BEMALEDANEK Telegram 2398
በቁጥር እጅግ ብዙ የሚባል ሰው፤ የሕይወት ጎዳናውን በራሱ የባለቤትነት ሥልጣን ተቆጣጥሮ በመኖር መንገዱ ላይ በውሳኔ እርምጃ ሲጓዝ አይታይም፡፡ ሰዎች በውስጣቸው ሌሎች ሰዎች ደባል ሆነው የሚኖሩ ያህል፤ በተቃራኒ ፍላጎቶች ሲንገላቱ፣ በተለያዩ ስሜቶች ሲዋዥቁ፣ በተሰበጣጠሩ አሳቦች ሲምታቱ፣ ባልተናበቡ እቅዶች ሲንከላወሱ፣ በሚነቃቀፉ ምግባሮች ሲደናገሩ፣ በሚለዋወጡ ጠባዮች ሲገለጡ ይስተዋላሉ፡፡ አንዳንዴሞ በተራራቁ የዋልታ ጥጎች ላይ በቆሙ ማንነቶች ከራሳቸው ጋር ክፉኛ እየተጋጩ፤ የኑሮ ገጠመኝ ባደረሳቸው ቦታ ላይ እንዴት እንደደረሱ ሳያውቁትና ሳይገነዘቡት ያለ'መኖርን ቀን እየቆጠሩ የሚኖሩ ጥቂት የማይባሉ ሰዎች አሉ፡፡ ነብዩ ምን አለ? .. "የሰው አካሄዱ ከራሱ ጋር እንዳይደለ አውቃለሁ"፡፡ ከራሱ ካልሆነ ታዲያ ከማን ጋር ነው?

ዲያቢሎስ ኃጢአት መፈጸማችንን ተከትሎ የመጣብን የውስጥ መደበላለቅ ውድቀታችን ላይ ይመካል፡፡ አንድ መሆን ያቃታቸው ውስጣዊ መገለጫዎቻችንን እንደ ጥሩ ዕድልና መሣሪያ በመጠቀም፤ የአእምሮ ሹክሹክታዎችን ከእኛ ለእኛ በማስደመጥ፣ በስሜት ግፊቶች ጀርባ ሆኖ ስሜቶችን በማዘባረቅ፣ ጠባያት በወጥነት መልክና ቅርጽ ተገኝተው የሰከነ ሁለንተና እንዳንይዝ የራሱን ጠባያት በተጻፉብን ባሕሪያቶቻችን በኩል በመግለጥ፣ ፍላጎትና የአኗኗር ዘይቤዎችን ተጋርቶ መስመር በማስለወጥ፣ ፍቃድና ውሳኔን ከፊት ቀድሞ በመምራትና ከኋላ ተከትሎ በመቆጣጠር፤ አካሄዳችን ከእግዚአብሔር ጋር ሳይሆን ከእርሱ ጋር እንዲሆን አድርጎ ወደ ወደደው መድረሻ በዝግታም በፍጥነትም ይመራናል፡፡ /አካሄዳችን ከእግዚአብሔር ጋር ሲሆን እንደ ኖኅ ከራሳችን ጋር አንድ እንሆናለን/

በዚህ ስለዚህ፤ አንዳንዶቻችን የአመላችን በተደጋጋሚ መቀያየርና አንዳች የጸና አቋም አለመያዝ ገርሞን እንዲሁ ራሳችንን እየታዘብን ተቀምጠናል፡፡ አንዳንዶቻችን የእኛነት መገለጫ አንድ ክፍል እንደሆነ አድርገን ተቀብለነው ከጊዜያዊ ሁነቶች ጋር ተሳስረን ከቅጽበት ጋር እንደ ቅጽበት የምንመላለስ ሰዎች ሆነናል፡፡ አንዳንዶቻችን ከራሳችን ጠባያትና አልረጋጋ የሚሉ ስሜቶች ጋር የግብግብ እልህ ተያይዘን፤ አንድ መሠረታዊ ገጽታ ያለው ማንነት ለመያዝ የምናደርገው ጥረት በተደጋጋሚ እየከሸፈ ግራ ሲያጋባን፤ ተስፋ ባለመቁረጥና በመቁረጥ መካከል ስንዋትት እንገኛለን፡፡ አንዳንዶቻችን ደግሞ፤ ከላይ የተገለጹትን አይነት ሰዎች ሁሉ በመሆን፤ አንዳንድ ቀን ራሳችንን የምንታዘብ፣ አንዳንድ ቀን እንደ ልዩ ማንነታችን የምንቀበል፣ በሌላ ቀን ከራሳችን ጋር የምንጣላና የምንፋለም ቀለም አልባ ሰዎች በመሆን እየተዘበራረቅን ዕድሜያችንን ቀጥለናል፡፡
 
