BEMALEDANEK Telegram 2383
በማለዳ ንቁ ቁጥር ! ፪
3•  ቅዱስ ቁርባን ክፍል - ፪       3.2•  ቅዱስ ቁርባን ለምን እንውሰድ ?            3.2.1•  በእግዚአብሔር በኩል                ✞ ፫ተኛው ቤተ መቅደስ (ትንሣኤ) ✞    "ኢየሱስም መልሶ። ይህን ቤተ መቅደስ አፍርሱት፥ በሦስት ቀንም አነሣዋለሁ አላቸው። ስለዚህ አይሁድ። ይህ ቤተ መቅደስ ከአርባ ስድስት ዓመት ጀምሮ ይሠራ ነበር፥ አንተስ በሦስት ቀን ታነሣዋለህን?…
3•  ቅዱስ ቁርባን

ክፍል - ፫

      3.2•  ቅዱስ ቁርባን ለምን እንውሰድ ?

           3.2.1•  በእግዚአብሔር በኩል

                  ✞ ሥርየተ ኃጢአት

   "ፍቅርም እንደዚህ ነው፤ እግዚአብሔር እርሱ ራሱ እንደ ወደደን ስለ ኃጢአታችንም ማስተስሪያ ይሆን ዘንድ ልጁን እንደ ላከ እንጂ እኛ እግዚአብሔርን እንደ ወደድነው አይደለም።"

                                      (1ኛ የዮሐንስ መልእክት 4፥10)

እግዚአብሔር በመጀመሪያ ካየልን መድረሻና ንጹሕ ፈቃድ ወጥተን፤ ከ"አትንኩ!" ትእዛዝ ተላልፈን ያልተፈቀደልንን በመንካታችን ከአምላክ አሳብና ባሕሪይ ተለይተናል፡፡ ፍጹሙን ሕግ ጥሰን ሥርዓት አፋልሰናል፡፡ ይህም ባሕሪያችን በገነት ሳለ የፈጸመው ቀዳሚው ጥፋት "የአዳም ኃጢአት" ሲባል ይጠራል፡፡

የሰው ልጅ የተከለከለውን የእውቀት ዛፍ ያለ ጊዜው ከበላ በኋላ መልካሙን እና ክፉውን ለማወቅ የሚችልበት የአእምሮው ኃይል ነቅቶአል፡፡ (ኦሪት ዘፍጥረት 3፥22) ይሄ እውነት የሚነግረን እውቀት የሚባለው ጉዳይ መልካምና ክፉ የሚባል ሁለት መልክ እንዳለው ነው፡፡ በመልካሙ እውቀት መንፈስ ቅዱስ ይገለጻል፤ በክፉው እውቀት ደግሞ መንፈስ ርኩስ ይገለጻል፡፡ ስለዚህ በሌላ አነጋገር እያልን ያለነው፤ አዳም ከገነት ከወጣ በኋላ በተቀደሰና ባልተቀደሰ መንፈስ መካከል የሚዋትት ሕይወት ይኖረዋል ነው፡፡

የአዳም ባሕሪይ የእውቀትን ዛፍ ከወሰደ በኋላ፤ በአእምሮ ታውቀው የሚገለጡ ግንዛቤዎቹ በመልካም (በጽድቅ) እና በክፉ (በኃጢአት) መካከል የሚመላለሱ ሆነዋል፡፡ ከዚህ የተነሣም፥ የሰው ልጅ ኃጢአትን አውቆ፥ በመቀጠል የሚፈጽምበት፥ ሁኔታ መጥቶአል፡፡ ይሄም ነገር በመጀመሪያ በአዳም ልጅ በቃየን ሕይወት ላይ ሊረጋገጥ ችሎአል፡፡

