BEMALEDANEK Telegram 2377
በማለዳ ንቁ ቁጥር ! ፪
3•  ቅዱስ ቁርባን      3.1•  ቅዱስ ቁርባን ምንድነው ? ክፍል - ፩           ✞ በልተን እንደወጣን በልተን እንመለሳለን ✞    "ለአዳም ሦስት ዕፅዋት ተሰጥተውት ነበር፤ አንዱን ሊጠብቀው፣ አንዱን ሊመገበው፣ አንዱን ሺሕ ዓመት ኖሮ ሊታደስበት፣ አትብላ ያለውን ዕፀ በለስ በበላ ጊዜ የሚታደስበት ዕፅ ተነሥቶታል፡፡ በሚታደስበት ዕፅ ሕይወትም ፈንታ ዛሬ ሥጋውና ደሙ ገብቶልናል፤ ሥጋውን…
3•  ቅዱስ ቁርባን

ክፍል - ፪

      3.2•  ቅዱስ ቁርባን ለምን እንውሰድ ?

           3.2.1•  በእግዚአብሔር በኩል

               ✞ ፫ተኛው ቤተ መቅደስ (ትንሣኤ)

   "ኢየሱስም መልሶ። ይህን ቤተ መቅደስ አፍርሱት፥ በሦስት ቀንም አነሣዋለሁ አላቸው። ስለዚህ አይሁድ። ይህ ቤተ መቅደስ ከአርባ ስድስት ዓመት ጀምሮ ይሠራ ነበር፥ አንተስ በሦስት ቀን ታነሣዋለህን? አሉት። እርሱ ግን ስለ ሰውነቱ ቤተ መቅደስ ይል ነበር።"

                                            (የዮሐንስ ወንጌል 2፥21)

አዳም ባሕሪያችን የተሠራበት "የሰውነት" መዝገብ ነው፡፡ (፲፮፤ በደመወዝ ጎሽሜ) ወይም አዳም ማለት ሰብአዊ ማንነትን የሚወክል አንድ ታላቅ ወንዝ ነው እንበለው፡፡ ከዚህ ወንዝ ውስጥ ሁላችን የሰው ልጆች ተገኝተናል፡፡ ስለዚህ ስለ አዳም ባሕሪይ ስናወጋ ስለ አንድ ዘፍጥረት ላይ ታሪኩ ስለሚዘከርለት ሰው ብቻ ሳይሆን ስለራሳችን ባሕሪይም ጭምር ነው የምናወሳው ማለት ነው፡፡

ይሄ አዳም የተባለ ሰው የተፈጠረው በእግዚአብሔር ልዩ ፈቃድ ነው፡፡ በመውለድ አንቀጽ ስናወራ አዳም የተወለደው ከእግዚአብሔር የፈቃድ ማኅፀን ነው፡፡ ይሄ በእግዚአብሔር ታስቦ የተገኘ ፍጡር "ቤተ መቅደስ" ተብሎም ይጠራል፡፡ (1ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 3፥16) እነሆ የአምላክ ቤተ መቅደስ ሙሉ በሙሉ ተሠርቶ በሚፈጸምበት በገነት እየታነጸ ሳለ፤ ከወላጁ ከእግዚአብሔር የሚለየው የዲያቢሎስን ፈቃድ በመፍቀዱ ምክንያት ቤተ መቅደሱ ሳይጠናቀቅ (እግዚአብሔር ያሰበው ሳይሆን) ፈረሰ፡፡ "ከአፈር ተሠርተሃልና ወደ አፈር ተመለስ" የሚል የመፍረስን ትእዛዝ በባሕሪዩ አደመጠ፡፡

አዳም የሚባለው ሰው ሞትን አወቀ የሚለውን አነጋገር በቤተ መቅደስ በኩል ብንደግመው ፈረሰ የሚለው ቃል ነው የሚስማማው፡፡ መፍረስ የሚለውን ቃል በአቻ ፍቺዎች ሲበየን፤ መበታተን፣ መበስበስ፣ ወደ ታች መመለስ ልንለው እንችላለን፡፡ በጥንት የዕብራውያን የሃይማኖት ትምህርት አጥኚዎች ዘንድ "ሞት" የሚለውን ቃል ሲተነትኑ፤ በውኃና በአፈር ውህዶች መካከል የሚከሰት የመበስበስ ሂደት ሲሉ ይተረጉሙታል፡፡ (አባዶን፤ መልአከ መንክራት ግርማ ወንድሙ)

