BEMALEDANEK Telegram 2389
በማለዳ ንቁ ቁጥር ! ፪
3•  ቅዱስ ቁርባን ክፍል - ፫       3.2•  ቅዱስ ቁርባን ለምን እንውሰድ ?            3.2.1•  በእግዚአብሔር በኩል                   ✞ ሥርየተ ኃጢአት ✞    "ፍቅርም እንደዚህ ነው፤ እግዚአብሔር እርሱ ራሱ እንደ ወደደን ስለ ኃጢአታችንም ማስተስሪያ ይሆን ዘንድ ልጁን እንደ ላከ እንጂ እኛ እግዚአብሔርን እንደ ወደድነው አይደለም።"                               …
3•  ቅዱስ ቁርባን

ክፍል - ፬

         3.2•  ቅዱስ ቁርባን ለምን እንውሰድ ?

                3.2.1•  በእግዚአብሔር በኩል

                         ✞ ዘላለማዊነት

ሰባተኛዋን ቀን ሳንደርስባት ወድቀናል፡፡ ቀኒቱ እግዚአብሔር ፍጥረታትን ሁሉ ፈጥሮ ያረፈባት ናት፡፡ ፍጹም ሰላምን፣ ዕረፍትን፣ ዘላለማዊነትን ምልክት ታደርጋለች፡፡

አዳም በገነት አንድ ሺሕ ዓመት (አንድ ቀን) ኖሮ ቢጨርስ፤ ወደ አዲሱ ሥርዓት ይገባና ከዕፀ ሕይወት በመብላት ለዘላለማዊ ሕልውና ይታደስ ነበር፡፡ ግን አልሆነም፡፡ አሳች ምክር ሰምቶ ወድቆአል፡፡ ወደ ዕረፍቲቱ ቀን ከመሄድ ይልቅ ወደኋላው ተመልሶ ወደ አንደኛው የዘፍጥረት ቀን ወርዶ ጎስቁሏል፡፡ ከዕፀ ሕይወት ዛፍ እንዳይደርስም ተከልክሎአል፡፡ ዘላለማዊነት ከነፍስ ባሕሪዩ ውስጥ ተደብቆ ቀረ፡፡

"አፈር ነህና ወደ አፈር ትመለሳለህ" የሚልን ትእዛዝ ሰብአዊ ማንነታችን ሰምቶአል፡፡ ከአፈር የተሠራው ሥጋችን ነው፡፡ አፈር ደግሞ የአንደኛው ቀን ፍጥረት ነው፡፡ ስለዚህ ሥጋችን ወደ አንደኛው ቀን፥ ወደኋላው ይገሰግሳል፡፡ ለመሞት እንኖራለን፡፡ ነፍስ ግን የመለኮት እፍታ ናት፡፡ ከማይለወጥ፣ ከማይጠፋ ሕልውና ተከፍላ የተገኘች ናት፡፡ በመሆኑ እርሷም የማትለወጥ፣ የማትጠፋ ዘላለማዊ አካል ናት፡፡ ወደ ሰባተኛው ቀን የመሄድ ፈቃድ በባሕሪይዋ ውስጥ ታትሞአል፡፡ ሥጋ ወደ አንደኛው ቀን፥ ነፍስ ወደ ሰባተኛው ቀን ይጓዛሉ፡፡

መሞትን አንፈልገውም፡፡ ከሞት ለመራቅ ማንኛውም አይነት ዋጋ ለመክፈል እንስማማለን፡፡ ሆኖም ግን እንሞታለን፡፡ አለመሞትን ብንመርጥም፥ አለመሞት አልቻልንም፡፡ ነፍስና ሥጋ ተጣልተውብናል፡፡ ከዕፀ ሕይወት ዛፍ ብንበላ ኖሮ፤ የዘላለማዊነት ኃይል በነፍስና በሥጋችን ላይ ይሠርጽልን ነበር፡፡ ግን ወደ ዛፉ እንዳንደርስ የሚጋርድ ኪሩብ ተሹሞብናል፡፡ ይሄ በባሕሪያችን ሲገለጽ፤ ዘላለማዊነትን ከውስጣችን ብናስሰውም እንዳንደርስበት መንገዱ ተዘግቶብናል፡፡ ወይንም ጠፍቶብናል፡፡ ሥጋ ወደታች ይዞን እየወረደ ከዕረፍቲቱ ቀን አርቆናል፡፡ አዳም (የሰው ልጅ ሁሉ) ወደ ሰባተኛው መግባትና ከፍ ከፍ ማለት አልቻለም፡፡

