BEMALEDANEK Telegram 2378
አንጓ ክስተቶችን እየመዘዙ ከመተረክ አንጻር፤ ይሄ "ዳግም" የመገንባት ሥራው "አብራምን ለይቶ በመጥራት" ጀመረ እንበል፡፡ (ኦሪት ዘፍጥረት 12፥1) እንደሚታወቀው አዳም የወደቀው በሴት ፈቃድ አማካኝነት ነው፡፡ ወይንም ወደ ምድር እንዲወርድ ምክንያት የሆነቺው ሔዋን ናት፡፡ ስለዚህ ወደዚህ ዓለም በሴት በኩል እየተወለድን እንመጣለን፡፡ (ዝኒ ከማሁ) እንኪያስ ቤተ መቅደሱ እንደገና መገንባት አለበት ስንል፤ አያይዘን ለመፍረሱ ምክንያት የሆነቺው ሔዋንም "እንደገና" መቀረጽ ይገባታል እያልን ነው፡፡ ("እንደገና" እየሠራን ነው ካልን፤ የመጀመሪያው የተፈጠርንበት የሰማዩ ሥርዓት በምድር ራሱው እየተደገመ እንደሚሄድ ልብ እንበል!)

እናም ለመፍረስ የሆነቺው ምክንያት፥ ለመገንባትም ምክንያት ትሆን ዘንድ፤ ይህቺ [አዲሲቱ] ምክንያት በአብራም ባሕሪይ ውስጥ መሠራት ጀመረች፡፡ በገነቱ ሥርዓት አዳምን አስተኝቶ ሔዋንን ከጎኑ በወጣች አጥንት እንደሠራት፤ በመሬቱም ሥርዓት ሌላውን ሕዝብ አስተኝቶ አብራምን ለይቶ እንደ አጥንት በማውጣት ይሠራ ጀመረ፡፡ ማለትም ሴቲቱ (ሔዋን) በአብራም ተለይቶ የመውጣት አጥንትነት እንደገና መሠራት ጀመረች፡፡ በገነቱ የአፈጣጠር ሥርዓት ስናወራ፤ አብራም ማለት ከአዳም ጎን የወጣው ሔዋን የተሠራችበት አጥንት ነው ማለት ነው፡፡

የብሉይ ዘመን የምንላቸው ስድስት ሺሕው ዓመታት (ስድስቱ ቀናት) ወንዱን ልጅ (አዳምን) ዳግም ለመውለድ ያማጡ ዓመታት ናቸው፡፡ በአብርሃም ተለይቶ የመውጣት የቃልኪዳን ትውልድነት ስትገነባ የቆየቺው ሴቲቱም፤ በምጥ ዘመኑ መድረሻ ላይ በተጨባጭ ተገልጣ ትታያለች፤ ድንግል ማርያም ሆና!

ከአዳም አስጀምረን እያየን የመጣነውን እውነታ፤ በሉቃስ ጽሕፈት (የሉቃስ ወንጌል 1፥28-35) ላይ በተቀመጠው፤ በገብርኤል ሰላምታ ውስጥ በአንኳር አገላለጽ ተጠቅልሎ እናገኘዋለን፡፡ መልአኩ ንግግሩን ሲጀምር "ደስ ይበልሽ፥ ጸጋ የሞላብሽ ሆይ፥ ጌታ ከአንቺ ጋር ነው፤ አንቺ ከሴቶች መካከል የተባረክሽ ነሽ" አላት። ከተወዳጂቱ በፊት የነበሩት ዘመናት (ብሉይ ዓመታት) የአዳም ባሕሪይ ወድቆ ያለበት ጊዜ እንደመሆኑ መጠን ሐዘን በሰዎች ላይ ነግሧል፡፡ አሁን የፈረሰው ቤተ መቅደስ እንደገና ተሠርቶ የሚገለጽበት አዲስ ዘመን መጥቶአልና "ደስ ይበልሽ" ሲል አበሠራት፡፡ በተጨማሪ አዳም ከልዕልናው ተለየ፤ ወደቀ፤ ስንል ጸጋን ስለማጣቱም እያወራን ነውና፤ ይሄ የተገፈፈው ጸጋ ወደ ሰዎች ስለመመለሱ "ጸጋ የሞላብሽ ሆይ" በማለት አሳወቃት፡፡ ቀጠለና "ጌታ ከአንቺ ጋር ነው፤ አንቺ ከሴቶች መካከል የተባረክሽ (የተለየሽ) ነሽ" አላት፡፡