ባሕሪያችን ኃጢአትን ለይቶ አውቆ መሥራት ጀመረ ማለት፤ ከፈጣሪ ጋር የነበረን የአንድነት ቅርበት እየሰፋ ይሄዳል ማለት ነው፡፡ አዳም ከገነት (የእግዚአብሔር ፈቃድ ከነበረው ቦታ) ወጣ የሚለውን አሳብ፤ የሰው ልጅ ባሕሪይ የአምላክን ፈቃድና እውነት ከሚከተልበት መንገድ እየራቀ እየራቀ ወጣ በሚል አተረጓጎም መረዳት ይኖርብናል፡፡ የዚህም ትንታኔ ማስረጃ፤ አዳም ወደ መሬት ተመልሶ ከመጣበት ጀምሮ እስከ አሁን ድረስ ያለው የአኗኗራችን ገጽታ ነው፡፡ ጊዜ ጊዜን እየተካ ዘመናት ወደፊት በቆጠሩ ቁጥር፤ የሰው ልጆችም በኃጢአትና በዓመፃ ሕይወት የምንመላለስበት አኳኋንም ጨምሯል፡፡ በዚህም ምክንያት ከእግዚአብሔር ተለያይተን የምንኖርበት ሁኔታ ከቀን ቀን እያደገ ሄዶ ዛሬ የምንገኝበት ከባድ የክፋት ዘመን ላይ አድርሶናል፡፡

በኛ እና በአምላክ መካከል ገብቶ መለያየትን ያመጣው ኃጢአትና የኃጢአት ኃይል (ዲያቢሎስ) እንዲወጣ፤ የእግዚአብሔር ልጅ ወገናችን ሆኖ ወደኛ መጣ፡፡ ኃጢአትን የማያውቅ፣ ንጹሕና ቅዱስ የሆነ ሰብአዊ ሥጋና ባሕሪይ ለብሶ፤ የኛን፥ በኃጢአት እሾህ እየተወጋ፣ በእርግማን አሜኬላ እየታነቀ፣ በስሕተት እውቀት እየተመራ ለረቂቅ ባርነት ተገዝቶ ያለ ሕልውናችንን ነጻ ሊያደርግልን ኑሮአችንን በትሕትና ሆኖ ኖረ፡፡ ጳውሎስ ሲናገር ፦

    "እንግዲህ ልጆቹ በሥጋና በደም ስለሚካፈሉ፥ እርሱ ደግሞ በሞት ላይ ሥልጣን ያለውን በሞት እንዲሽር፥ ይኸውም ዲያብሎስ ነው፥ በሕይወታቸውም ሁሉ ስለ ሞት ፍርሃት በባርነት ይታሰሩ የነበሩትን ሁሉ ነጻ እንዲያወጣ፥ በሥጋና በደም እንዲሁ ተካፈለ። የአብርሃምን ዘር ይዞአል እንጂ የያዘው የመላእክትን አይደለም። ስለዚህ የሕዝብን ኃጢአት ለማስተስረይ፥ ለእግዚአብሔር በሆነው ነገር ሁሉ የሚምርና የታመነ ሊቀ ካህናት እንዲሆን፥ በነገር ሁሉ ወንድሞቹን ሊመስል ተገባው።"

                                             (ወደ ዕብራውያን 2፥14-17)

በእርሱ ቅድስና ሊቀድሰን የወደደ ቅዱስ ጌታ፤ በባሕሪይና በዘራችን ተጣብቶ ወደ ውድቀት ሲመራን የነበረውን የገነቱን ጥፋት ሊያጠፋልን፤ ጥፋትን የማያውቅ ሥጋውን እንጀራ አድርጎ በማቅረብ፤ በመብላት እንደወደቅን በመብላት ደሞ ከወደቅንበት እንድንነሣ ራሱን "እንካችሁ" አለን፡፡

   "ሲበሉም ኢየሱስ እንጀራን አንሥቶ ባረከ ቈርሶም ለደቀ መዛሙርቱ ሰጠና። እንካችሁ፥ ብሉ ይህ ሥጋዬ ነው አለ። ጽዋንም አንሥቶ አመስግኖም ሰጣቸው እንዲህም አለ። ሁላችሁ ከእርሱ ጠጡ፤ ስለ ብዙዎች ለኃጢአት ይቅርታ የሚፈስ የአዲስ ኪዳን ደሜ ይህ ነው።"

                                             (የማቴዎስ ወንጌል 26፥26-28)


የምንነጋገርበት ጉዳይ "ስለ ብዙዎች ለኃጢአት ይቅርታ የሚፈስ የአዲስ ኪዳን ደሜ ይህ ነው" የሚለው የመድኃኒቱ የምሕረት ድምፅ ላይ አለ፡፡

