BEMALEDANEK Telegram 2391
ስንጀምረው ተፈጥሮ ለኛ ትሠራ ዘንድ ነበረ የተፈጠረቺው፡፡ መጽሐፈ ኢያሱ ምዕራፍ 10'ን ስናይ፤ ኢያሱ በእግዚአብሔር ፊት ፀሐይን በገባዖን ምድር አቁሟታል፡፡ ጨረቃንም አዘግይቷታል፡፡ እኛ አሁን እግዚአብሔር ፊት መቆም ስላቃተን ለተፈጥሮ ብቻ ለመሥራት ተገድደናል፡፡ አልፎም ተርፎ አንዳንዴ ተፈጥሮ ስትከዳን ለመኖራችን አደጋም ጭምር ታመጣብናለች፡፡ የእግዚአብሔር ሕዝቦች ባሕር ከፍለው ተሻገሩ የሚለውን ታሪክ ክርስቲያኖች በመጽሐፍ ቅዱሳቸው ይዘው፤ ዛሬ ከአገር ሊወጡ ሲሹለከለኩ፣ እንደ ዕቃ ሲጫኑ ሲወርዱ፤ ባሕር ደርምሷቸው ስንቶች የዓሳ እራት ሆነው እንደቀሩ ቤቱ ይቁጠረው፡፡ በተፈጥሮ አደጋ ምክንያት ስንቶች አለቁ? መሬት ሲንሸራተት የስንት ሰዎች ሕይወት አብሮ ተንሸራተተ? የጎርፍ ውኃ ስንቶችን እያላተመ ወሰደ? የእሳት ሰደድ የስንቶችን ሕይወትና ኑሮ አነደደ? የአውሎ ነፋስ ወጀብ ስንቶችን ለሥርዓተ ቀብር አስክሬናቸው እንኳ እንዳይገኝ አርቆ ቀበረ?

እግዚአብሔር የሌለው የሰው ልጅ በተፈጥሮ ሥር ነው፡፡ አሁን በዚህ በምዕራባውያኑ እና ሩቅ ምሥራቃውያኑ ውስጥ ያሉ አገሮች ከአሁን አሁን መሬት ከዳችን እያሉ ከሚመጣው አደጋና ሰቆቃ ለመትረፍ ቤት ሲሠሩ፣ መንገድ ሲገነቡ፣ ኢንደስትሪ ሲተክሉ የተፈጥሮ አደጋን መቋቋም እንዲችል አድርገው ነው፡፡ ለዘመናትም በዚህ የተፈጥሮ ግብ ግብ መካከል የኖሩ ዜጎችም ተፈጥሮን እየፈሩ፣ ተፈጥሮን ባለማመን እየጠበቁ፣ ተፈጥሮን አጨንቁረው እያዩ ይኖራሉ፡፡

በዘመነ ፍዳ የዲያቢሎስ ክንድና አገዛዙ ሰልጥኖ ከሕግ በታች አድርጎ የሰው ልጆችን በዘር ጉዳትና ውድቀት ውስጥ አስሮ፤ ስጦታችንን ሲፋለም የኖረበትን ዘመን ወደ ምሕረት ሊለውጠው እግዚአብሔር ቃል ፍቅር ይዞት ሥጋ ሆነና ጸጋንና እውነትን ተመልቶ ወደ ጊዜና ወደ ሕይወታችን መጣ፡፡ ሲመጣ ከሰጠን ታላላቅ ሰማያዊ በረከቶች መካከል አንደኛው ንጹሕ ሥጋውና ቅዱስ ደሙ ነው፡፡