ወንዱ ልጅ እንደገና ሊወለድ ያስፈልገዋል፡፡ በሌለ አባባል ከወደቀበት ከአንደኛው ቀን ሥርዓት ተነሥቶ ወደ ስድስተኛው ቀን ሥርዓት በመሄድ ከፈረሰበት መሠራት አለበት፡፡ ከዛ በመቀጠል ወደ ሰባተኛው የዕረፍት ቀን መግባት ያስፈልገዋል፡፡ ገና ስንፈጠር ወደዚህ ቀን እንድንደርስ በአምላክ ታስበን ስለሆነ፤ የፈጣሪ ፈቃዱ በባሕሪያችን አለ፡፡ አውቀነውም ሆነ ሳናውቀው ወደ ቀኒቱ ለመድረስ ስንጣጣር እንኖራለን፡፡ ወንዱን ልጅ ለማግኘት እናምጣለን፡፡

አዳምን እንደገና ለመውለድ /የሰውን ልጅ እንደገና ለማደስ/ በባሕሪይ ያማጥንባቸው ዓመታት በክርስትናው አስተምህሮ የብሉይ ኪዳን ዘመናት ይባላሉ፡፡ እነዚያ 5500 ዓመታት ሲፈጸሙ፤ ስድስተኛው ሺሕ ዘመን ላይ ወይንም በዘፈጥረት አገላለጽ በተፈጠርንበት ስድስተኛው ቀን አጋማሽ ላይ (አርብ 6:00) ወንዱ ልጅ ተወለደ፡፡ ፍጹሙ ስብእና፥ አዳም ከጠፋበት ተገኘ፡፡ እነሆ፥ የሰው ልጅ ከመውደቅ የሚነሣበት አዲሱ ዘመን፤ ሐዲስ ኪዳን መጣ!

ኢየሱስ ክርስቶስ ዳግማዊው አዳም ነው፡፡ በእግዚአብሔር ልቦና የተጸነሰው፣ ንጹሑና ቅዱሱ "ሰው' ማለት ነው፡፡ የመጀመሪያው ሰው በእግዚአብሔር ፈቃድ በስድስቱ ቀናት የፍጥረታት ባሕሪይ ድምርነት ተሠርቶ ነበር፡፡ ሆኖም ግን ከፈቃዱ ወጥቶ ፈርሶአል፡፡ እንደገና በእግዚአብሔር ፈቃድ የፈረሰው ባሕሪይ ሲገነባ፤ ሁለተኛው አዳም በስድስቱ ሺሕ ዓመታት በኩል ተሠርቶ ተወለደ፡፡ እናስታውስ! አዳም ወደ ዘላለማዊ ሕልውና እንዲደርሰ ታስቦ ነው የተፈጠረው፡፡ ስለዚህ ሁለተኛው አዳም ዳግም የተወለደው ወደዚህ ወደታሰበልን የዕረፍት ቀን፥ የዘላለም ሕይወት ይዞን እንዲሄድ ነው፡፡ ወይንም ከዕፀ ሕይወት ፍሬ ይሰጠን ዘንድ ነው ወደኛ መጥቶ ባሕሪያችንን የተዋሐደው፡፡ ከዕፀ ሕይወት? እንዴት? .. ውዳሴ ማርያም ዘሐሙስ ፦