ከአካሉ የተሠራች በመሆኗ ምክንያት አዳም ሲፈርስ አብራ የፈረሰቺው ሔዋንን፤ በአብርሃም ተለይቶ የመውጣት አጥንትነት እንደገና እርሷንም ሊሠራት ጀመረ አላልንም? .. ስለዚህ ይህቺ "ሴት" ሆና በመጨረሻ በሥጋ የምትገለጸዋ የወንዱ ልጅ አጥንት፤ በአብርሃም የቃልኪዳን ትውልድ (በወንዶቹ) ውስጥ ስትገነባ.. ስትገነባ ትቆይና ጊዜው ሲደርስ ሥጋ ለብሳ ስትገለጽ፤ ድንግል ማርያም ሆናለች፡፡

እመቤቲቱ በሥጋ ከመገለጧ በፊት በነ'አብርሃም ተለይቶ የመውጣት የትውልድ ቅብብሎሽ ስትሠራ ቆይታለች፡፡ ተለይተው ከወጡት አባቶቿ የተወለደቺው ብላቴናይቱ፤ ይሄ የመለየት ኃይል፤ ሥጋ ሆና ከገብርኤል ጋር በተነጋገረችበት ጊዜ ላይ እንዲህ ሲመሰከርላት እንሰማለን፤ "አንቺ ከሴቶች መካከል የተለየሽ ነሽ"!

የመዳን ምክንያት ትሆን ዘንድ ተለይታ የወጣቺው ዳግማዊቱ አጥንት ሥጋ (ሔዋን) በሆነች ጊዜ፤ የሰማዩ ሥርዓት በምድር እየተደገመ ነው ብለናልና፤ አዳም የገነቱን ድምፅ ዳግም ይናገረዋል፡፡ "ይህች አጥንት ከአጥንቴ ናት፥ ሥጋም ከሥጋዬ ናት" ይላል፡፡ (ኦሪት ዘፍጥረት 2፥23) በሐዲስ ኪዳንኛ አገላለጽ፤ አዳም ከሥጋዋ ሥጋ፥ ከነፍሷ ነፍሷ ሊነሣ ከሔዋኒቱ "በመዋሐድ" ይወለዳል፡፡ ዘመኑ በተስፋ ሲነገሩ የነበሩ እውነታዎች በሥጋ የሚገለጡበት የጸጋ ዘመን ነውና፤ ዳግማዊው አዳም ተጨባጭ ሆኖ በዚህ ዓለም ይገለጻል፡፡ ስሙም ኢየሱስ (መፍረሳችንን የሚፈውስልን መድኃኒት) ሲባል ይሰየማል፡፡

አሁን ወደኋላ የወደቀው ቤተ መቅደስ ወደቦታው ተመለሰ፡፡ የፈረሰው ባሕሪይ ዳግም ተገነባ፡፡ በእግዚአብሔር ታስቦ፥ በስድስት ቀኖች ተሠርቶ፥ ሆኖም ወደ አንደኛው ቀን በመመለስ አፈር የሚሆነው ስብእና፤ እስከ አሁን ባየነው አካሄድ መሠረት እንደገና ከቀን አንድ ወደ ቀን ስድስት (ከመጀመሪያው ወደ ስድስተኛው ሺሕ ዘመን) እየተሰበሰበ ተሠራ፡፡

በሰማይ የተሠራው አዳም ስለፈረሰ፤ በምድር ድጋሚ የሰው ልጅ በእግዚአብሔር ፈቃድ ተሠራና ሁለተኛው አዳም ክርስቶስ ባሕሪያችንን ተዋሕዶ ተወለደ፡፡ ባሕሪያችንን ሲዋሐደው፤ የኛ ባሕሪይ ሞትን አስቀድሞ ሰምቶት ነበር፡፡ እግዚአብሔር አንዴ የተናገረው ቃል እስከ ዓለም ምፅዓት ድረስ የሚቀጥል ነውና፤ "ሞትን ትሞታለህ" የሚለው ድምፅ እስከ መጨረሻው ጊዜ ድረስ ለባሕሪያችን የሚደመጥ ይሆናል፡፡ በሌላ አባባል፤ ሞትን ከሰሙት አዳምና ሔዋን ሁላችን በሥጋ እንወለድ ዘንድ ግድ ነውና፤ ሞትን መሞታችን የማይቀር ነው፡፡