ኃጢአት ፈጽመን ከእግዚአብሔር እየራቅን መኖር ከጀመርን በኋላ፤ ስሕተታችንን የምናርምበትን መንገድ ልናገኘው አልቻልንም ነበር፡፡ ይልቁንም ከስሕተት ላይ ሌላ ስሕተት እየደረብን፤ ከዓመፃ ላይ ዓመፃ እየጨመርን፤ ከነባር ኃጢአት ላይ አዲስ ኃጢአት እየፈጸምን፤ ከክፉ መናፍስት ጋር በአንድም በሌላም አቅጣጫ እየተባበርን መኖርን መረጥን፡፡

ይሄ ምርጫችን ደግሞ የእግዚአብሔር ፈቃድ አይደለም፡፡ እርሱ በቀዳማዊው አሳቡ ሲፈጥረን ለዚህ አይነት ሕይወት ፈጽሞ አላሰበንም፡፡ በመጀመሪያ መልካም እንደሆነ ያየልን የስብእና ከፍታ ከሥጋ ፈቃዳችን የተነሣ ወደኛ ሳይመጣ ቀርቶአል፡፡ ይሄ አሳብ ደግሞ ሕያው በሆነ መለኮት የታሰበ ሕያው አሳብ ነውና ከመፈጸም ሊቀር አይችልም፡፡ ስለዚህ ያሰበልንን ሊነግረን በቃሉ በኩል እርሱ ወደኛ መጣ፡፡

የእግዚአብሔር ቃል ወደኛ የመጣው ከጠፋንበት (ከአምላክ ከራቅንበት) ቦታ ያገኘን ዘንድ እንደሆነ እናስታውስ፡፡ የጠፋነው ደግሞ በኃጢአት ነው፡፡ ስለሆነ ከጠፋንበት የምንገኘው ለኃጢአታችን ሥርየት ሲከናወንልን ነው ማለት ነው፡፡ በመሆኑም ፈላጊያችን ቃል ሥጋ (ዘመድ) ሆነና የራቀ ሕልውናችንን ወደርሱ አቀረበው፡፡ በሌላ አነጋገር "ወንድማችን" እስከሆነበት ጥግ ድረስ ከሸሸንበት ጎሬ ገብቶ ሊወዳጀን ፈቀደ፡፡

አዳም ከወደቀበት ስፍራ ላይ በመገኘት አዳምን የሆነው ተወዳጁ፤ የሰውን ባሕሪይ ከወደቀበት አንስቶ ወደ አባቱ መንግሥት ለመመለስ ዋጋ መክፈል ነበረበት (በእርግጥም መነሣት እንጂ መውደቅ ዋጋ አያስከፍልም)፡፡ ይህም ዋጋ እስከ ሞት ድረስ የሚሄድ ታላቅ ዋጋ ነው፡፡ ከሞትም ደግሞ ለከባድ ሕማምና ለከፍተኛ ስቃይ የሚዳርግ ቁስልን የሚጠይቅ ሞት!

     "እርሱ ግን ስለ መተላለፋችን ቈሰለ፥ ስለ በደላችንም ደቀቀ፤ የደኅንነታችንም ተግሣጽ በእርሱ ላይ ነበረ፥ በእርሱም ቍስል እኛ ተፈወስን።"

                                                       (ትንቢተ ኢሳይያስ 53፥5)

እኛ እንገረፈው ዘንድ የተገባ ጅራፍን በጀርባው አስተናገደ፡፡ እኛ እንቀበለው ዘንድ የሚያስፈልግ ድብደባን በሰውነቱ ታገሰ፡፡ እኛ እንሸከመው ዘንድ የተስማማ መከራን በትከሻው አኖረ፡፡ እኛ እንታመመው ዘንድ የታዘዘ ቁስልን እርሱ ተቀበለ፡፡ በብያኔ ደረጃ፤ ቁስል ማለት የሥጋ መቆረስ ማለት ነው ብንል እንችላለን፡፡ እነሆም ስለኛ ስለሁላችን ኃጢአት ሲል አንዱ ክርስቶስ ክቡር ሥጋውን በመስቀል ላይ ቆረሰ፡፡

መድኃኒቱ በመስቀል ላይ ሆኖ መሥዋዕት ከመሆኑ አንድ ዕለት አስቀድሞ፤ ለተማሪዎቹ ሥጋውን እንዲበሉ እንደሰጣቸው በወንጌል ተጽፎልናል፡፡ ይሄ ሥጋ የተቆረሰው ግን በቀጣዩ ዕለት በአርብ ነበር፡፡ እስቲ በቀላል በምሳሌ እንየው፡፡



tgoop.com/bemaledanek/2383
Create:
Last Update:

3•  ቅዱስ ቁርባን

ክፍል - ፫

      3.2•  ቅዱስ ቁርባን ለምን እንውሰድ ?

