BEMALEDANEK Telegram 2379
ስለዚህ ዓለም በዚህ ዘመኗ አርጅታብናለች፡፡ ከፀሐይ በታች ምንም አዲስ ነገር የለም የሚለው የሕይወት ጽሑፍ በገሐድ እንደጋራ ይነበበን ጀምሯል፡፡ ሁሉ ነገር ጥለነው የምንሄደው ከንቱ ድካም እንደሆነ ሲገባን ተስፋ መቁረጥን በምድራችን ላይ አንግሠነዋል፡፡ እንኪያስ መልካም ብለን ስንከባከባቸው በቆዩ የሰውነት እሴቶች ላይ ማመፅ ጀምረናል፡፡ መኖርን አሁን በምናየው ልክ እየለካን አፍንጫችን ሥር ባሉ ጉዳዮች ጭልጥ ብለን መጥፋትን አማራጭ አድርገናል፡፡ ወዴት እንደምንሄድ፣ አድራሻችን የት እንደሚያደርስ፣ አቅጣጫችን ወደ ምን እንደሚመራ አናውቅም፤ የነፍስ ካርታ የለንም!

ሦስተኛውን ቤተ መቅደስ አላወቅነውም፤ ለማወቅም ፈቃድ ያለን አይመስልም፡፡ ከማመን አለማመን ተሽሎናል፡፡ ባሕሪያችን ወደ ዘላለም እረፍት ለመሄድ ይታገለናል፤ ግን መንገዱን ስለማናውቀው የምናደርገውን አጥተን፤ በሌላ በመሰለን መንገድ ስንባዝን ይኸው ዙሪያው ተዘግቶብን አለን፡፡ ወደ ዕፀ ሕይወት እንዳንደርስ የተጋረደው ኪሩብ፤ በሐዲስ ኪዳንም ዘመን ከፊታችን እስከ ሰይፉ ቆሞ የሚታየን ሰዎች ብዙ እንሆናለን፡፡

እስኪ ዝም ብለን እንጠይቅ፡፡ ምንድነው የመኖራችን ዋጋ? ምንድነው የሕይወት ትርጉም? የምንሠራውና የምናውቀው ሁሉ ከሞት ባሻገር ካልተከተለን እንግዲያው ልፋታችን የቱን ሚዛን ይደፋል? ፍጻሜያችን ምንድነው? .. እሺ የምንመኘው ሁሉ ሆነ፡፡ ገንዘቡ ገባ፤ ሒሳቡም ተከማቸ፡፡ ከዛስ? ምንድነው መጨረሻው? ተደሰቶ የመኖርን ብያኔ በውል አውቀነዋል ወይ? ከመብላት፣ ከመጠጣትና ከመዝናኛ ያለፈ ፍጡርነት በኛነት ውስጥ የለም? ካለስ ምንድነው? በእግዚአብሔር ሕልውና ካመንን እህሳ የተናገራቸውን ቃላት እንቀበላቸዋለን? ወይስ አንቀበላቸውም? ሳንወለድ የነበረውን ጊዜ አናውቀውም፤ አናውቀውም ማለት ግን የለም ማለት አልነበረም፡፡ እናስ ከሞትን በኋላ የሚኖረውን ጊዜ ስናስብ ምን እናስባለን? አሊያስ ቀድሞውኑ አናስብም? .. እስኪ ዝም ብለን እንጠይቅ!

መጠየቅና ተረጋግተን ማሰብ ስንጀምር፤ የእውነትን ፈለግ ለመከተል ዕድል እናገኛለን፡፡ መድኃኒቱ "ሕይወትም፣ መንገድም፣ እውነትም" ነው፡፡ ያገኘናል፤ ከተዘጋብን ቅርቃር ያወጣናል፤ ባሕሪያችንን ባሕሪይ አድርጎ በአባት ቀኝ ተቀምጦአልና የምንበላወስበትን ድካም ሁሉ ያውቀዋል! ስላወቀም ይሸከመዋል፤ የእርሱን ቀሊል ቀንበርም ይሰጠናል፡፡ "አሳርፋችኋለሁ" ሲል በወንጌላዊ ማቴዎስ ዘመን የተናገረው ቃል ያለአንዳች ጥርጥር ዛሬም የታመነ ነው፡፡ ይሄም ያረፈ ሰው የሚጽፈው ምስክርነት ነው፡፡ አዎ፤ ሦስተኛውን ቤተመቅደስ ይገነባ ዘንድ ውድ ሥጋውን የቆረሰ ንጹሕ ደሙን ያፈሰሰ አባትየው፤ የታመነ ነው፡፡ ስለ እዚህ ስለተከበረ ሥጋና ደም፤ ስለ ቤተ መቅደስነታችን ማሰብ እንጀምር!


(ጽሑፉ ረዝሞዋል፤ ቢሆንም አንብቡ! እንደተሰጠኝ አቀብያለሁ፤ የቀረው ድርሻ የእጃችሁ ነው፤ "በጎቹ" ድምፁን ይሰሙታል! ይቀበሉ ዘንድ ራሳቸውን ለአባትየው ያቀበሉ ሁሉ የሚገባቸውን ያገኙታል!)