የፈረሰው ቤተ መቅደስ የተገነባው በስድስት ቀናት ውስጥ ነው፡፡ እያንዳንዱ የዘፍጥረት ቀናት (ከእሁድ እስከ አርብ ያሉት) አዳምን ለማስገኘት የፍጡርን ባሕሪይ ያዋጡ ነበር፡፡ በሌላ አገላለጽ ሰው ማለት የስድስቱ ቀን ፍጡራን ባሕሪያት መጥቅሊያና መካተቻ የሆነ ፍጡር ነው /ሰው የተፈጠረው በዕለተ አርብ ነው፤ አርብ ደግሞ ማለት ማካተቻ፤ መደምደሚያ ማለት ነው/፡፡ እግዚአብሔር አዳምን ከፈጠረ በኋላ አርፏል፡፡ ወይንም ሌላ መፍጠሩን አቁሟል፡፡ በመሆኑ በዚህ መሠረት ከተናገርን፤ የሰው ልጅ የአምላክ ማረፊያ ቤተ መቅደስ ነው መባሉ ልክ ይሆናል፡፡

ሞት ወደ አዳም ባሕሪይ ከመጣ በኋላ ግን፤ በስድስቱ ቀናት "ድምርነት" የተሠራው ሰው ወደኋላ (ወደ መጀመሪያው) ቀን መልሶ ፈርሷል፡፡ "ወደ አፈር ተመለስ" የሚል ትእዛዝ የተሰጠው የሰው ልጅ፤ ከስድስተኛው ቀን (የአርብ) የፍጡር ሥርዓት "ሰውነት" እየፈረሰ ሄዶ ወደ አንደኛው ቀን (የእሁድ) የፍጡር ሥርዓት "አፈርነት" ይመለሳል፡፡ በአጭሩ፤ አዳም የተከለከለውን ካደረገ በኋላ፤ በውስጡ ተሰብስበው ሰው ያሰኙት የስድስቱ ቀን ፍጡራን ባሕሪያት ተጣሉበት፡፡ ፍጥረት ሁሉ በባሕሪይ አዳምን ለማስገኘት ወደፊት በሚቆጥሩ ቀናት እየተሰበሰቡ እንዲሄዱ ተሠርተው ሳለ፤ አዳም ግን ከዚህ ሕግ ተፋልሶ ወጥቶ የዛፉን ፍሬ ከበላ በኋላ "ወደ አፈር ተመለስ" ስለተባለ፤ ከፍጡራን ባሕሪይ በተቃራኒ እየተጓዘ ወደ አንደኛው ቀን በመመለስ፤ ከራሱም ከተፈጥሮም ጋር ጸብ ጀምሯል፡፡ /የዛፉን ፍሬ ከወሰድን በኋላ ከቀን ስድስት ወደ ቀን አንድ በባሕሪይ በመውደቅ መጥተናል እያልን ነው/ የሰው ልጅ ከገነቱ ስህተት አስከትሎ ጉስቅልና ያገኘው ለዚህ ነው፡፡ ማለት አዳም ከእግዚአብሔር ተለይቶ ሲወጣ፤ ውስጡ ካሉት የፍጥረታት ባሕሪይ ጋር ቀውስ ጀምሯልና፤ ይህ የውስጥ የባሕሪያት ተቃርኖ ወደ ውጪ ወጥቶ ሲገለጽ፤ ፀሐይ ታተኩሰው፣ ዝናብ ይቀጠቅጠው፣ እሳት ያቃጥለው፣ ውኃ ይጠማው፣ ርሃብ ይይዘው፣ በሽታ ያገኘው፣ ድካም ይሰማው፣ ጉንዳን ይቆነጥጠው፣ ጊንጥ ይነድፈው፣ አራዊት ያሳድዱት፣ ወዘተ... ጀመር፡፡

