም እጃ መንሻ ማለት ነው ትርጉሙ፡፡ በግእዙ ትርጉም ደግሞ መቀራረቢያ፣ መገናኛ ማለት ነው ይሉታል፡፡ ሦስተኛ በሚስጢር ትርጓሜው መሥዋዕት ማለት ነው፡፡

የመድኃኒቱ ክቡር ሥጋውና ቅዱስ ደሙ ቅዱስ ቁርባን በሚል ስያሜ ይጠራል፡፡ በላይኛው አንቀጽ በቃል ፍቺው እንዳየነው ቁርባን የተለያዩ የስም ትርጉሞች አሉት፡፡ እነዚህ ትርጉሞች በየራሳቸው ከጌታችን ሥጋና ደም ጋር ግንኙነት አላቸው፡፡ እስቲ እንመልከታቸው፡፡



tgoop.com/bemaledanek/2371
Create:
Last Update:

3•  ቅዱስ ቁርባን

     3.1•  ቅዱስ ቁርባን ምንድነው ?

ክፍል - ፩

          ✞ በልተን እንደወጣን በልተን እንመለሳለን

   "ለአዳም ሦስት ዕፅዋት ተሰጥተውት ነበር፤ አንዱን ሊጠብቀው፣ አንዱን ሊመገበው፣ አንዱን ሺሕ ዓመት ኖሮ ሊታደስበት፣ አትብላ ያለውን ዕፀ በለስ በበላ ጊዜ የሚታደስበት ዕፅ ተነሥቶታል፡፡ በሚታደስበት ዕፅ ሕይወትም ፈንታ ዛሬ ሥጋውና ደሙ ገብቶልናል፤ ሥጋውን ደሙን ተቀብለን፤ በልጅነት ታድሰን መንግሥተ ሰማያት የምንገባ ሆነናል፡፡"

                             (ኦሪት ዘልደት አንድምታ)


በአባት ዘንድ ታስበን ተፈጥረናል፡፡ የመጀመሪያው ሰው አዳም በእግዚአብሔር ልቦና ተጸንሶ፤ ሰው የተባለ ፍጥረት ሊሆን ሲወለድ፤ የባሕሪይ ዕድገቱን እንዲጨርስ ዔድን ገነት በተባለች ቦታ ገብቶአል፡፡ ማለት አዳም የተባለ እግዚአብሔር በፈቃዱ ጸንሶ ያስገኘው ልጅ፤ ገነት በተባለች ማኅፀን ውስጥ በባሕሪይ ያድግ ነበር፡፡

አዳም አካሉና ባሕሪዩ ከተፈጠረባት ጊዜ አንስቶ፤ እግዚአብሔር አስቀድሞ ወዳዘጋጀለት ከፍታ በባሕሪዩ ያድግ ነበር፡፡ ይሄ የዕድገት ቆይታ ደግሞ በገነት ሥርዓት አንድ ቀን ያህል ይፈጃል፡፡ በምድር (ከፀሐይ በታች ባለ ሥርዓት) ሲሆን አንድ ሺሕ ያህል ዓመት ይሆናል (2ኛ የጴጥሮስ መልእክት 3፥8)፡፡

አዳም በስድስተኛው ቀን አጋማሽ (አርብ 6:00) ላይ ተጸንሶ በመቀጠል ወደሚያድግበት ቦታ ወደ ገነት ገብቶአል፡፡ (ኦሪት ዘፍጥረት 2፥8) በገነትም አንዱን ቀን (ሺሕውን ዓመት) ቆይቶ ሲጨርስ ከዕፀ ሕይወት ዛፍ ይበላና ይታደሳል፡፡ በሌላ አነጋገር ሰባተኛው ቀን (ቅዳሜ) ሲገባ፤ አዳም ዕድገቱን ጨርሶ ሕያው በመሆን በእውቀትና በጥበብ ይወለዳል፡፡ ወደ ፍጹም የባሕሪይ ልዕልና ይደርሳል፤ ይረቃል፤ ወደ ቀጣዩ ቀን ሥርዓት ይሄዳል፡፡

እግዚአብሔር እንደዚህ አስቦ፥ አዳምም በታሰበለት ውስጥ እየሄደ ሳለ፤ የገነቱን ሥርዓት የሚረብሽ አንድ ድምፅ ወደ ሔዋን መጣ፡፡ መጥቶም የባሕሪይ ዕድገታችሁን ሳትጨርሱ እንዳትነኩት የተባሉትን የዛፍ ፍሬ ያለ ቀኑ እንዲነኩት አግባባቸው፡፡ በሴቲቱ አሳቦች መካከል አማራጭ የሚሆንን "ባዕድ አሳብ" ዲያቢሎስ አጫወተ፡፡ ተቀበለቺው፤ በላች፤ ለአዳምም ሰጠቺውና በላ፡፡ ከበሉም በኋላ፤ ከአትብሉ ሕግ የወጣው የሰው ልጅ ባሕሪይ ከአምላኩ ፈቃድ ተለይቶ መጓዝ በመጀመሩ፤ አዳምና ሔዋን ከዚህ በፊት ተስምቶአቸው የማይታወቅ ሌላ ስሜት ተሰማቸው፡፡ ፍርሃት፣ ባዶነትና ጭንቀት ውስጣቸውን አገኘው፡፡ የጸጋ ብርሃናቸውን አጡ፡፡