ታዲያ ይሄን ክቡር ሥጋና ደም ስንቀበል ተፈጥሮን ማገልገላችን ይቀርና ተፈጥሮ እኛን ለማገልገል ወደ ኑሮአችን ትታዘዛለች፡፡ ምክንያቱም የመጀመሪያውን ንጹሑን የአዳም ስብእና እያገኘነው እያገኘነው ስለምንሄድ፤ በነፍስ ወረቀታችን ላይ የተጻፈው ተፈጥሮን የማዘዝ ሥልጣን መገለጥ ይጀምራል፡፡ እነሆ፥ ተፈጥሮ ላንተ እንድትስማማ የክርስቶስ ሥጋና ደም ያስፈልግሃል፡፡ "የሰማይ አባታችን ሆይ፥ ለአዳም የሰጠኸውን ቀዳሚ ጸጋና ሞገስ እንዲሁ በኔ ሕይወትም ስጠኝ፡፡ ጊዜና ዘመን እንዳይገዛኝ የሕይወቴን መግቢያ መውጪያ ተቆጣጠረው፡፡ የመኖርን ሚስጢር ከሰማያዊ ስጦታዎችህ ጋር ግለጥልኝ፡፡ የዕረፍቲቱን ቀን ኃይል በባሕሪዬ ውስጥ አኑርልኝ፡፡ ሕያው እውነትህ በኑሮዬ ውስጥ ይጀምር" እያልክ ቅዱስ ቁርባን ስትወስድ ..  ያን ጊዜ የተፈጥሮ ባለቤት መሆን ትጀምራለህ፡፡ ጊዜ አንተ ስለለፋህ ብቻ ሳይሆን ጊዜው አንተን ሊያግዝህ የማያቋርጡ ዕድሎችን እየያዘ ወዳንተ ይመጣል፡፡ ሁኔታዎች አንተ ስለተጨነቅላቸው ሳይሆን ሁኔታዎች ላንተ ሊጨነቁልህ ወዳንተ ይገሰግሳሉ፡፡ በረከት አንተ ስለደከምክለት ብቻ ሳይሆን፤ ስለወጣህ ስለወረድክለት ሳይሆን፤ በረከት ካንተ ጋር ለመሆን ወዳንተ ይመጣል፡፡ የሚደግፉህና የሚያበረቱህ ልበ ቀና ሰዎች ሳትጠራቸው ወዳንተ ይመጣሉ፡፡ የሚያስፈልግህን ሁሉ በጊዜ ጊዜው እንድትሰጥህ ተፈጥሮ ከሰማይ አምላካችን ትእዛዝ ትቀበላለች፡፡ ከዛ በኋላ ሰውና ዲያቢሎስ የቱንም ደረጃ ያህል ቢሮጡ አይቀድሙህም፡፡ ክፉዎች የዘጉት በር ሁሉ እየተከፈተ፥ የከፈቱትም ሁሉ እየተዘጋ፤ የበረከትና የሰላም ገባር ወንዞች ወዳንተ የሕይወት ወንዝ ያለማቋረጥ እየመጡ ይቀላቀላሉ፡፡ የእግዚአብሔር ስሙ የተመሰገነ ይሁን

ይሄ የሚሆነው ግን በመጀመሪያው አቋም ሲኖረን ነው፡፡ በተሰበረ ልብና የእውነት ፍቅር ወደ እግዚአብሔር የመጠጋት ቁርጠኝነት ሲኖረን ነው፡፡ በቅዱስ ቁርባኑ በመቀደስ ከውስጥም ከውጪም የዘላለማዊነትን ቅርጽና ገጽታ መያዝ ስንጀምር ተፈጥሮ ለአዳም እንደታዘዘቺውና እንዲጠብቃትም እንደተሰጠቺው ወዳንተ እርዳታዎችን ልታደርግልህ ትመጣለች፡፡ የዛሬው ትውልድ ተፈጥሮ የሸሸቺው ትውልድ ነው፡፡ ዓለም ሲደነግጥ አብሮ የሚደነግጥ፣ ዓለም ሲፈራ አብሮ የሚፈራ፣ ዓለም ሲሸወድ አብሮ የሚሸወድ ትውልድ ነው፡፡ ስለዚህ የሕይወት ምሪቱንና የራእይ መረጃዎቹን ከቴሌቪዥን፣ ከኢንተርኔት፣ ከጋዜጣና ከመገናኛ አውታሮች ብቻ የሚጠብቅ እየሆነ፤ ዜናዎች ሲጨክኑ እየተሳቀቀ፣ ዜናዎች ሲያበስሩ እየፈነጠዘ፣ ዜናዎች ሲወሳሰቡ ግራ እየተጋባ የሚኖር ሆኖ ይገኛል፡፡

ወደ ሥጋና ደሙ መጓዛችንን እንቀጥላለን. . .
#ጸባኦት_ይከተላችሁ
@bemaledanek



tgoop.com/bemaledanek/2391
Create:
Last Update:

ስንጀምረው ተፈጥሮ ለኛ ትሠራ ዘንድ ነበረ የተፈጠረቺው፡፡ መጽሐፈ ኢያሱ ምዕራፍ 10'ን ስናይ፤ ኢያሱ በእግዚአብሔር ፊት ፀሐይን በገባዖን ምድር አቁሟታል፡፡ ጨረቃንም አዘግይቷታል፡፡ እኛ አሁን እግዚአብሔር ፊት መቆም ስላቃተን ለተፈጥሮ ብቻ ለመሥራት ተገድደናል፡፡ አልፎም ተርፎ አንዳንዴ ተፈጥሮ ስትከዳን ለመኖራችን አደጋም ጭምር ታመጣብናለች፡፡ የእግዚአብሔር ሕዝቦች ባሕር ከፍለው ተሻገሩ የሚለውን ታሪክ ክርስቲያኖች በመጽሐፍ ቅዱሳቸው ይዘው፤ ዛሬ ከአገር ሊወጡ ሲሹለከለኩ፣ እንደ ዕቃ ሲጫኑ ሲወርዱ፤ ባሕር ደርምሷቸው ስንቶች የዓሳ እራት ሆነው እንደቀሩ ቤቱ ይቁጠረው፡፡ በተፈጥሮ አደጋ ምክንያት ስንቶች አለቁ? መሬት ሲንሸራተት የስንት ሰዎች ሕይወት አብሮ ተንሸራተተ? የጎርፍ ውኃ ስንቶችን እያላተመ ወሰደ? የእሳት ሰደድ የስንቶችን ሕይወትና ኑሮ አነደደ? የአውሎ ነፋስ ወጀብ ስንቶችን ለሥርዓተ ቀብር አስክሬናቸው እንኳ እንዳይገኝ አርቆ ቀበረ?

እግዚአብሔር የሌለው የሰው ልጅ በተፈጥሮ ሥር ነው፡፡ አሁን በዚህ በምዕራባውያኑ እና ሩቅ ምሥራቃውያኑ ውስጥ ያሉ አገሮች ከአሁን አሁን መሬት ከዳችን እያሉ ከሚመጣው አደጋና ሰቆቃ ለመትረፍ ቤት ሲሠሩ፣ መንገድ ሲገነቡ፣ ኢንደስትሪ ሲተክሉ የተፈጥሮ አደጋን መቋቋም እንዲችል አድርገው ነው፡፡ ለዘመናትም በዚህ የተፈጥሮ ግብ ግብ መካከል የኖሩ ዜጎችም ተፈጥሮን እየፈሩ፣ ተፈጥሮን ባለማመን እየጠበቁ፣ ተፈጥሮን አጨንቁረው እያዩ ይኖራሉ፡፡

በዘመነ ፍዳ የዲያቢሎስ ክንድና አገዛዙ ሰልጥኖ ከሕግ በታች አድርጎ የሰው ልጆችን በዘር ጉዳትና ውድቀት ውስጥ አስሮ፤ ስጦታችንን ሲፋለም የኖረበትን ዘመን ወደ ምሕረት ሊለውጠው እግዚአብሔር ቃል ፍቅር ይዞት ሥጋ ሆነና ጸጋንና እውነትን ተመልቶ ወደ ጊዜና ወደ ሕይወታችን መጣ፡፡ ሲመጣ ከሰጠን ታላላቅ ሰማያዊ በረከቶች መካከል አንደኛው ንጹሕ ሥጋውና ቅዱስ ደሙ ነው፡፡