      "ከዕፀ ሕይወት እንበላ ዘንድ አደለን። ይኸውም እኛን ስለመውደድ መጥቶ ያዳነን የክርስቶስ ክቡር ሥጋው ክቡር ደሙ ነው"

ወደ ዘላለማዊነት የሚወስደው መንገድ ተዘግቶብን ነበር ብለናል፡፡ ሕያው ሆነን ለመኖር እንዳንችል ከአምላክ ፈቃድ ርቀን ጠፍተናል፡፡ በራሳችን ሕያው ለመሆን በብዙ አይነት መንገዶች እየተጓዝን ብንደክምም፤ ከመቃብር የሚያልፍ ኑሮን ማግኘት አልቻልንም፡፡ ከዚህም የተነሣ ስናስብ፣ ስንፈልግ፣ ስናቅድና ስንሠራ ሞትን መጨረሻ አድርገን ነው፡፡ የእግዚአብሔር ልጅ ወደኛ በመጣ ጊዜ ግን፤ ይሄ እስከ ሞት ድረስ የሚረዝመው ታሪካችን ሊለወጥ ችሏል፡፡ የዘላለማዊነትን ድምፅ ከዘላለም ጌታ አድምጠናል፡፡

       "ሥጋዬን የሚበላ ደሜንም የሚጠጣ የዘላለም ሕይወት አለው፥ እኔም በመጨረሻው ቀን አስነሣዋለሁ።" (ተመስገን!)

                                                       (የዮሐንስ ወንጌል 6፥54)

የዳግማዊው አዳም የሚሞት ሥጋና ደም ከማይሞት የመለኮት ባሕሪይ ጋር የተዋሐደ ነው፡፡ ስለሆነ፤ ሁለተኛው አዳም የማይሞትን ባሕሪይ ተዋሕዶ አለና ከሞት ባሻገር የሚቀጥል ሕልውና አለው፡፡

እኛ ግን የተወለድነው፥ አዳም ከእግዚአብሔር ፈቃድ ከተሰደደ በኋላ ነው፡፡ ማለት፤ የመጀመሪያው ሰው፥ ሞትን በሰማ ባሕሪዩ በኩል ነው ይዋለድ ዘንድ የሆነው፡፡ ስለዚህ ልጆቹ እኛም ሟቾች ነን፡፡ ከሚፈርሰው ሥጋ ተገኝተናልና እንፈርሳለን፡፡

የአምላክ የባሕሪይ ልጅ ታዲያ፤ የሰው ልጆች ሁሉ የሚወለዱበትን የአዳምን ባሕሪይ ሲዋሐደው፤ ከማይጠፋ፣ ከማይሞት መለኮታዊ ባሕሪዩ ጋር አንድ አደረገው፡፡ ይህን ዘላለማዊ ባሕሪይን የተዋሐደ ሥጋውን እና ደሙን መብል አድርጎ ሲሰጠን፤ የኛም ሥጋና ደም ዘላለማዊነትን ያገኝ ዘንድ ሆነለት፡፡ ከዕፅ ሕይወት እንድንበላ አደለን የሚያሰኘው እንግዲህ ይሄ ነው፡፡

የክርስቶስ ሥጋና ደም ስለ ዘላለማዊ ሕልውና ሲባል የተሰጠን ዕፀ ሕይወታችን ነው፡፡ በመብላታችን ምክንያት ከዘላለም ሕይወት (ከሰባተኛው ቀን) እንደተለየን፤ በመብላታችን ምክንያት ወደ ዘላለም ሕይወት እንድንመለስ ቅዱስ ቁርባንን በምሕረቱ ዘመን ተቀብለናል፡፡ ቅዱስ ቁርባን ስለ ዘላለም እውነት፣ ስለ ዘላለም ሰላም፣ ስለ ዘላለም ዕረፍት የምንቀበለው የሕያውነት ኃይል ነው፡፡