ይሄ የጋራ ሐቃችን ሆኖ ሳለ፤ የሰው ልጅ የውስጣዊ ማንነት መተረማመረስና አልጨበጥ ማለት ከመንፈሳዊው ዓለም ጋር በቀጥታ እንደሚያያዝ፤ የክፉ መናፍስት አንዱ የውጊያ አዝመራ ስለመሆኑም፤ በጣም ለብዙዎቻችን ገና ሊገባን እንኳ አልጀመረም፡፡ ምክንያቱም ርኩሳን መናፍስት ዓላማቸውን ለማስፈጸም የሚሄዱበትን ሚስጢራዊ አካሄድ፣ ከሰው ልጆች ሕይወት ጋር ያላቸው ጥብቅ ትስስር፣ የማጥፋት አሠራር ጥበባቸውን እና ወደ ግባቸው ለመድረስ የሚጓዙበትን ሂደት፤ በሚገባ ለመገንዘብ የምናሳየው መሻት አነስተኛ በመሆኑ፤ ስውራኑ አጥቂዎቻችን በቸልተኝነታችን በኩል የተቀዳጁትን ኃይል የበለጠ ከዘመን ዘመን እያጠነከሩ፤ የእስራት ገመዳቸውን በማጥበቅ የሰብአዊነት ሕልውና ከምድረ ገጽ እንዲጠፋ በብርቱ እየሠሩ ይገኛሉ፡፡
 
በአንድ ሰው ውስጥ ብዙ እርስ በእርስ የሚጋጩ ማንነቶች ሊከሰቱ የቻሉት፤ ከላይ ባስቀመጥነው የአዳም ታሪክ ውስጥ በተፈጠረው ከእግዚአብሔር ፈቃድ አፈንግጦ የመውጣት ስሕተትነት እንደሆነ አንስተናል፡፡ በዚህ ጥፋታችን ላይም በመመካት ዲያቢሎስ ውሳጣዊ አንድነት እንዳናገኝ በተለያዩ ረቂቅ መንገዶች ተጠቅሞ እንደሚፋለም በአጭሩ ዳስሰናል፡፡ የበለጠ ግልጽ እይታ እንዲኖረን እነዚህን መንገዶቹን በሦስት ጎራዎች ከፍለን እንመልከታቸው፡፡
 
              ሀ] ሰው እና ሰው ውስጥ ያለ መንፈሱ ሲጋጩ
 
የአብዛኞቻችን የተለመደ ችግር ነው፡፡ ከውስጥ ተቃራኒ ግፊት ሆኖ የሚመራን፣ የጥል አሳብ ሆኖ የሚወተውተን፣ ምሪት ሆኖ ወደማንፈልገው የሚወስደን ኃይል ሲቆጣጠረን ብዙ ጊዜ ይገኛል፡፡ ይሄ ለምን ሆነ ስንል፤ የኛ የሰብአዊ ማንነት እና የመናፍስቱ ማንነት በአንድ ጉዳይ ላይ የተለያየ አቋም፣ የተለያየ አመለካከት፣ የተለያየ አካሄድና የተለያየ እቅድ ሲኖረን፤ መናፍስቱ ከውስጥ እኛን መስለው እኛን ይጣሉ ዘንድ ስልት ይቀይሳሉ፡፡
 