በመለኮት ቤት ውስጥ ብርሃን ብቻ ነው ያለው፡፡ ጨለማ የለም፡፡ ስለዚህ ከብርሃን ኃይል ጠፍተው የጨለሙት እነ አዳም ከእግዚአብሔር ጋር መገናኘት አልቻሉም፤ እርሱ ወዳለበት መሄድ አቃታቸው፡፡ ከላይ በተነሣንበት አንቀጽ ስናወራ፤ የሰው ልጅ ባሕሪይ አምላክ አስቦ ወዳዘጋጀለት ከፍታ ማደግ መቀጠል አልቻለም፡፡ እንኪያስ እኛ ወደርሱ "አሳብ" (አባት) መሄድ እንዳቃተን ሲያይ፤ እርሱ ወደኛ "በቃሉ" (በልጁ) መጣ፡፡ አዳምና ሔዋን ጠፍተው ወዳሉበት ቦታ ሰኮና ብእሲ (የሰው ኮቴ) እያሰማ መጣና "አዳምን ጠርቶ። ወዴት ነህ? አለው፡፡" (ኦሪት ዘፍጥረት 3፥9)

ተርጓሚዎች የእግዚአብሔር ቃል (ወልድ) "ወዴት ነህ?" ሲል መናገሩ አዳም ያለበት ጠፍቶት አልነበረም፤ "በኋላ ዘመን ሥጋን ተዋሕጄ አድንሃለው" ሲለው ነው ይላሉ፡፡ ይሄ ማለት "ወዴት ነህ" የምትለዋ የፍለጋ ጥሪ በአዳም ባሕሪይ ውስጥ የተጻፈች ረቂቅ ተስፋ ሆና ተቀምጣለች፡፡ በሆነ ጊዜ በሆነ ቦታ ላይ አዳም ከጠፋበት ስፍራ ላይ መጥቶ የሚያገኘው አንድ ኃይል እንዳለ እዛው በገነት ሳለ በውስጡ (በባሕሪዩ) አውቆታል፡፡

ባሕሪያችን ተስፋ እንደሰነቀ አልቀረም፡፡ ራሱን "የሰው ልጅ" እያለ የሚጠራ የእግዚአብሔር ልጅ "የጠፋውን ልፈልግ መጥቼያለሁ" ሲል በገነት የጠራን መለኮታዊ ቃል እርሱ እንደነበረ ተናገረ፡፡ (የማቴዎስ ወንጌል 18፥11) ወዴት ነህ ያለ ያ "ቃል ሥጋ ሆነና"፤ ሕልውናችን ጠፍቶ የነበረበትን ነጥብ አገኘው፡፡ ከአባቱ (ከአሳቡ) ተለይተን በመውጣታችን ምክንያት የመጡብንን ባዕድ ስሜቶች፣ ጠባያቶችና የክፉ መንፈስ እውቀቶች እያጠፋና የእርሱን እያስተማረ በመካከላችን ተመላለሰ፡፡ አገልግሎቱ ወደ ዋናው ክፍል ላይ የሚደርስበት ደረጃ ላይ ሲቃረብም በአይሁድ ምኩራብ ሳለ የሚከተለውን ተናገረ ፦

   "የላከኝ አብ ከሳበው በቀር ወደ እኔ ሊመጣ የሚችል የለም፥ እኔም በመጨረሻው ቀን አስነሣዋለሁ። ሁሉም ከእግዚአብሔር የተማሩ ይሆናሉ ተብሎ በነቢያት ተጽፎአል፤ እንግዲህ ከአብ የሰማ የተማረም ሁሉ ወደ እኔ ይመጣል። አብን ያየ ማንም የለም፤ ከእግዚአብሔር ከሆነ በቀር፥ እርሱ አብን አይቶአል። እውነት እውነት እላችኋለሁ በእኔ የሚያምን የዘላለም ሕይወት አለው፡፡ የሕይወት እንጀራ እኔ ነኝ፡፡ አባቶቻችሁ በምድረ በዳ መና በሉ ሞቱ፤ ሰው ከእርሱ በልቶ እንዳይሞት ከሰማይ አሁን የወረደ እንጀራ ይህ ነው። ከሰማይ የወረደ ሕያው እንጀራ እኔ ነኝ፤ ሰው ከዚህ እንጀራ ቢበላ ለዘላለም ይኖራል፤ እኔም ስለ ዓለም ሕይወት የምሰጠው እንጀራ ሥጋዬ ነው