ከሚጠፋው አዳም ሥጋና ደም የተወለድን ሰዎች፤ ከማይጠፋው አዳም ሥጋና ደም ስንርቅ፤ የነፍሳችን የዘላለማዊነት ባሕሪይ ከሥጋችን መሠረት ሥር የሚያርፍበትን ስፍራ አጥቶ ኑሮአችን እስከሞት ድረስ በሚዘልቁ ቅጽበቶች ይሞላ ዘንድ ግድ ይሆንበታል፡፡

የዘላለም ሕይወትን የሚያድለው የክርስቶስ ሥጋና ደም ከሰውነትና ከዘመናችን ከተለየ፤ የሚጠብቀን ነገር ቢኖር እንዲሁ ትርኪ ሚርኪ የሆነ በብልጭታ ሁነቶችና በአጋጣሚዎች ላይ የቆመ ጊዜያዊ ኑሮ ነው፡፡ በወረት ቅጽበቶች የላመና ወዲያው ወዲያው የሚለዋወጥ አኗኗር የዛሬዋ ዓለም አገራት ዜጎች ሁሉ የሚጋሩት የአንድነት ገጽታ ሆኗል፡፡

ዓለም፤ በሳይንስ አስተንትኖቷና በቁስ እውቀት ሚዛን ልኬቷ በመስፈር የሕይወትን መርህ ደንግጋ ስታበቃ፤ "ሥጋዬ የተቀበለ ደሜን የተቀበለ ዘላለማዊ ነው" ያለውን ሕያው ቃል በጊዜያዊ ቃላቶች በመለወጥ ሰዎችን ለረጅም ዘመናት ያለማቋረጥ ስለሰበከች፤ የዘመናችን ትውልድ በተለይ ዘላለማዊነት የሚባለውን የሕያውነት አካል ሊያውቀውና ሊኖረው ቀርቶ ትርጉሙ ምን እንደሆነ አይገባውም፡፡



tgoop.com/bemaledanek/2389
Create:
Last Update:

3•  ቅዱስ ቁርባን

ክፍል - ፬

         3.2•  ቅዱስ ቁርባን ለምን እንውሰድ ?

                3.2.1•  በእግዚአብሔር በኩል

                         ✞ ዘላለማዊነት

ሰባተኛዋን ቀን ሳንደርስባት ወድቀናል፡፡ ቀኒቱ እግዚአብሔር ፍጥረታትን ሁሉ ፈጥሮ ያረፈባት ናት፡፡ ፍጹም ሰላምን፣ ዕረፍትን፣ ዘላለማዊነትን ምልክት ታደርጋለች፡፡

አዳም በገነት አንድ ሺሕ ዓመት (አንድ ቀን) ኖሮ ቢጨርስ፤ ወደ አዲሱ ሥርዓት ይገባና ከዕፀ ሕይወት በመብላት ለዘላለማዊ ሕልውና ይታደስ ነበር፡፡ ግን አልሆነም፡፡ አሳች ምክር ሰምቶ ወድቆአል፡፡ ወደ ዕረፍቲቱ ቀን ከመሄድ ይልቅ ወደኋላው ተመልሶ ወደ አንደኛው የዘፍጥረት ቀን ወርዶ ጎስቁሏል፡፡ ከዕፀ ሕይወት ዛፍ እንዳይደርስም ተከልክሎአል፡፡ ዘላለማዊነት ከነፍስ ባሕሪዩ ውስጥ ተደብቆ ቀረ፡፡