ታዲያ ይሄን ክቡር ሥጋና ደም ስንቀበል ተፈጥሮን ማገልገላችን ይቀርና ተፈጥሮ እኛን ለማገልገል ወደ ኑሮአችን ትታዘዛለች፡፡ ምክንያቱም የመጀመሪያውን ንጹሑን የአዳም ስብእና እያገኘነው እያገኘነው ስለምንሄድ፤ በነፍስ ወረቀታችን ላይ የተጻፈው ተፈጥሮን የማዘዝ ሥልጣን መገለጥ ይጀምራል፡፡ እነሆ፥ ተፈጥሮ ላንተ እንድትስማማ የክርስቶስ ሥጋና ደም ያስፈልግሃል፡፡ "የሰማይ አባታችን ሆይ፥ ለአዳም የሰጠኸውን ቀዳሚ ጸጋና ሞገስ እንዲሁ በኔ ሕይወትም ስጠኝ፡፡ ጊዜና ዘመን እንዳይገዛኝ የሕይወቴን መግቢያ መውጪያ ተቆጣጠረው፡፡ የመኖርን ሚስጢር ከሰማያዊ ስጦታዎችህ ጋር ግለጥልኝ፡፡ የዕረፍቲቱን ቀን ኃይል በባሕሪዬ ውስጥ አኑርልኝ፡፡ ሕያው እውነትህ በኑሮዬ ውስጥ ይጀምር" እያልክ ቅዱስ ቁርባን ስትወስድ ..  ያን ጊዜ የተፈጥሮ ባለቤት መሆን ትጀምራለህ፡፡ ጊዜ አንተ ስለለፋህ ብቻ ሳይሆን ጊዜው አንተን ሊያግዝህ የማያቋርጡ ዕድሎችን እየያዘ ወዳንተ ይመጣል፡፡ ሁኔታዎች አንተ ስለተጨነቅላቸው ሳይሆን ሁኔታዎች ላንተ ሊጨነቁልህ ወዳንተ ይገሰግሳሉ፡፡ በረከት አንተ ስለደከምክለት ብቻ ሳይሆን፤ ስለወጣህ ስለወረድክለት ሳይሆን፤ በረከት ካንተ ጋር ለመሆን ወዳንተ ይመጣል፡፡ የሚደግፉህና የሚያበረቱህ ልበ ቀና ሰዎች ሳትጠራቸው ወዳንተ ይመጣሉ፡፡ የሚያስፈልግህን ሁሉ በጊዜ ጊዜው እንድትሰጥህ ተፈጥሮ ከሰማይ አምላካችን ትእዛዝ ትቀበላለች፡፡ ከዛ በኋላ ሰውና ዲያቢሎስ የቱንም ደረጃ ያህል ቢሮጡ አይቀድሙህም፡፡ ክፉዎች የዘጉት በር ሁሉ እየተከፈተ፥ የከፈቱትም ሁሉ እየተዘጋ፤ የበረከትና የሰላም ገባር ወንዞች ወዳንተ የሕይወት ወንዝ ያለማቋረጥ እየመጡ ይቀላቀላሉ፡፡ የእግዚአብሔር ስሙ የተመሰገነ ይሁን

ይሄ የሚሆነው ግን በመጀመሪያው አቋም ሲኖረን ነው፡፡ በተሰበረ ልብና የእውነት ፍቅር ወደ እግዚአብሔር የመጠጋት ቁርጠኝነት ሲኖረን ነው፡፡ በቅዱስ ቁርባኑ በመቀደስ ከውስጥም ከውጪም የዘላለማዊነትን ቅርጽና ገጽታ መያዝ ስንጀምር ተፈጥሮ ለአዳም እንደታዘዘቺውና እንዲጠብቃትም እንደተሰጠቺው ወዳንተ እርዳታዎችን ልታደርግልህ ትመጣለች፡፡ የዛሬው ትውልድ ተፈጥሮ የሸሸቺው ትውልድ ነው፡፡ ዓለም ሲደነግጥ አብሮ የሚደነግጥ፣ ዓለም ሲፈራ አብሮ የሚፈራ፣ ዓለም ሲሸወድ አብሮ የሚሸወድ ትውልድ ነው፡፡ ስለዚህ የሕይወት ምሪቱንና የራእይ መረጃዎቹን ከቴሌቪዥን፣ ከኢንተርኔት፣ ከጋዜጣና ከመገናኛ አውታሮች ብቻ የሚጠብቅ እየሆነ፤ ዜናዎች ሲጨክኑ እየተሳቀቀ፣ ዜናዎች ሲያበስሩ እየፈነጠዘ፣ ዜናዎች ሲወሳሰቡ ግራ እየተጋባ የሚኖር ሆኖ ይገኛል፡፡

ወደ ሥጋና ደሙ መጓዛችንን እንቀጥላለን. . .
#ጸባኦት_ይከተላችሁ
@bemaledanek

BY በማለዳ ንቁ ቁጥር ! ፪


Share with your friend now:
tgoop.com/bemaledanek/2391

View MORE
Open in Telegram


Telegram News

Date: |

In the next window, choose the type of your channel. If you want your channel to be public, you need to develop a link for it. In the screenshot below, it’s ”/catmarketing.” If your selected link is unavailable, you’ll need to suggest another option. With Bitcoin down 30% in the past week, some crypto traders have taken to Telegram to “voice” their feelings. “[The defendant] could not shift his criminal liability,” Hui said. Clear During the meeting with TSE Minister Edson Fachin, Perekopsky also mentioned the TSE channel on the platform as one of the firm's key success stories. Launched as part of the company's commitments to tackle the spread of fake news in Brazil, the verified channel has attracted more than 184,000 members in less than a month.
from us


Telegram በማለዳ ንቁ ቁጥር ! ፪
FROM American