እግዚአብሔር አዳም የተባለን ቤተ መቅደስ ከፍጡራን ባሕሪያት ሰብስቦ በመጀመሪያ ሲሠራው እንዲፈርስ አስቦ አልነበረም፡፡ ይልቅ አስቀድሞ አስቦ ያዘጋጀለት (መልካም እንደሆነ ያየለት) የከፍታ ሥርዓት አለ፡፡ ይሄ መለኮታዊ አሳብ በራሱ "ሕያው" ከመሆኑ የተነሳ ከመፈጸም አይቀርምና፤ አሳቡ እንዲሳካ ከፈቃዱ ውጥቶ የፈረሰው አዳም እንደገና በፈቃዱ መሠራት አለበት፡፡ ደግሞም ቀድሞውኑም የሠራን እርሱ ስለሆነ፤ ከፈረስንበትም ቦታ ላይ አንስቶ እንደገና ሊገነባን የሚችለው እርሱ ብቻ ነው፡፡ "እንደገና" የምንገነባ ከሆነ ደግሞ፤ "መጀመሪያ የተሠራንበት መንፈሳዊ አካሄድ መደገም" ይኖርበታል፡፡ ማለትም በኦሪት መግቢያ ላይ ተዘርዝረው ያሉት ስድስቱ ቀናት ዳግም ተሰብስበው የፈረሰውን ማንነታችንን መልሰው ሊገነቡት ይገባል፡፡ በመሆኑም እግዚአብሔር ባሕሪያችንን አስቀድሞ ላየው ልዕልና ለማብቃት "እንደገና ስድስቱን ቀናት እየጠራ ይሠራን ጀመር"፡፡

እንደገና ይሠራናል ሲባል፤ አንድ መገንዘብ ያለብን ወሳኝ ጉዳይ አለ፡፡ መጀመሪያ ስንሠራ በስድስቱ የዘልደት ቀናት ስብስብነት እንደነበር ከላይ ጠቅሰናል፡፡ እነዚያ ቀናት ደግሞ በእግዚአብሔር ጊዜ የተሰሉ "ሰማያዊ ቀኖች" ናቸው፡፡ ከመነሻ እስከ መድረሻ የሚዘልቀው የፍጥረታት "ባሕሪይ" የተቀረጸባቸው ረቂቅ ሥርዓቶች ናቸው፡፡

ለሁለተኛ ጊዜ እንደገና በነዚህ ስድስት ቀናት ውጤትነት የምንሠራበት ሂደት ከቀን አንድ /ከዛፉ በልተን ወደ ቀን አንድ እንደተመለስን ያስታውሷል/ ጀምሮ ሲደገም፤ ዳግም የመሥራት ሂደቱ ስፍራ እንደለወጠ ማስተዋል ይገባናል፡፡ ማለትም እኛ መጀመሪያ ከተሠራንበት የእግዚአብሔር ሥርዓት ተለይተን ወጥተን ወደ ምድር ወርደናል (ቦታ ቀየረናል)፡፡ ስለዚህ መጀመሪያ የተሠራንባቸው እነዚያ ስድስቱ ሰማያዊ ቀናት ድጋሚ ይሠሩን ዘንድ ሲሰበሰቡ፤ አቆጣጠራቸው ተሰደን በመጣንበት በምድር ሥርዓት በኩል የሚሰላ ይሆናል (በቀየረነው ቦታ መሠረት ማለት ነው)፡፡ በደንብ ለማብራራት፤ በገነት ሳለን የጊዜ ልኬት የሚለካው በእግዚአብሔር በኩል ባለ ስሌት ነበር፡፡ ወደ ምድር ከመጣን በኋላ ግን ጊዜያት የሚሰፈሩት በመውጣት በመግባታቸው ምክንያት ዘመናትን እንዲያስታውቁን በተሰጡን የሦስተኛው ቀን ፍጥረታት (ፀሐይ፣ ጨረቃ፣ ከዋክብት) በኩል ነው፡፡ በመሆኑም ተከትሎን ወደ ምድር የመጣው እግዚአብሔር ስድስቱን ቀናት እየሰበሰበ ዳግም ሲሠራን በሰውኛ አቆጣጠር እየለካ ይሆናል፡፡ በእግዚአብሔር (በገነት ሳለን) የነበረው አንድ ቀን፤ በእኛ (በምድር ሆነን) አንድ ሺሕ ያህል ዓመት ይሆናልና፤ ወደኋላ (ወደ አፈርነት) በመመለስ የፈረስንባቸው ስድስቱ ሰማያዊ ቀናት ወደፊት እንደገና እኛን ለመመለስ በምድር ሲሰበሰቡ ስድስት ሺሕ ያህል ዓመታት ይቆጥራሉ፡፡



tgoop.com/bemaledanek/2377
Create:
Last Update:

3•  ቅዱስ ቁርባን

ክፍል - ፪

      3.2•  ቅዱስ ቁርባን ለምን እንውሰድ ?