"አፈር ነህና ወደ አፈር ትመለሳለህ" የሚልን ትእዛዝ ሰብአዊ ማንነታችን ሰምቶአል፡፡ ከአፈር የተሠራው ሥጋችን ነው፡፡ አፈር ደግሞ የአንደኛው ቀን ፍጥረት ነው፡፡ ስለዚህ ሥጋችን ወደ አንደኛው ቀን፥ ወደኋላው ይገሰግሳል፡፡ ለመሞት እንኖራለን፡፡ ነፍስ ግን የመለኮት እፍታ ናት፡፡ ከማይለወጥ፣ ከማይጠፋ ሕልውና ተከፍላ የተገኘች ናት፡፡ በመሆኑ እርሷም የማትለወጥ፣ የማትጠፋ ዘላለማዊ አካል ናት፡፡ ወደ ሰባተኛው ቀን የመሄድ ፈቃድ በባሕሪይዋ ውስጥ ታትሞአል፡፡ ሥጋ ወደ አንደኛው ቀን፥ ነፍስ ወደ ሰባተኛው ቀን ይጓዛሉ፡፡

መሞትን አንፈልገውም፡፡ ከሞት ለመራቅ ማንኛውም አይነት ዋጋ ለመክፈል እንስማማለን፡፡ ሆኖም ግን እንሞታለን፡፡ አለመሞትን ብንመርጥም፥ አለመሞት አልቻልንም፡፡ ነፍስና ሥጋ ተጣልተውብናል፡፡ ከዕፀ ሕይወት ዛፍ ብንበላ ኖሮ፤ የዘላለማዊነት ኃይል በነፍስና በሥጋችን ላይ ይሠርጽልን ነበር፡፡ ግን ወደ ዛፉ እንዳንደርስ የሚጋርድ ኪሩብ ተሹሞብናል፡፡ ይሄ በባሕሪያችን ሲገለጽ፤ ዘላለማዊነትን ከውስጣችን ብናስሰውም እንዳንደርስበት መንገዱ ተዘግቶብናል፡፡ ወይንም ጠፍቶብናል፡፡ ሥጋ ወደታች ይዞን እየወረደ ከዕረፍቲቱ ቀን አርቆናል፡፡ አዳም (የሰው ልጅ ሁሉ) ወደ ሰባተኛው መግባትና ከፍ ከፍ ማለት አልቻለም፡፡

ወንዱ ልጅ እንደገና ሊወለድ ያስፈልገዋል፡፡ በሌለ አባባል ከወደቀበት ከአንደኛው ቀን ሥርዓት ተነሥቶ ወደ ስድስተኛው ቀን ሥርዓት በመሄድ ከፈረሰበት መሠራት አለበት፡፡ ከዛ በመቀጠል ወደ ሰባተኛው የዕረፍት ቀን መግባት ያስፈልገዋል፡፡ ገና ስንፈጠር ወደዚህ ቀን እንድንደርስ በአምላክ ታስበን ስለሆነ፤ የፈጣሪ ፈቃዱ በባሕሪያችን አለ፡፡ አውቀነውም ሆነ ሳናውቀው ወደ ቀኒቱ ለመድረስ ስንጣጣር እንኖራለን፡፡ ወንዱን ልጅ ለማግኘት እናምጣለን፡፡

አዳምን እንደገና ለመውለድ /የሰውን ልጅ እንደገና ለማደስ/ በባሕሪይ ያማጥንባቸው ዓመታት በክርስትናው አስተምህሮ የብሉይ ኪዳን ዘመናት ይባላሉ፡፡ እነዚያ 5500 ዓመታት ሲፈጸሙ፤ ስድስተኛው ሺሕ ዘመን ላይ ወይንም በዘፈጥረት አገላለጽ በተፈጠርንበት ስድስተኛው ቀን አጋማሽ ላይ (አርብ 6:00) ወንዱ ልጅ ተወለደ፡፡ ፍጹሙ ስብእና፥ አዳም ከጠፋበት ተገኘ፡፡ እነሆ፥ የሰው ልጅ ከመውደቅ የሚነሣበት አዲሱ ዘመን፤ ሐዲስ ኪዳን መጣ!