ወደ ሥጋና ደሙ መጓዛችንን እንቀጥላለን. . .
#ጸባኦት_ይከተላችሁ
@bemaledanek



tgoop.com/bemaledanek/2379
Create:
Last Update:

ስለዚህ ዓለም በዚህ ዘመኗ አርጅታብናለች፡፡ ከፀሐይ በታች ምንም አዲስ ነገር የለም የሚለው የሕይወት ጽሑፍ በገሐድ እንደጋራ ይነበበን ጀምሯል፡፡ ሁሉ ነገር ጥለነው የምንሄደው ከንቱ ድካም እንደሆነ ሲገባን ተስፋ መቁረጥን በምድራችን ላይ አንግሠነዋል፡፡ እንኪያስ መልካም ብለን ስንከባከባቸው በቆዩ የሰውነት እሴቶች ላይ ማመፅ ጀምረናል፡፡ መኖርን አሁን በምናየው ልክ እየለካን አፍንጫችን ሥር ባሉ ጉዳዮች ጭልጥ ብለን መጥፋትን አማራጭ አድርገናል፡፡ ወዴት እንደምንሄድ፣ አድራሻችን የት እንደሚያደርስ፣ አቅጣጫችን ወደ ምን እንደሚመራ አናውቅም፤ የነፍስ ካርታ የለንም!

ሦስተኛውን ቤተ መቅደስ አላወቅነውም፤ ለማወቅም ፈቃድ ያለን አይመስልም፡፡ ከማመን አለማመን ተሽሎናል፡፡ ባሕሪያችን ወደ ዘላለም እረፍት ለመሄድ ይታገለናል፤ ግን መንገዱን ስለማናውቀው የምናደርገውን አጥተን፤ በሌላ በመሰለን መንገድ ስንባዝን ይኸው ዙሪያው ተዘግቶብን አለን፡፡ ወደ ዕፀ ሕይወት እንዳንደርስ የተጋረደው ኪሩብ፤ በሐዲስ ኪዳንም ዘመን ከፊታችን እስከ ሰይፉ ቆሞ የሚታየን ሰዎች ብዙ እንሆናለን፡፡

እስኪ ዝም ብለን እንጠይቅ፡፡ ምንድነው የመኖራችን ዋጋ? ምንድነው የሕይወት ትርጉም? የምንሠራውና የምናውቀው ሁሉ ከሞት ባሻገር ካልተከተለን እንግዲያው ልፋታችን የቱን ሚዛን ይደፋል? ፍጻሜያችን ምንድነው? .. እሺ የምንመኘው ሁሉ ሆነ፡፡ ገንዘቡ ገባ፤ ሒሳቡም ተከማቸ፡፡ ከዛስ? ምንድነው መጨረሻው? ተደሰቶ የመኖርን ብያኔ በውል አውቀነዋል ወይ? ከመብላት፣ ከመጠጣትና ከመዝናኛ ያለፈ ፍጡርነት በኛነት ውስጥ የለም? ካለስ ምንድነው? በእግዚአብሔር ሕልውና ካመንን እህሳ የተናገራቸውን ቃላት እንቀበላቸዋለን? ወይስ አንቀበላቸውም? ሳንወለድ የነበረውን ጊዜ አናውቀውም፤ አናውቀውም ማለት ግን የለም ማለት አልነበረም፡፡ እናስ ከሞትን በኋላ የሚኖረውን ጊዜ ስናስብ ምን እናስባለን? አሊያስ ቀድሞውኑ አናስብም? .. እስኪ ዝም ብለን እንጠይቅ!

መጠየቅና ተረጋግተን ማሰብ ስንጀምር፤ የእውነትን ፈለግ ለመከተል ዕድል እናገኛለን፡፡ መድኃኒቱ "ሕይወትም፣ መንገድም፣ እውነትም" ነው፡፡ ያገኘናል፤ ከተዘጋብን ቅርቃር ያወጣናል፤ ባሕሪያችንን ባሕሪይ አድርጎ በአባት ቀኝ ተቀምጦአልና የምንበላወስበትን ድካም ሁሉ ያውቀዋል! ስላወቀም ይሸከመዋል፤ የእርሱን ቀሊል ቀንበርም ይሰጠናል፡፡ "አሳርፋችኋለሁ" ሲል በወንጌላዊ ማቴዎስ ዘመን የተናገረው ቃል ያለአንዳች ጥርጥር ዛሬም የታመነ ነው፡፡ ይሄም ያረፈ ሰው የሚጽፈው ምስክርነት ነው፡፡ አዎ፤ ሦስተኛውን ቤተመቅደስ ይገነባ ዘንድ ውድ ሥጋውን የቆረሰ ንጹሕ ደሙን ያፈሰሰ አባትየው፤ የታመነ ነው፡፡ ስለ እዚህ ስለተከበረ ሥጋና ደም፤ ስለ ቤተ መቅደስነታችን ማሰብ እንጀምር!


(ጽሑፉ ረዝሞዋል፤ ቢሆንም አንብቡ! እንደተሰጠኝ አቀብያለሁ፤ የቀረው ድርሻ የእጃችሁ ነው፤ "በጎቹ" ድምፁን ይሰሙታል! ይቀበሉ ዘንድ ራሳቸውን ለአባትየው ያቀበሉ ሁሉ የሚገባቸውን ያገኙታል!)

ወደ ሥጋና ደሙ መጓዛችንን እንቀጥላለን. . .
#ጸባኦት_ይከተላችሁ
@bemaledanek

BY በማለዳ ንቁ ቁጥር ! ፪


Share with your friend now:
tgoop.com/bemaledanek/2379

View MORE
Open in Telegram


Telegram News

Date: |

Telegram Android app: Open the chats list, click the menu icon and select “New Channel.” SUCK Channel Telegram Add the logo from your device. Adjust the visible area of your image. Congratulations! Now your Telegram channel has a face Click “Save”.! On June 7, Perekopsky met with Brazilian President Jair Bolsonaro, an avid user of the platform. According to the firm's VP, the main subject of the meeting was "freedom of expression." 1What is Telegram Channels?
from us


Telegram በማለዳ ንቁ ቁጥር ! ፪
FROM American