                        (የዮሐንስ ወንጌል 6፥44-51)

ሺሕውን ዓመት በመጨረስ ወደ ሰባተኛው ቀን በመግባት፤ በነፍስና በሥጋችን ላይ የምትሠርፅ የሕይወት ዕፅን በልተን ከገነት ማኅፀን መወለድ ሲገባን፤ ነገር ግን ያለ ቀኑና ያለ ሥርዓቱ ከእውቀት ዛፍ በልተን ያለ ጊዜያችን ተወለድን፡፡ በተለመደው የመጽሐፍ አገላለጽ ከገነት ተባረርን፡፡ በእናቱ ማኅፀን ያለ ጽንስ እውቀትን ከውጪ መቀበል ከጀመረ ተወልዷል ማለት ነው፡፡ ያለ ጊዜው የተወለደ ልጅ ደግሞ ይሞታልና፤ በአካል ወደ አፈር፥ በባሕሪይ ከእግዚአብሔር አሳብ ወደ መለየት፥ በነፍስ አድራሻው ወደማይታወቅ ጨለማ መውረድ ጀመርን፡፡ ይሄ ወደታች የመውረድ ጉዞ ጠቅለል ባለ ቃል "ሞት" ይባላል፡፡

በመብል የተነሣ ሞት የሚባለው ውድቀት ወደ ተፈጥሮአችን መጣ፡፡ ከወደቅንበት ለመነሣት ብዙ ብንጥርም ሊሳካልን አልቻለም፡፡ አለመሞትን ብንፈልግም እንደምንፈልገው ግን አልሆነልንም፡፡ ውስጣችን ማደግ፣ መርቀቅና ከፍ ከፍ ማለትን ይመኛል፡፡ ሆኖም አካላችን ወደተፈጠረበት አፈር ይጓዛል፡፡ ከእርሱነቱ ተክፍላ በእኛ ውስጥ ያለች ነፍስ ወደ ፈጣሪ ፈቃድ መሄድን ትፈቅዳለች፤ ሥጋ ግን ወደ ራሱ ፈቃድ ያዘነብላል፡፡ በአጭሩ ከራሳችንም ከእግዚአብሔርም ተጣላን፡፡

ስለዚህ? እርቅ ያስፈልጋል፡፡ እርቁ እንዲኖር ደግሞ በመጀመሪያ ከጠፋንበት መገኘት ይኖርብናል፡፡ ስለዚህ የእግዚአብሔር ቃል ይፈልገን ዘንድ ተሰደን ወደሄድንበት ምድር ተከትሎን መጣ፡፡ ባገኘንም ጊዜ ከወገናችን እንደ አንዱ ሆነና በሥጋ ተዛመደን፡፡ ጉድለታችንን እየሞላ፣ ጥያቄያችንን እየመለሰ፣ መንገዳችንን እያቀና ውስጣችንን እየገነባ ቆየና፤ ወደኛ የመጣበትን ዋናውን ሥራ አከናወነልን፡፡ ከራቅነው እግዚአብሔር የምንቀርብበትን መንገድ ሰጠን፡፡ እንዴት?

ቁርባን በቁሙ የሱርስት (የሶርያ ቋንቋ) ቃል ነው፡፡ አምኃ ወይንም እጃ መንሻ ማለት ነው ትርጉሙ፡፡ በግእዙ ትርጉም ደግሞ መቀራረቢያ፣ መገናኛ ማለት ነው ይሉታል፡፡ ሦስተኛ በሚስጢር ትርጓሜው መሥዋዕት ማለት ነው፡፡

የመድኃኒቱ ክቡር ሥጋውና ቅዱስ ደሙ ቅዱስ ቁርባን በሚል ስያሜ ይጠራል፡፡ በላይኛው አንቀጽ በቃል ፍቺው እንዳየነው ቁርባን የተለያዩ የስም ትርጉሞች አሉት፡፡ እነዚህ ትርጉሞች በየራሳቸው ከጌታችን ሥጋና ደም ጋር ግንኙነት አላቸው፡፡ እስቲ እንመልከታቸው፡፡

BY በማለዳ ንቁ ቁጥር ! ፪


Share with your friend now:
tgoop.com/bemaledanek/2371

View MORE
Open in Telegram


Telegram News

Date: |

A Hong Kong protester with a petrol bomb. File photo: Dylan Hollingsworth/HKFP. As the broader market downturn continues, yelling online has become the crypto trader’s latest coping mechanism after the rise of Goblintown Ethereum NFTs at the end of May and beginning of June, where holders made incoherent groaning sounds and role-played as urine-loving goblin creatures in late-night Twitter Spaces. End-to-end encryption is an important feature in messaging, as it's the first step in protecting users from surveillance. As five out of seven counts were serious, Hui sentenced Ng to six years and six months in jail. Unlimited number of subscribers per channel
from us


Telegram በማለዳ ንቁ ቁጥር ! ፪
FROM American