ኢየሱስ ክርስቶስ ዳግማዊው አዳም ነው፡፡ በእግዚአብሔር ልቦና የተጸነሰው፣ ንጹሑና ቅዱሱ "ሰው' ማለት ነው፡፡ የመጀመሪያው ሰው በእግዚአብሔር ፈቃድ በስድስቱ ቀናት የፍጥረታት ባሕሪይ ድምርነት ተሠርቶ ነበር፡፡ ሆኖም ግን ከፈቃዱ ወጥቶ ፈርሶአል፡፡ እንደገና በእግዚአብሔር ፈቃድ የፈረሰው ባሕሪይ ሲገነባ፤ ሁለተኛው አዳም በስድስቱ ሺሕ ዓመታት በኩል ተሠርቶ ተወለደ፡፡ እናስታውስ! አዳም ወደ ዘላለማዊ ሕልውና እንዲደርሰ ታስቦ ነው የተፈጠረው፡፡ ስለዚህ ሁለተኛው አዳም ዳግም የተወለደው ወደዚህ ወደታሰበልን የዕረፍት ቀን፥ የዘላለም ሕይወት ይዞን እንዲሄድ ነው፡፡ ወይንም ከዕፀ ሕይወት ፍሬ ይሰጠን ዘንድ ነው ወደኛ መጥቶ ባሕሪያችንን የተዋሐደው፡፡ ከዕፀ ሕይወት? እንዴት? .. ውዳሴ ማርያም ዘሐሙስ ፦

      "ከዕፀ ሕይወት እንበላ ዘንድ አደለን። ይኸውም እኛን ስለመውደድ መጥቶ ያዳነን የክርስቶስ ክቡር ሥጋው ክቡር ደሙ ነው"

ወደ ዘላለማዊነት የሚወስደው መንገድ ተዘግቶብን ነበር ብለናል፡፡ ሕያው ሆነን ለመኖር እንዳንችል ከአምላክ ፈቃድ ርቀን ጠፍተናል፡፡ በራሳችን ሕያው ለመሆን በብዙ አይነት መንገዶች እየተጓዝን ብንደክምም፤ ከመቃብር የሚያልፍ ኑሮን ማግኘት አልቻልንም፡፡ ከዚህም የተነሣ ስናስብ፣ ስንፈልግ፣ ስናቅድና ስንሠራ ሞትን መጨረሻ አድርገን ነው፡፡ የእግዚአብሔር ልጅ ወደኛ በመጣ ጊዜ ግን፤ ይሄ እስከ ሞት ድረስ የሚረዝመው ታሪካችን ሊለወጥ ችሏል፡፡ የዘላለማዊነትን ድምፅ ከዘላለም ጌታ አድምጠናል፡፡

       "ሥጋዬን የሚበላ ደሜንም የሚጠጣ የዘላለም ሕይወት አለው፥ እኔም በመጨረሻው ቀን አስነሣዋለሁ።" (ተመስገን!)

                                                       (የዮሐንስ ወንጌል 6፥54)

የዳግማዊው አዳም የሚሞት ሥጋና ደም ከማይሞት የመለኮት ባሕሪይ ጋር የተዋሐደ ነው፡፡ ስለሆነ፤ ሁለተኛው አዳም የማይሞትን ባሕሪይ ተዋሕዶ አለና ከሞት ባሻገር የሚቀጥል ሕልውና አለው፡፡

እኛ ግን የተወለድነው፥ አዳም ከእግዚአብሔር ፈቃድ ከተሰደደ በኋላ ነው፡፡ ማለት፤ የመጀመሪያው ሰው፥ ሞትን በሰማ ባሕሪዩ በኩል ነው ይዋለድ ዘንድ የሆነው፡፡ ስለዚህ ልጆቹ እኛም ሟቾች ነን፡፡ ከሚፈርሰው ሥጋ ተገኝተናልና እንፈርሳለን፡፡