ምሳሌ እንመልከት፡፡ የሰላቢ፣ የዛር፣ የጣዖት፣ ስግብግብ የቡዳ መንፈሶች፤ ሰዎች ዐሥራት በኩራት ሲያወጡ አይወዱም፡፡ ስለዚህ ሠርተው የሚያገኙት ገንዘብ ወደ ቤተክርስቲያን ዐሥራት ሆኖ እንዳይደርስ፤ የውስጥ ጫና በመፍጠር፤ ዐሥራቱ እንዳይወጣ በራሳችን የአሳብ ልክ አሳብ ሆነው ይጣሉናል፡፡ "ኸረ ብዙ ቀዳዳዎች ያሉብህ ሰው ነህ ቀጣዩን ወር ታወጣለህ፤ አሁን ለዚህ ጉዳይ አውለውና በቶሎ ተክተህ ትሰጣለህ፤ ምንም በረከት ላታገኚ ዝም ብለሽ ነው ተይው ባክሽ፤ እግዚአብሔር ያንቺን ችግር ያውቃል ሲመችሽ ታወጪያለሽ" እና ወዘተ... የአሳብ ግፊቶችን በኛ ውስጠኛ ሕሊና ውስጥ በማመላለስ ዐሥራት ማውጣት የፈለገውን መንፈሳዊ ፍላጎታችንን ይዋጉታል፡፡
 
ታዲያ እጅግ በቁጥር የበዙ ሰዎች ውሳኔያቸው ከመለዋወጡ በፊት፤ ውሳኔ እንዲለወጥ ከውስጥ የሚገፋ ሁለተኛ ኃይል እንዳለባቸው ልብ አይሉትም፡፡ ምክንያቱም፤ መናፍስቱ ከውስጥ ሆነው ከኛ አሳብ ተደብቀው ሲጣሉን፤ ራሳችንን በራሳችን የምናወራ እንጂ ከሌላ ባዕድ ፍጡር ጋር እየተከራከርን እንደሆነ እንድናስተውል አይፈቅዱልንም፡፡
 
የክፋት መናፍስት የጥፋት አሳባቸውን ወደ ጥፋት ግብር ከመቀየራቸው በፊት ሁልጊዜ መቼት የሚባለውን "መቼ" እና "የት" የሚለውን የሥነ ጥበብ ሕግ ይጠቀሙታል፡፡ ይኸውም፤ መቼ የጥፋት አሳብ ማመንጨት፣ መቼ የጥፋት ግፊት መጨመር፣ መቼ የጥፋት ግብርን ማጽደቅ የሚል፤ ጊዜን ከውስጥ ወደ ውጪና ከውጪ ወደ ውስጥ የመጠበቅን ነገር ይጠነቀቁለታል፡፡ የት ብለው በሚጠብቁት የቦታ መምረጥ አሠራር ውስጥ ደግሞ፤ የት ስፍራ ላይ ጥፋቱን እንደሚመሩ፣ የት የውስጥ ተጽዕኖውን በጉልበት እንደሚፈጥሩ፣ የት የዓለማ ሥራቸውን እንደሚያስፈጽሙ ከውስጥ ሆነው ያቅዳሉ፡፡ ማለት ለምሳሌ፤ በመንፈሳዊ ጥንካሬና እውቀት ውስጥ ባለንበት ሰዓትና ቦታ ላይ መናፍስቱ የሌሉ ያህል ዝም ይላሉ፡፡ ከጊዜያት ቆይታ በኋላም ወደ ሥጋዊ አኗኗርና መንፈሳዊ ድክመት የምናዘነብልበት መቼና የት ሲመጣ፤ ከውስጥ ሆነው የመጣላት እቅዳቸውን ከውጪ በመጣው አጋጣሚ አስታክከው ለመፈጸም ይንቀሳቀሳሉ፡፡



tgoop.com/bemaledanek/2398
Create:
Last Update:

በቁጥር እጅግ ብዙ የሚባል ሰው፤ የሕይወት ጎዳናውን በራሱ የባለቤትነት ሥልጣን ተቆጣጥሮ በመኖር መንገዱ ላይ በውሳኔ እርምጃ ሲጓዝ አይታይም፡፡ ሰዎች በውስጣቸው ሌሎች ሰዎች ደባል ሆነው የሚኖሩ ያህል፤ በተቃራኒ ፍላጎቶች ሲንገላቱ፣ በተለያዩ ስሜቶች ሲዋዥቁ፣ በተሰበጣጠሩ አሳቦች ሲምታቱ፣ ባልተናበቡ እቅዶች ሲንከላወሱ፣ በሚነቃቀፉ ምግባሮች ሲደናገሩ፣ በሚለዋወጡ ጠባዮች ሲገለጡ ይስተዋላሉ፡፡ አንዳንዴሞ በተራራቁ የዋልታ ጥጎች ላይ በቆሙ ማንነቶች ከራሳቸው ጋር ክፉኛ እየተጋጩ፤ የኑሮ ገጠመኝ ባደረሳቸው ቦታ ላይ እንዴት እንደደረሱ ሳያውቁትና ሳይገነዘቡት ያለ'መኖርን ቀን እየቆጠሩ የሚኖሩ ጥቂት የማይባሉ ሰዎች አሉ፡፡ ነብዩ ምን አለ? .. "የሰው አካሄዱ ከራሱ ጋር እንዳይደለ አውቃለሁ"፡፡ ከራሱ ካልሆነ ታዲያ ከማን ጋር ነው?

ዲያቢሎስ ኃጢአት መፈጸማችንን ተከትሎ የመጣብን የውስጥ መደበላለቅ ውድቀታችን ላይ ይመካል፡፡ አንድ መሆን ያቃታቸው ውስጣዊ መገለጫዎቻችንን እንደ ጥሩ ዕድልና መሣሪያ በመጠቀም፤ የአእምሮ ሹክሹክታዎችን ከእኛ ለእኛ በማስደመጥ፣ በስሜት ግፊቶች ጀርባ ሆኖ ስሜቶችን በማዘባረቅ፣ ጠባያት በወጥነት መልክና ቅርጽ ተገኝተው የሰከነ ሁለንተና እንዳንይዝ የራሱን ጠባያት በተጻፉብን ባሕሪያቶቻችን በኩል በመግለጥ፣ ፍላጎትና የአኗኗር ዘይቤዎችን ተጋርቶ መስመር በማስለወጥ፣ ፍቃድና ውሳኔን ከፊት ቀድሞ በመምራትና ከኋላ ተከትሎ በመቆጣጠር፤ አካሄዳችን ከእግዚአብሔር ጋር ሳይሆን ከእርሱ ጋር እንዲሆን አድርጎ ወደ ወደደው መድረሻ በዝግታም በፍጥነትም ይመራናል፡፡ /አካሄዳችን ከእግዚአብሔር ጋር ሲሆን እንደ ኖኅ ከራሳችን ጋር አንድ እንሆናለን/

በዚህ ስለዚህ፤ አንዳንዶቻችን የአመላችን በተደጋጋሚ መቀያየርና አንዳች የጸና አቋም አለመያዝ ገርሞን እንዲሁ ራሳችንን እየታዘብን ተቀምጠናል፡፡ አንዳንዶቻችን የእኛነት መገለጫ አንድ ክፍል እንደሆነ አድርገን ተቀብለነው ከጊዜያዊ ሁነቶች ጋር ተሳስረን ከቅጽበት ጋር እንደ ቅጽበት የምንመላለስ ሰዎች ሆነናል፡፡ አንዳንዶቻችን ከራሳችን ጠባያትና አልረጋጋ የሚሉ ስሜቶች ጋር የግብግብ እልህ ተያይዘን፤ አንድ መሠረታዊ ገጽታ ያለው ማንነት ለመያዝ የምናደርገው ጥረት በተደጋጋሚ እየከሸፈ ግራ ሲያጋባን፤ ተስፋ ባለመቁረጥና በመቁረጥ መካከል ስንዋትት እንገኛለን፡፡ አንዳንዶቻችን ደግሞ፤ ከላይ የተገለጹትን አይነት ሰዎች ሁሉ በመሆን፤ አንዳንድ ቀን ራሳችንን የምንታዘብ፣ አንዳንድ ቀን እንደ ልዩ ማንነታችን የምንቀበል፣ በሌላ ቀን ከራሳችን ጋር የምንጣላና የምንፋለም ቀለም አልባ ሰዎች በመሆን እየተዘበራረቅን ዕድሜያችንን ቀጥለናል፡፡
 