በሥጋ የተወለደው ዳግማዊው አዳምም፤ ንጹሕና ቅዱስ የሆነውን አካል ይዞ ቢመጣም፤ ለሞት የታዘዘ ባሕሪያችንን ስለተዋሐደ፤ በሥጋ ይሞት ዘንድ ግድ ይሆናል፡፡

ሆኖም ግን ሁለተኛው አዳም እንደ መጀመሪያው አዳም ያልሆነበት አንድ ሌላ ልዩ ነገር አለ፡፡ እርሱ ባሕሪይው የሰው ባሕሪይ ብቻ አልነበረም፤ ፍጹም አምላክ የሆነ የመለኮትም ባሕሪይ ነው፡፡ ተዋሕዶ በሚለው ዶግማ ውስጥ የምንናገረው እውነት ይህ ነው፡፡

የእግዚአብሔር ልጅ (ወልድ) እስከሞት ድረስ የሚሄደውን ባሕሪያችንን ገንዘብ አድርጎ በሥጋው ወራት ሲመላለስ፤ ወደ አይሁድ ቤተ መቅደስ በሄደበት አንዱ ጊዜ ላይ የሚከተለውን ተናገረ ይላል ዮሐንስ ፦

   "ይህን ቤተ መቅደስ አፍርሱት፥ በሦስት ቀንም አነሣዋለሁ አላቸው። ስለዚህ አይሁድ። ይህ ቤተ መቅደስ ከአርባ ስድስት ዓመት ጀምሮ ይሠራ ነበር፥ አንተስ በሦስት ቀን ታነሣዋለህን? አሉት። እርሱ ግን ስለ ሰውነቱ ቤተ መቅደስ ይል ነበር።"

                                            (የዮሐንስ ወንጌል 2፥21)

መድኃኒቱ ወደ ኢየሩሳሌም ቤተ መቅደስ በገባ ጊዜ  "በሬዎችንና በጎችን ርግቦችንም የሚሸጡትን ገንዘብ ለዋጮችንም ተቀምጠው አገኘ፤" በዚህም ተቆጥቶ ጅራፍ አነሳ፡፡ ነጋዴዎቹንም ከመቅደሱ አባረረ፡፡ አይሁዳውያኑም "ይህን ለማድረግ አንተ ምን ሥልጣን አለህ?" ሲሉ ጠየቁት፡፡ ጌታም መለሰና "ይህን ቤተ መቅደስ አፍርሱ፤ በሦስተኛው ቀንም እገነባዋለሁ" አላቸው፡፡

በዚህ መልስ ጠያቂዎቹ ተገረሙ፤ እንደ ድፍረትም ሳይቆጥሩት አይቀርም፡፡ "46 ዓመታትን የፈጀ ሕንጻን በ3 ቀን ሠራዋለሁ ትላለህን?" ሲሉም ተናገሩት፡፡ የመድኃኒቱ መልስ በኋላ የገባው ሐዋሪያ ግን "አፍርሱት፤ እኔም አነሣዋለሁ" ስላለው ቤተ መቅደስ ምንነት ሲረዳ፤ ከኢየሱስ ምላሽ ለጥቆ "እርሱ ግን ስለ ሰውነቱ ቤተ መቅደስ ይል ነበር" ብሎ በመጻፍ የተረዳውን ሚሥጢር አካፍሎናል፡፡

እንደተነጋገርነው አዳም የእግዚአብሔር መንፈስ ማደሪያ ቤተ መቅደስ ነው፡፡ ሰውነት ቤተ መቅደስነት ነው (ያልገባን ትልቅ ክብር!)፡፡ መድኃኒቱ አፍርሱት ሲል ለአይሁዶቹ የሚነግራቸው ስለ ሰውነቱ ነበር፡፡ በሌላ አባባል "የሚፈርስ ሥጋ (ሞትን የሰማ ባሕሪይ) ተዋሕጄያለሁና ጊዜው ሲደርስ ልትገድሉኝ አላችሁ" እያለ የሚመጣውን ተነብዮአል፡፡



tgoop.com/bemaledanek/2378
Create:
Last Update:

አንጓ ክስተቶችን እየመዘዙ ከመተረክ አንጻር፤ ይሄ "ዳግም" የመገንባት ሥራው "አብራምን ለይቶ በመጥራት" ጀመረ እንበል፡፡ (ኦሪት ዘፍጥረት 12፥1) እንደሚታወቀው አዳም የወደቀው በሴት ፈቃድ አማካኝነት ነው፡፡ ወይንም ወደ ምድር እንዲወርድ ምክንያት የሆነቺው ሔዋን ናት፡፡ ስለዚህ ወደዚህ ዓለም በሴት በኩል እየተወለድን እንመጣለን፡፡ (ዝኒ ከማሁ) እንኪያስ ቤተ መቅደሱ እንደገና መገንባት አለበት ስንል፤ አያይዘን ለመፍረሱ ምክንያት የሆነቺው ሔዋንም "እንደገና" መቀረጽ ይገባታል እያልን ነው፡፡ ("እንደገና" እየሠራን ነው ካልን፤ የመጀመሪያው የተፈጠርንበት የሰማዩ ሥርዓት በምድር ራሱው እየተደገመ እንደሚሄድ ልብ እንበል!)

እናም ለመፍረስ የሆነቺው ምክንያት፥ ለመገንባትም ምክንያት ትሆን ዘንድ፤ ይህቺ [አዲሲቱ] ምክንያት በአብራም ባሕሪይ ውስጥ መሠራት ጀመረች፡፡ በገነቱ ሥርዓት አዳምን አስተኝቶ ሔዋንን ከጎኑ በወጣች አጥንት እንደሠራት፤ በመሬቱም ሥርዓት ሌላውን ሕዝብ አስተኝቶ አብራምን ለይቶ እንደ አጥንት በማውጣት ይሠራ ጀመረ፡፡ ማለትም ሴቲቱ (ሔዋን) በአብራም ተለይቶ የመውጣት አጥንትነት እንደገና መሠራት ጀመረች፡፡ በገነቱ የአፈጣጠር ሥርዓት ስናወራ፤ አብራም ማለት ከአዳም ጎን የወጣው ሔዋን የተሠራችበት አጥንት ነው ማለት ነው፡፡

የብሉይ ዘመን የምንላቸው ስድስት ሺሕው ዓመታት (ስድስቱ ቀናት) ወንዱን ልጅ (አዳምን) ዳግም ለመውለድ ያማጡ ዓመታት ናቸው፡፡ በአብርሃም ተለይቶ የመውጣት የቃልኪዳን ትውልድነት ስትገነባ የቆየቺው ሴቲቱም፤ በምጥ ዘመኑ መድረሻ ላይ በተጨባጭ ተገልጣ ትታያለች፤ ድንግል ማርያም ሆና!

ከአዳም አስጀምረን እያየን የመጣነውን እውነታ፤ በሉቃስ ጽሕፈት (የሉቃስ ወንጌል 1፥28-35) ላይ በተቀመጠው፤ በገብርኤል ሰላምታ ውስጥ በአንኳር አገላለጽ ተጠቅልሎ እናገኘዋለን፡፡ መልአኩ ንግግሩን ሲጀምር "ደስ ይበልሽ፥ ጸጋ የሞላብሽ ሆይ፥ ጌታ ከአንቺ ጋር ነው፤ አንቺ ከሴቶች መካከል የተባረክሽ ነሽ" አላት። ከተወዳጂቱ በፊት የነበሩት ዘመናት (ብሉይ ዓመታት) የአዳም ባሕሪይ ወድቆ ያለበት ጊዜ እንደመሆኑ መጠን ሐዘን በሰዎች ላይ ነግሧል፡፡ አሁን የፈረሰው ቤተ መቅደስ እንደገና ተሠርቶ የሚገለጽበት አዲስ ዘመን መጥቶአልና "ደስ ይበልሽ" ሲል አበሠራት፡፡ በተጨማሪ አዳም ከልዕልናው ተለየ፤ ወደቀ፤ ስንል ጸጋን ስለማጣቱም እያወራን ነውና፤ ይሄ የተገፈፈው ጸጋ ወደ ሰዎች ስለመመለሱ "ጸጋ የሞላብሽ ሆይ" በማለት አሳወቃት፡፡ ቀጠለና "ጌታ ከአንቺ ጋር ነው፤ አንቺ ከሴቶች መካከል የተባረክሽ (የተለየሽ) ነሽ" አላት፡፡