           3.2.1•  በእግዚአብሔር በኩል

               ✞ ፫ተኛው ቤተ መቅደስ (ትንሣኤ)

   "ኢየሱስም መልሶ። ይህን ቤተ መቅደስ አፍርሱት፥ በሦስት ቀንም አነሣዋለሁ አላቸው። ስለዚህ አይሁድ። ይህ ቤተ መቅደስ ከአርባ ስድስት ዓመት ጀምሮ ይሠራ ነበር፥ አንተስ በሦስት ቀን ታነሣዋለህን? አሉት። እርሱ ግን ስለ ሰውነቱ ቤተ መቅደስ ይል ነበር።"

                                            (የዮሐንስ ወንጌል 2፥21)

አዳም ባሕሪያችን የተሠራበት "የሰውነት" መዝገብ ነው፡፡ (፲፮፤ በደመወዝ ጎሽሜ) ወይም አዳም ማለት ሰብአዊ ማንነትን የሚወክል አንድ ታላቅ ወንዝ ነው እንበለው፡፡ ከዚህ ወንዝ ውስጥ ሁላችን የሰው ልጆች ተገኝተናል፡፡ ስለዚህ ስለ አዳም ባሕሪይ ስናወጋ ስለ አንድ ዘፍጥረት ላይ ታሪኩ ስለሚዘከርለት ሰው ብቻ ሳይሆን ስለራሳችን ባሕሪይም ጭምር ነው የምናወሳው ማለት ነው፡፡

ይሄ አዳም የተባለ ሰው የተፈጠረው በእግዚአብሔር ልዩ ፈቃድ ነው፡፡ በመውለድ አንቀጽ ስናወራ አዳም የተወለደው ከእግዚአብሔር የፈቃድ ማኅፀን ነው፡፡ ይሄ በእግዚአብሔር ታስቦ የተገኘ ፍጡር "ቤተ መቅደስ" ተብሎም ይጠራል፡፡ (1ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 3፥16) እነሆ የአምላክ ቤተ መቅደስ ሙሉ በሙሉ ተሠርቶ በሚፈጸምበት በገነት እየታነጸ ሳለ፤ ከወላጁ ከእግዚአብሔር የሚለየው የዲያቢሎስን ፈቃድ በመፍቀዱ ምክንያት ቤተ መቅደሱ ሳይጠናቀቅ (እግዚአብሔር ያሰበው ሳይሆን) ፈረሰ፡፡ "ከአፈር ተሠርተሃልና ወደ አፈር ተመለስ" የሚል የመፍረስን ትእዛዝ በባሕሪዩ አደመጠ፡፡

አዳም የሚባለው ሰው ሞትን አወቀ የሚለውን አነጋገር በቤተ መቅደስ በኩል ብንደግመው ፈረሰ የሚለው ቃል ነው የሚስማማው፡፡ መፍረስ የሚለውን ቃል በአቻ ፍቺዎች ሲበየን፤ መበታተን፣ መበስበስ፣ ወደ ታች መመለስ ልንለው እንችላለን፡፡ በጥንት የዕብራውያን የሃይማኖት ትምህርት አጥኚዎች ዘንድ "ሞት" የሚለውን ቃል ሲተነትኑ፤ በውኃና በአፈር ውህዶች መካከል የሚከሰት የመበስበስ ሂደት ሲሉ ይተረጉሙታል፡፡ (አባዶን፤ መልአከ መንክራት ግርማ ወንድሙ)

የፈረሰው ቤተ መቅደስ የተገነባው በስድስት ቀናት ውስጥ ነው፡፡ እያንዳንዱ የዘፍጥረት ቀናት (ከእሁድ እስከ አርብ ያሉት) አዳምን ለማስገኘት የፍጡርን ባሕሪይ ያዋጡ ነበር፡፡ በሌላ አገላለጽ ሰው ማለት የስድስቱ ቀን ፍጡራን ባሕሪያት መጥቅሊያና መካተቻ የሆነ ፍጡር ነው /ሰው የተፈጠረው በዕለተ አርብ ነው፤ አርብ ደግሞ ማለት ማካተቻ፤ መደምደሚያ ማለት ነው/፡፡ እግዚአብሔር አዳምን ከፈጠረ በኋላ አርፏል፡፡ ወይንም ሌላ መፍጠሩን አቁሟል፡፡ በመሆኑ በዚህ መሠረት ከተናገርን፤ የሰው ልጅ የአምላክ ማረፊያ ቤተ መቅደስ ነው መባሉ ልክ ይሆናል፡፡