ይሄ የጋራ ሐቃችን ሆኖ ሳለ፤ የሰው ልጅ የውስጣዊ ማንነት መተረማመረስና አልጨበጥ ማለት ከመንፈሳዊው ዓለም ጋር በቀጥታ እንደሚያያዝ፤ የክፉ መናፍስት አንዱ የውጊያ አዝመራ ስለመሆኑም፤ በጣም ለብዙዎቻችን ገና ሊገባን እንኳ አልጀመረም፡፡ ምክንያቱም ርኩሳን መናፍስት ዓላማቸውን ለማስፈጸም የሚሄዱበትን ሚስጢራዊ አካሄድ፣ ከሰው ልጆች ሕይወት ጋር ያላቸው ጥብቅ ትስስር፣ የማጥፋት አሠራር ጥበባቸውን እና ወደ ግባቸው ለመድረስ የሚጓዙበትን ሂደት፤ በሚገባ ለመገንዘብ የምናሳየው መሻት አነስተኛ በመሆኑ፤ ስውራኑ አጥቂዎቻችን በቸልተኝነታችን በኩል የተቀዳጁትን ኃይል የበለጠ ከዘመን ዘመን እያጠነከሩ፤ የእስራት ገመዳቸውን በማጥበቅ የሰብአዊነት ሕልውና ከምድረ ገጽ እንዲጠፋ በብርቱ እየሠሩ ይገኛሉ፡፡
 
በአንድ ሰው ውስጥ ብዙ እርስ በእርስ የሚጋጩ ማንነቶች ሊከሰቱ የቻሉት፤ ከላይ ባስቀመጥነው የአዳም ታሪክ ውስጥ በተፈጠረው ከእግዚአብሔር ፈቃድ አፈንግጦ የመውጣት ስሕተትነት እንደሆነ አንስተናል፡፡ በዚህ ጥፋታችን ላይም በመመካት ዲያቢሎስ ውሳጣዊ አንድነት እንዳናገኝ በተለያዩ ረቂቅ መንገዶች ተጠቅሞ እንደሚፋለም በአጭሩ ዳስሰናል፡፡ የበለጠ ግልጽ እይታ እንዲኖረን እነዚህን መንገዶቹን በሦስት ጎራዎች ከፍለን እንመልከታቸው፡፡
 
              ሀ] ሰው እና ሰው ውስጥ ያለ መንፈሱ ሲጋጩ
 
የአብዛኞቻችን የተለመደ ችግር ነው፡፡ ከውስጥ ተቃራኒ ግፊት ሆኖ የሚመራን፣ የጥል አሳብ ሆኖ የሚወተውተን፣ ምሪት ሆኖ ወደማንፈልገው የሚወስደን ኃይል ሲቆጣጠረን ብዙ ጊዜ ይገኛል፡፡ ይሄ ለምን ሆነ ስንል፤ የኛ የሰብአዊ ማንነት እና የመናፍስቱ ማንነት በአንድ ጉዳይ ላይ የተለያየ አቋም፣ የተለያየ አመለካከት፣ የተለያየ አካሄድና የተለያየ እቅድ ሲኖረን፤ መናፍስቱ ከውስጥ እኛን መስለው እኛን ይጣሉ ዘንድ ስልት ይቀይሳሉ፡፡
 
ምሳሌ እንመልከት፡፡ የሰላቢ፣ የዛር፣ የጣዖት፣ ስግብግብ የቡዳ መንፈሶች፤ ሰዎች ዐሥራት በኩራት ሲያወጡ አይወዱም፡፡ ስለዚህ ሠርተው የሚያገኙት ገንዘብ ወደ ቤተክርስቲያን ዐሥራት ሆኖ እንዳይደርስ፤ የውስጥ ጫና በመፍጠር፤ ዐሥራቱ እንዳይወጣ በራሳችን የአሳብ ልክ አሳብ ሆነው ይጣሉናል፡፡ "ኸረ ብዙ ቀዳዳዎች ያሉብህ ሰው ነህ ቀጣዩን ወር ታወጣለህ፤ አሁን ለዚህ ጉዳይ አውለውና በቶሎ ተክተህ ትሰጣለህ፤ ምንም በረከት ላታገኚ ዝም ብለሽ ነው ተይው ባክሽ፤ እግዚአብሔር ያንቺን ችግር ያውቃል ሲመችሽ ታወጪያለሽ" እና ወዘተ... የአሳብ ግፊቶችን በኛ ውስጠኛ ሕሊና ውስጥ በማመላለስ ዐሥራት ማውጣት የፈለገውን መንፈሳዊ ፍላጎታችንን ይዋጉታል፡፡
 