ከአካሉ የተሠራች በመሆኗ ምክንያት አዳም ሲፈርስ አብራ የፈረሰቺው ሔዋንን፤ በአብርሃም ተለይቶ የመውጣት አጥንትነት እንደገና እርሷንም ሊሠራት ጀመረ አላልንም? .. ስለዚህ ይህቺ "ሴት" ሆና በመጨረሻ በሥጋ የምትገለጸዋ የወንዱ ልጅ አጥንት፤ በአብርሃም የቃልኪዳን ትውልድ (በወንዶቹ) ውስጥ ስትገነባ.. ስትገነባ ትቆይና ጊዜው ሲደርስ ሥጋ ለብሳ ስትገለጽ፤ ድንግል ማርያም ሆናለች፡፡

እመቤቲቱ በሥጋ ከመገለጧ በፊት በነ'አብርሃም ተለይቶ የመውጣት የትውልድ ቅብብሎሽ ስትሠራ ቆይታለች፡፡ ተለይተው ከወጡት አባቶቿ የተወለደቺው ብላቴናይቱ፤ ይሄ የመለየት ኃይል፤ ሥጋ ሆና ከገብርኤል ጋር በተነጋገረችበት ጊዜ ላይ እንዲህ ሲመሰከርላት እንሰማለን፤ "አንቺ ከሴቶች መካከል የተለየሽ ነሽ"!

የመዳን ምክንያት ትሆን ዘንድ ተለይታ የወጣቺው ዳግማዊቱ አጥንት ሥጋ (ሔዋን) በሆነች ጊዜ፤ የሰማዩ ሥርዓት በምድር እየተደገመ ነው ብለናልና፤ አዳም የገነቱን ድምፅ ዳግም ይናገረዋል፡፡ "ይህች አጥንት ከአጥንቴ ናት፥ ሥጋም ከሥጋዬ ናት" ይላል፡፡ (ኦሪት ዘፍጥረት 2፥23) በሐዲስ ኪዳንኛ አገላለጽ፤ አዳም ከሥጋዋ ሥጋ፥ ከነፍሷ ነፍሷ ሊነሣ ከሔዋኒቱ "በመዋሐድ" ይወለዳል፡፡ ዘመኑ በተስፋ ሲነገሩ የነበሩ እውነታዎች በሥጋ የሚገለጡበት የጸጋ ዘመን ነውና፤ ዳግማዊው አዳም ተጨባጭ ሆኖ በዚህ ዓለም ይገለጻል፡፡ ስሙም ኢየሱስ (መፍረሳችንን የሚፈውስልን መድኃኒት) ሲባል ይሰየማል፡፡

አሁን ወደኋላ የወደቀው ቤተ መቅደስ ወደቦታው ተመለሰ፡፡ የፈረሰው ባሕሪይ ዳግም ተገነባ፡፡ በእግዚአብሔር ታስቦ፥ በስድስት ቀኖች ተሠርቶ፥ ሆኖም ወደ አንደኛው ቀን በመመለስ አፈር የሚሆነው ስብእና፤ እስከ አሁን ባየነው አካሄድ መሠረት እንደገና ከቀን አንድ ወደ ቀን ስድስት (ከመጀመሪያው ወደ ስድስተኛው ሺሕ ዘመን) እየተሰበሰበ ተሠራ፡፡

በሰማይ የተሠራው አዳም ስለፈረሰ፤ በምድር ድጋሚ የሰው ልጅ በእግዚአብሔር ፈቃድ ተሠራና ሁለተኛው አዳም ክርስቶስ ባሕሪያችንን ተዋሕዶ ተወለደ፡፡ ባሕሪያችንን ሲዋሐደው፤ የኛ ባሕሪይ ሞትን አስቀድሞ ሰምቶት ነበር፡፡ እግዚአብሔር አንዴ የተናገረው ቃል እስከ ዓለም ምፅዓት ድረስ የሚቀጥል ነውና፤ "ሞትን ትሞታለህ" የሚለው ድምፅ እስከ መጨረሻው ጊዜ ድረስ ለባሕሪያችን የሚደመጥ ይሆናል፡፡ በሌላ አባባል፤ ሞትን ከሰሙት አዳምና ሔዋን ሁላችን በሥጋ እንወለድ ዘንድ ግድ ነውና፤ ሞትን መሞታችን የማይቀር ነው፡፡

በሥጋ የተወለደው ዳግማዊው አዳምም፤ ንጹሕና ቅዱስ የሆነውን አካል ይዞ ቢመጣም፤ ለሞት የታዘዘ ባሕሪያችንን ስለተዋሐደ፤ በሥጋ ይሞት ዘንድ ግድ ይሆናል፡፡