የአምላክ የባሕሪይ ልጅ ታዲያ፤ የሰው ልጆች ሁሉ የሚወለዱበትን የአዳምን ባሕሪይ ሲዋሐደው፤ ከማይጠፋ፣ ከማይሞት መለኮታዊ ባሕሪዩ ጋር አንድ አደረገው፡፡ ይህን ዘላለማዊ ባሕሪይን የተዋሐደ ሥጋውን እና ደሙን መብል አድርጎ ሲሰጠን፤ የኛም ሥጋና ደም ዘላለማዊነትን ያገኝ ዘንድ ሆነለት፡፡ ከዕፅ ሕይወት እንድንበላ አደለን የሚያሰኘው እንግዲህ ይሄ ነው፡፡

የክርስቶስ ሥጋና ደም ስለ ዘላለማዊ ሕልውና ሲባል የተሰጠን ዕፀ ሕይወታችን ነው፡፡ በመብላታችን ምክንያት ከዘላለም ሕይወት (ከሰባተኛው ቀን) እንደተለየን፤ በመብላታችን ምክንያት ወደ ዘላለም ሕይወት እንድንመለስ ቅዱስ ቁርባንን በምሕረቱ ዘመን ተቀብለናል፡፡ ቅዱስ ቁርባን ስለ ዘላለም እውነት፣ ስለ ዘላለም ሰላም፣ ስለ ዘላለም ዕረፍት የምንቀበለው የሕያውነት ኃይል ነው፡፡

ከሚጠፋው አዳም ሥጋና ደም የተወለድን ሰዎች፤ ከማይጠፋው አዳም ሥጋና ደም ስንርቅ፤ የነፍሳችን የዘላለማዊነት ባሕሪይ ከሥጋችን መሠረት ሥር የሚያርፍበትን ስፍራ አጥቶ ኑሮአችን እስከሞት ድረስ በሚዘልቁ ቅጽበቶች ይሞላ ዘንድ ግድ ይሆንበታል፡፡

የዘላለም ሕይወትን የሚያድለው የክርስቶስ ሥጋና ደም ከሰውነትና ከዘመናችን ከተለየ፤ የሚጠብቀን ነገር ቢኖር እንዲሁ ትርኪ ሚርኪ የሆነ በብልጭታ ሁነቶችና በአጋጣሚዎች ላይ የቆመ ጊዜያዊ ኑሮ ነው፡፡ በወረት ቅጽበቶች የላመና ወዲያው ወዲያው የሚለዋወጥ አኗኗር የዛሬዋ ዓለም አገራት ዜጎች ሁሉ የሚጋሩት የአንድነት ገጽታ ሆኗል፡፡

ዓለም፤ በሳይንስ አስተንትኖቷና በቁስ እውቀት ሚዛን ልኬቷ በመስፈር የሕይወትን መርህ ደንግጋ ስታበቃ፤ "ሥጋዬ የተቀበለ ደሜን የተቀበለ ዘላለማዊ ነው" ያለውን ሕያው ቃል በጊዜያዊ ቃላቶች በመለወጥ ሰዎችን ለረጅም ዘመናት ያለማቋረጥ ስለሰበከች፤ የዘመናችን ትውልድ በተለይ ዘላለማዊነት የሚባለውን የሕያውነት አካል ሊያውቀውና ሊኖረው ቀርቶ ትርጉሙ ምን እንደሆነ አይገባውም፡፡

BY በማለዳ ንቁ ቁጥር ! ፪


Share with your friend now:
tgoop.com/bemaledanek/2389

View MORE
Open in Telegram


Telegram News

Date: |

Users are more open to new information on workdays rather than weekends. Telegram message that reads: "Bear Market Screaming Therapy Group. You are only allowed to send screaming voice notes. Everything else = BAN. Text pics, videos, stickers, gif = BAN. Anything other than screaming = BAN. You think you are smart = BAN. The optimal dimension of the avatar on Telegram is 512px by 512px, and it’s recommended to use PNG format to deliver an unpixelated avatar. Developing social channels based on exchanging a single message isn’t exactly new, of course. Back in 2014, the “Yo” app was launched with the sole purpose of enabling users to send each other the greeting “Yo.” ZDNET RECOMMENDS
from us


Telegram በማለዳ ንቁ ቁጥር ! ፪
FROM American