           3.2.1•  በእግዚአብሔር በኩል

                  ✞ ሥርየተ ኃጢአት

   "ፍቅርም እንደዚህ ነው፤ እግዚአብሔር እርሱ ራሱ እንደ ወደደን ስለ ኃጢአታችንም ማስተስሪያ ይሆን ዘንድ ልጁን እንደ ላከ እንጂ እኛ እግዚአብሔርን እንደ ወደድነው አይደለም።"

                                      (1ኛ የዮሐንስ መልእክት 4፥10)

እግዚአብሔር በመጀመሪያ ካየልን መድረሻና ንጹሕ ፈቃድ ወጥተን፤ ከ"አትንኩ!" ትእዛዝ ተላልፈን ያልተፈቀደልንን በመንካታችን ከአምላክ አሳብና ባሕሪይ ተለይተናል፡፡ ፍጹሙን ሕግ ጥሰን ሥርዓት አፋልሰናል፡፡ ይህም ባሕሪያችን በገነት ሳለ የፈጸመው ቀዳሚው ጥፋት "የአዳም ኃጢአት" ሲባል ይጠራል፡፡

የሰው ልጅ የተከለከለውን የእውቀት ዛፍ ያለ ጊዜው ከበላ በኋላ መልካሙን እና ክፉውን ለማወቅ የሚችልበት የአእምሮው ኃይል ነቅቶአል፡፡ (ኦሪት ዘፍጥረት 3፥22) ይሄ እውነት የሚነግረን እውቀት የሚባለው ጉዳይ መልካምና ክፉ የሚባል ሁለት መልክ እንዳለው ነው፡፡ በመልካሙ እውቀት መንፈስ ቅዱስ ይገለጻል፤ በክፉው እውቀት ደግሞ መንፈስ ርኩስ ይገለጻል፡፡ ስለዚህ በሌላ አነጋገር እያልን ያለነው፤ አዳም ከገነት ከወጣ በኋላ በተቀደሰና ባልተቀደሰ መንፈስ መካከል የሚዋትት ሕይወት ይኖረዋል ነው፡፡

የአዳም ባሕሪይ የእውቀትን ዛፍ ከወሰደ በኋላ፤ በአእምሮ ታውቀው የሚገለጡ ግንዛቤዎቹ በመልካም (በጽድቅ) እና በክፉ (በኃጢአት) መካከል የሚመላለሱ ሆነዋል፡፡ ከዚህ የተነሣም፥ የሰው ልጅ ኃጢአትን አውቆ፥ በመቀጠል የሚፈጽምበት፥ ሁኔታ መጥቶአል፡፡ ይሄም ነገር በመጀመሪያ በአዳም ልጅ በቃየን ሕይወት ላይ ሊረጋገጥ ችሎአል፡፡

ባሕሪያችን ኃጢአትን ለይቶ አውቆ መሥራት ጀመረ ማለት፤ ከፈጣሪ ጋር የነበረን የአንድነት ቅርበት እየሰፋ ይሄዳል ማለት ነው፡፡ አዳም ከገነት (የእግዚአብሔር ፈቃድ ከነበረው ቦታ) ወጣ የሚለውን አሳብ፤ የሰው ልጅ ባሕሪይ የአምላክን ፈቃድና እውነት ከሚከተልበት መንገድ እየራቀ እየራቀ ወጣ በሚል አተረጓጎም መረዳት ይኖርብናል፡፡ የዚህም ትንታኔ ማስረጃ፤ አዳም ወደ መሬት ተመልሶ ከመጣበት ጀምሮ እስከ አሁን ድረስ ያለው የአኗኗራችን ገጽታ ነው፡፡ ጊዜ ጊዜን እየተካ ዘመናት ወደፊት በቆጠሩ ቁጥር፤ የሰው ልጆችም በኃጢአትና በዓመፃ ሕይወት የምንመላለስበት አኳኋንም ጨምሯል፡፡ በዚህም ምክንያት ከእግዚአብሔር ተለያይተን የምንኖርበት ሁኔታ ከቀን ቀን እያደገ ሄዶ ዛሬ የምንገኝበት ከባድ የክፋት ዘመን ላይ አድርሶናል፡፡