ሆኖም ግን ሁለተኛው አዳም እንደ መጀመሪያው አዳም ያልሆነበት አንድ ሌላ ልዩ ነገር አለ፡፡ እርሱ ባሕሪይው የሰው ባሕሪይ ብቻ አልነበረም፤ ፍጹም አምላክ የሆነ የመለኮትም ባሕሪይ ነው፡፡ ተዋሕዶ በሚለው ዶግማ ውስጥ የምንናገረው እውነት ይህ ነው፡፡

የእግዚአብሔር ልጅ (ወልድ) እስከሞት ድረስ የሚሄደውን ባሕሪያችንን ገንዘብ አድርጎ በሥጋው ወራት ሲመላለስ፤ ወደ አይሁድ ቤተ መቅደስ በሄደበት አንዱ ጊዜ ላይ የሚከተለውን ተናገረ ይላል ዮሐንስ ፦

   "ይህን ቤተ መቅደስ አፍርሱት፥ በሦስት ቀንም አነሣዋለሁ አላቸው። ስለዚህ አይሁድ። ይህ ቤተ መቅደስ ከአርባ ስድስት ዓመት ጀምሮ ይሠራ ነበር፥ አንተስ በሦስት ቀን ታነሣዋለህን? አሉት። እርሱ ግን ስለ ሰውነቱ ቤተ መቅደስ ይል ነበር።"

                                            (የዮሐንስ ወንጌል 2፥21)

መድኃኒቱ ወደ ኢየሩሳሌም ቤተ መቅደስ በገባ ጊዜ  "በሬዎችንና በጎችን ርግቦችንም የሚሸጡትን ገንዘብ ለዋጮችንም ተቀምጠው አገኘ፤" በዚህም ተቆጥቶ ጅራፍ አነሳ፡፡ ነጋዴዎቹንም ከመቅደሱ አባረረ፡፡ አይሁዳውያኑም "ይህን ለማድረግ አንተ ምን ሥልጣን አለህ?" ሲሉ ጠየቁት፡፡ ጌታም መለሰና "ይህን ቤተ መቅደስ አፍርሱ፤ በሦስተኛው ቀንም እገነባዋለሁ" አላቸው፡፡

በዚህ መልስ ጠያቂዎቹ ተገረሙ፤ እንደ ድፍረትም ሳይቆጥሩት አይቀርም፡፡ "46 ዓመታትን የፈጀ ሕንጻን በ3 ቀን ሠራዋለሁ ትላለህን?" ሲሉም ተናገሩት፡፡ የመድኃኒቱ መልስ በኋላ የገባው ሐዋሪያ ግን "አፍርሱት፤ እኔም አነሣዋለሁ" ስላለው ቤተ መቅደስ ምንነት ሲረዳ፤ ከኢየሱስ ምላሽ ለጥቆ "እርሱ ግን ስለ ሰውነቱ ቤተ መቅደስ ይል ነበር" ብሎ በመጻፍ የተረዳውን ሚሥጢር አካፍሎናል፡፡

እንደተነጋገርነው አዳም የእግዚአብሔር መንፈስ ማደሪያ ቤተ መቅደስ ነው፡፡ ሰውነት ቤተ መቅደስነት ነው (ያልገባን ትልቅ ክብር!)፡፡ መድኃኒቱ አፍርሱት ሲል ለአይሁዶቹ የሚነግራቸው ስለ ሰውነቱ ነበር፡፡ በሌላ አባባል "የሚፈርስ ሥጋ (ሞትን የሰማ ባሕሪይ) ተዋሕጄያለሁና ጊዜው ሲደርስ ልትገድሉኝ አላችሁ" እያለ የሚመጣውን ተነብዮአል፡፡

BY በማለዳ ንቁ ቁጥር ! ፪


Share with your friend now:
tgoop.com/bemaledanek/2378

View MORE
Open in Telegram


Telegram News

Date: |

Telegram message that reads: "Bear Market Screaming Therapy Group. You are only allowed to send screaming voice notes. Everything else = BAN. Text pics, videos, stickers, gif = BAN. Anything other than screaming = BAN. You think you are smart = BAN. How to Create a Private or Public Channel on Telegram? To edit your name or bio, click the Menu icon and select “Manage Channel.” Matt Hussey, editorial director of NEAR Protocol (and former editor-in-chief of Decrypt) responded to the news of the Telegram group with “#meIRL.” “Hey degen, are you stressed? Just let it all out,” he wrote, along with a link to join the group.
from us


Telegram በማለዳ ንቁ ቁጥር ! ፪
FROM American