ሞት ወደ አዳም ባሕሪይ ከመጣ በኋላ ግን፤ በስድስቱ ቀናት "ድምርነት" የተሠራው ሰው ወደኋላ (ወደ መጀመሪያው) ቀን መልሶ ፈርሷል፡፡ "ወደ አፈር ተመለስ" የሚል ትእዛዝ የተሰጠው የሰው ልጅ፤ ከስድስተኛው ቀን (የአርብ) የፍጡር ሥርዓት "ሰውነት" እየፈረሰ ሄዶ ወደ አንደኛው ቀን (የእሁድ) የፍጡር ሥርዓት "አፈርነት" ይመለሳል፡፡ በአጭሩ፤ አዳም የተከለከለውን ካደረገ በኋላ፤ በውስጡ ተሰብስበው ሰው ያሰኙት የስድስቱ ቀን ፍጡራን ባሕሪያት ተጣሉበት፡፡ ፍጥረት ሁሉ በባሕሪይ አዳምን ለማስገኘት ወደፊት በሚቆጥሩ ቀናት እየተሰበሰቡ እንዲሄዱ ተሠርተው ሳለ፤ አዳም ግን ከዚህ ሕግ ተፋልሶ ወጥቶ የዛፉን ፍሬ ከበላ በኋላ "ወደ አፈር ተመለስ" ስለተባለ፤ ከፍጡራን ባሕሪይ በተቃራኒ እየተጓዘ ወደ አንደኛው ቀን በመመለስ፤ ከራሱም ከተፈጥሮም ጋር ጸብ ጀምሯል፡፡ /የዛፉን ፍሬ ከወሰድን በኋላ ከቀን ስድስት ወደ ቀን አንድ በባሕሪይ በመውደቅ መጥተናል እያልን ነው/ የሰው ልጅ ከገነቱ ስህተት አስከትሎ ጉስቅልና ያገኘው ለዚህ ነው፡፡ ማለት አዳም ከእግዚአብሔር ተለይቶ ሲወጣ፤ ውስጡ ካሉት የፍጥረታት ባሕሪይ ጋር ቀውስ ጀምሯልና፤ ይህ የውስጥ የባሕሪያት ተቃርኖ ወደ ውጪ ወጥቶ ሲገለጽ፤ ፀሐይ ታተኩሰው፣ ዝናብ ይቀጠቅጠው፣ እሳት ያቃጥለው፣ ውኃ ይጠማው፣ ርሃብ ይይዘው፣ በሽታ ያገኘው፣ ድካም ይሰማው፣ ጉንዳን ይቆነጥጠው፣ ጊንጥ ይነድፈው፣ አራዊት ያሳድዱት፣ ወዘተ... ጀመር፡፡

እግዚአብሔር አዳም የተባለን ቤተ መቅደስ ከፍጡራን ባሕሪያት ሰብስቦ በመጀመሪያ ሲሠራው እንዲፈርስ አስቦ አልነበረም፡፡ ይልቅ አስቀድሞ አስቦ ያዘጋጀለት (መልካም እንደሆነ ያየለት) የከፍታ ሥርዓት አለ፡፡ ይሄ መለኮታዊ አሳብ በራሱ "ሕያው" ከመሆኑ የተነሳ ከመፈጸም አይቀርምና፤ አሳቡ እንዲሳካ ከፈቃዱ ውጥቶ የፈረሰው አዳም እንደገና በፈቃዱ መሠራት አለበት፡፡ ደግሞም ቀድሞውኑም የሠራን እርሱ ስለሆነ፤ ከፈረስንበትም ቦታ ላይ አንስቶ እንደገና ሊገነባን የሚችለው እርሱ ብቻ ነው፡፡ "እንደገና" የምንገነባ ከሆነ ደግሞ፤ "መጀመሪያ የተሠራንበት መንፈሳዊ አካሄድ መደገም" ይኖርበታል፡፡ ማለትም በኦሪት መግቢያ ላይ ተዘርዝረው ያሉት ስድስቱ ቀናት ዳግም ተሰብስበው የፈረሰውን ማንነታችንን መልሰው ሊገነቡት ይገባል፡፡ በመሆኑም እግዚአብሔር ባሕሪያችንን አስቀድሞ ላየው ልዕልና ለማብቃት "እንደገና ስድስቱን ቀናት እየጠራ ይሠራን ጀመር"፡፡