በኛ እና በአምላክ መካከል ገብቶ መለያየትን ያመጣው ኃጢአትና የኃጢአት ኃይል (ዲያቢሎስ) እንዲወጣ፤ የእግዚአብሔር ልጅ ወገናችን ሆኖ ወደኛ መጣ፡፡ ኃጢአትን የማያውቅ፣ ንጹሕና ቅዱስ የሆነ ሰብአዊ ሥጋና ባሕሪይ ለብሶ፤ የኛን፥ በኃጢአት እሾህ እየተወጋ፣ በእርግማን አሜኬላ እየታነቀ፣ በስሕተት እውቀት እየተመራ ለረቂቅ ባርነት ተገዝቶ ያለ ሕልውናችንን ነጻ ሊያደርግልን ኑሮአችንን በትሕትና ሆኖ ኖረ፡፡ ጳውሎስ ሲናገር ፦

    "እንግዲህ ልጆቹ በሥጋና በደም ስለሚካፈሉ፥ እርሱ ደግሞ በሞት ላይ ሥልጣን ያለውን በሞት እንዲሽር፥ ይኸውም ዲያብሎስ ነው፥ በሕይወታቸውም ሁሉ ስለ ሞት ፍርሃት በባርነት ይታሰሩ የነበሩትን ሁሉ ነጻ እንዲያወጣ፥ በሥጋና በደም እንዲሁ ተካፈለ። የአብርሃምን ዘር ይዞአል እንጂ የያዘው የመላእክትን አይደለም። ስለዚህ የሕዝብን ኃጢአት ለማስተስረይ፥ ለእግዚአብሔር በሆነው ነገር ሁሉ የሚምርና የታመነ ሊቀ ካህናት እንዲሆን፥ በነገር ሁሉ ወንድሞቹን ሊመስል ተገባው።"

                                             (ወደ ዕብራውያን 2፥14-17)

በእርሱ ቅድስና ሊቀድሰን የወደደ ቅዱስ ጌታ፤ በባሕሪይና በዘራችን ተጣብቶ ወደ ውድቀት ሲመራን የነበረውን የገነቱን ጥፋት ሊያጠፋልን፤ ጥፋትን የማያውቅ ሥጋውን እንጀራ አድርጎ በማቅረብ፤ በመብላት እንደወደቅን በመብላት ደሞ ከወደቅንበት እንድንነሣ ራሱን "እንካችሁ" አለን፡፡

   "ሲበሉም ኢየሱስ እንጀራን አንሥቶ ባረከ ቈርሶም ለደቀ መዛሙርቱ ሰጠና። እንካችሁ፥ ብሉ ይህ ሥጋዬ ነው አለ። ጽዋንም አንሥቶ አመስግኖም ሰጣቸው እንዲህም አለ። ሁላችሁ ከእርሱ ጠጡ፤ ስለ ብዙዎች ለኃጢአት ይቅርታ የሚፈስ የአዲስ ኪዳን ደሜ ይህ ነው።"

                                             (የማቴዎስ ወንጌል 26፥26-28)


የምንነጋገርበት ጉዳይ "ስለ ብዙዎች ለኃጢአት ይቅርታ የሚፈስ የአዲስ ኪዳን ደሜ ይህ ነው" የሚለው የመድኃኒቱ የምሕረት ድምፅ ላይ አለ፡፡

ኃጢአት ፈጽመን ከእግዚአብሔር እየራቅን መኖር ከጀመርን በኋላ፤ ስሕተታችንን የምናርምበትን መንገድ ልናገኘው አልቻልንም ነበር፡፡ ይልቁንም ከስሕተት ላይ ሌላ ስሕተት እየደረብን፤ ከዓመፃ ላይ ዓመፃ እየጨመርን፤ ከነባር ኃጢአት ላይ አዲስ ኃጢአት እየፈጸምን፤ ከክፉ መናፍስት ጋር በአንድም በሌላም አቅጣጫ እየተባበርን መኖርን መረጥን፡፡