ታዲያ እጅግ በቁጥር የበዙ ሰዎች ውሳኔያቸው ከመለዋወጡ በፊት፤ ውሳኔ እንዲለወጥ ከውስጥ የሚገፋ ሁለተኛ ኃይል እንዳለባቸው ልብ አይሉትም፡፡ ምክንያቱም፤ መናፍስቱ ከውስጥ ሆነው ከኛ አሳብ ተደብቀው ሲጣሉን፤ ራሳችንን በራሳችን የምናወራ እንጂ ከሌላ ባዕድ ፍጡር ጋር እየተከራከርን እንደሆነ እንድናስተውል አይፈቅዱልንም፡፡
 
የክፋት መናፍስት የጥፋት አሳባቸውን ወደ ጥፋት ግብር ከመቀየራቸው በፊት ሁልጊዜ መቼት የሚባለውን "መቼ" እና "የት" የሚለውን የሥነ ጥበብ ሕግ ይጠቀሙታል፡፡ ይኸውም፤ መቼ የጥፋት አሳብ ማመንጨት፣ መቼ የጥፋት ግፊት መጨመር፣ መቼ የጥፋት ግብርን ማጽደቅ የሚል፤ ጊዜን ከውስጥ ወደ ውጪና ከውጪ ወደ ውስጥ የመጠበቅን ነገር ይጠነቀቁለታል፡፡ የት ብለው በሚጠብቁት የቦታ መምረጥ አሠራር ውስጥ ደግሞ፤ የት ስፍራ ላይ ጥፋቱን እንደሚመሩ፣ የት የውስጥ ተጽዕኖውን በጉልበት እንደሚፈጥሩ፣ የት የዓለማ ሥራቸውን እንደሚያስፈጽሙ ከውስጥ ሆነው ያቅዳሉ፡፡ ማለት ለምሳሌ፤ በመንፈሳዊ ጥንካሬና እውቀት ውስጥ ባለንበት ሰዓትና ቦታ ላይ መናፍስቱ የሌሉ ያህል ዝም ይላሉ፡፡ ከጊዜያት ቆይታ በኋላም ወደ ሥጋዊ አኗኗርና መንፈሳዊ ድክመት የምናዘነብልበት መቼና የት ሲመጣ፤ ከውስጥ ሆነው የመጣላት እቅዳቸውን ከውጪ በመጣው አጋጣሚ አስታክከው ለመፈጸም ይንቀሳቀሳሉ፡፡

BY በማለዳ ንቁ ቁጥር ! ፪


Share with your friend now:
tgoop.com/bemaledanek/2398

View MORE
Open in Telegram


Telegram News

Date: |

Co-founder of NFT renting protocol Rentable World emiliano.eth shared the group Tuesday morning on Twitter, calling out the "degenerate" community, or crypto obsessives that engage in high-risk trading. The channel also called on people to turn out for illegal assemblies and listed the things that participants should bring along with them, showing prior planning was in the works for riots. The messages also incited people to hurl toxic gas bombs at police and MTR stations, he added. It’s yet another bloodbath on Satoshi Street. As of press time, Bitcoin (BTC) and the broader cryptocurrency market have corrected another 10 percent amid a massive sell-off. Ethereum (EHT) is down a staggering 15 percent moving close to $1,000, down more than 42 percent on the weekly chart. Healing through screaming therapy Private channels are only accessible to subscribers and don’t appear in public searches. To join a private channel, you need to receive a link from the owner (administrator). A private channel is an excellent solution for companies and teams. You can also use this type of channel to write down personal notes, reflections, etc. By the way, you can make your private channel public at any moment.
from us


Telegram በማለዳ ንቁ ቁጥር ! ፪
FROM American