እንደገና ይሠራናል ሲባል፤ አንድ መገንዘብ ያለብን ወሳኝ ጉዳይ አለ፡፡ መጀመሪያ ስንሠራ በስድስቱ የዘልደት ቀናት ስብስብነት እንደነበር ከላይ ጠቅሰናል፡፡ እነዚያ ቀናት ደግሞ በእግዚአብሔር ጊዜ የተሰሉ "ሰማያዊ ቀኖች" ናቸው፡፡ ከመነሻ እስከ መድረሻ የሚዘልቀው የፍጥረታት "ባሕሪይ" የተቀረጸባቸው ረቂቅ ሥርዓቶች ናቸው፡፡

ለሁለተኛ ጊዜ እንደገና በነዚህ ስድስት ቀናት ውጤትነት የምንሠራበት ሂደት ከቀን አንድ /ከዛፉ በልተን ወደ ቀን አንድ እንደተመለስን ያስታውሷል/ ጀምሮ ሲደገም፤ ዳግም የመሥራት ሂደቱ ስፍራ እንደለወጠ ማስተዋል ይገባናል፡፡ ማለትም እኛ መጀመሪያ ከተሠራንበት የእግዚአብሔር ሥርዓት ተለይተን ወጥተን ወደ ምድር ወርደናል (ቦታ ቀየረናል)፡፡ ስለዚህ መጀመሪያ የተሠራንባቸው እነዚያ ስድስቱ ሰማያዊ ቀናት ድጋሚ ይሠሩን ዘንድ ሲሰበሰቡ፤ አቆጣጠራቸው ተሰደን በመጣንበት በምድር ሥርዓት በኩል የሚሰላ ይሆናል (በቀየረነው ቦታ መሠረት ማለት ነው)፡፡ በደንብ ለማብራራት፤ በገነት ሳለን የጊዜ ልኬት የሚለካው በእግዚአብሔር በኩል ባለ ስሌት ነበር፡፡ ወደ ምድር ከመጣን በኋላ ግን ጊዜያት የሚሰፈሩት በመውጣት በመግባታቸው ምክንያት ዘመናትን እንዲያስታውቁን በተሰጡን የሦስተኛው ቀን ፍጥረታት (ፀሐይ፣ ጨረቃ፣ ከዋክብት) በኩል ነው፡፡ በመሆኑም ተከትሎን ወደ ምድር የመጣው እግዚአብሔር ስድስቱን ቀናት እየሰበሰበ ዳግም ሲሠራን በሰውኛ አቆጣጠር እየለካ ይሆናል፡፡ በእግዚአብሔር (በገነት ሳለን) የነበረው አንድ ቀን፤ በእኛ (በምድር ሆነን) አንድ ሺሕ ያህል ዓመት ይሆናልና፤ ወደኋላ (ወደ አፈርነት) በመመለስ የፈረስንባቸው ስድስቱ ሰማያዊ ቀናት ወደፊት እንደገና እኛን ለመመለስ በምድር ሲሰበሰቡ ስድስት ሺሕ ያህል ዓመታት ይቆጥራሉ፡፡

BY በማለዳ ንቁ ቁጥር ! ፪


Share with your friend now:
tgoop.com/bemaledanek/2377

View MORE
Open in Telegram


Telegram News

Date: |

While some crypto traders move toward screaming as a coping mechanism, many mental health experts have argued that “scream therapy” is pseudoscience. Scientific research or no, it obviously feels good. But a Telegram statement also said: "Any requests related to political censorship or limiting human rights such as the rights to free speech or assembly are not and will not be considered." Add up to 50 administrators Deputy District Judge Peter Hui sentenced computer technician Ng Man-ho on Thursday, a month after the 27-year-old, who ran a Telegram group called SUCK Channel, was found guilty of seven charges of conspiring to incite others to commit illegal acts during the 2019 extradition bill protests and subsequent months. The public channel had more than 109,000 subscribers, Judge Hui said. Ng had the power to remove or amend the messages in the channel, but he “allowed them to exist.”
from us


Telegram በማለዳ ንቁ ቁጥር ! ፪
FROM American