ይሄ ምርጫችን ደግሞ የእግዚአብሔር ፈቃድ አይደለም፡፡ እርሱ በቀዳማዊው አሳቡ ሲፈጥረን ለዚህ አይነት ሕይወት ፈጽሞ አላሰበንም፡፡ በመጀመሪያ መልካም እንደሆነ ያየልን የስብእና ከፍታ ከሥጋ ፈቃዳችን የተነሣ ወደኛ ሳይመጣ ቀርቶአል፡፡ ይሄ አሳብ ደግሞ ሕያው በሆነ መለኮት የታሰበ ሕያው አሳብ ነውና ከመፈጸም ሊቀር አይችልም፡፡ ስለዚህ ያሰበልንን ሊነግረን በቃሉ በኩል እርሱ ወደኛ መጣ፡፡

የእግዚአብሔር ቃል ወደኛ የመጣው ከጠፋንበት (ከአምላክ ከራቅንበት) ቦታ ያገኘን ዘንድ እንደሆነ እናስታውስ፡፡ የጠፋነው ደግሞ በኃጢአት ነው፡፡ ስለሆነ ከጠፋንበት የምንገኘው ለኃጢአታችን ሥርየት ሲከናወንልን ነው ማለት ነው፡፡ በመሆኑም ፈላጊያችን ቃል ሥጋ (ዘመድ) ሆነና የራቀ ሕልውናችንን ወደርሱ አቀረበው፡፡ በሌላ አነጋገር "ወንድማችን" እስከሆነበት ጥግ ድረስ ከሸሸንበት ጎሬ ገብቶ ሊወዳጀን ፈቀደ፡፡

አዳም ከወደቀበት ስፍራ ላይ በመገኘት አዳምን የሆነው ተወዳጁ፤ የሰውን ባሕሪይ ከወደቀበት አንስቶ ወደ አባቱ መንግሥት ለመመለስ ዋጋ መክፈል ነበረበት (በእርግጥም መነሣት እንጂ መውደቅ ዋጋ አያስከፍልም)፡፡ ይህም ዋጋ እስከ ሞት ድረስ የሚሄድ ታላቅ ዋጋ ነው፡፡ ከሞትም ደግሞ ለከባድ ሕማምና ለከፍተኛ ስቃይ የሚዳርግ ቁስልን የሚጠይቅ ሞት!

     "እርሱ ግን ስለ መተላለፋችን ቈሰለ፥ ስለ በደላችንም ደቀቀ፤ የደኅንነታችንም ተግሣጽ በእርሱ ላይ ነበረ፥ በእርሱም ቍስል እኛ ተፈወስን።"

                                                       (ትንቢተ ኢሳይያስ 53፥5)

እኛ እንገረፈው ዘንድ የተገባ ጅራፍን በጀርባው አስተናገደ፡፡ እኛ እንቀበለው ዘንድ የሚያስፈልግ ድብደባን በሰውነቱ ታገሰ፡፡ እኛ እንሸከመው ዘንድ የተስማማ መከራን በትከሻው አኖረ፡፡ እኛ እንታመመው ዘንድ የታዘዘ ቁስልን እርሱ ተቀበለ፡፡ በብያኔ ደረጃ፤ ቁስል ማለት የሥጋ መቆረስ ማለት ነው ብንል እንችላለን፡፡ እነሆም ስለኛ ስለሁላችን ኃጢአት ሲል አንዱ ክርስቶስ ክቡር ሥጋውን በመስቀል ላይ ቆረሰ፡፡

መድኃኒቱ በመስቀል ላይ ሆኖ መሥዋዕት ከመሆኑ አንድ ዕለት አስቀድሞ፤ ለተማሪዎቹ ሥጋውን እንዲበሉ እንደሰጣቸው በወንጌል ተጽፎልናል፡፡ ይሄ ሥጋ የተቆረሰው ግን በቀጣዩ ዕለት በአርብ ነበር፡፡ እስቲ በቀላል በምሳሌ እንየው፡፡

BY በማለዳ ንቁ ቁጥር ! ፪


Share with your friend now:
tgoop.com/bemaledanek/2383

View MORE
Open in Telegram


Telegram News

Date: |

Invite up to 200 users from your contacts to join your channel A Telegram channel is used for various purposes, from sharing helpful content to implementing a business strategy. In addition, you can use your channel to build and improve your company image, boost your sales, make profits, enhance customer loyalty, and more. Write your hashtags in the language of your target audience. ZDNET RECOMMENDS 4How to customize a Telegram channel?
from us


Telegram በማለዳ ንቁ ቁጥር ! ፪
FROM American