BEMALEDANEK Telegram 2403
ባለፉት ክፍሎቻችን በተደጋጋሚ እንዳወሳነው፤ የክርስቶስን ሥጋና ደም ከምንወስድበት ብዙ ምክንያቶች መካከል አንድነትን የተመለከተው ርእስ ይጠቀሳል፡፡ የኛን ሥጋን ተዋሕዶ ከእኛ ጋር አንድ የሆነ የእግዚአብሔር የባሕሪይ ልጅ፤ እኛን የሆነበትን የእርሱን ሥጋ ተዋሕደን ከእርሱ ጋር በአንድነት የምንኖርበት መንክር ጥበብ በተቀደሰው ማዕድ በኩል አካፍሎናል፡፡

ቤተሰቦች በሥጋና በደም ተዋልደው መዛመዳቸው በፍቅርና በአንድነት ስለመኖራቸው ዋስትና አይሆንም፡፡ ለዚህ ማስረጃው ማንም ሳይሆን እኛና ኑሮአችን ነን፡፡ በመልክ የተመሳሰሉ ሰዎች በቅራኔ ጠባያት ተለያይተው ለጸብ የሚፈላለጉ ሲሆኑ ማየት የጊዜያችን አንዱ ልማድ ሆኗል፡፡ ወንድማማቾች ከአንድ ማኅፀን የተወለዱ ጠላቶች ሆነው እርስ በእርስ ሲበላሉ መስማት የማይገርም ጉዳይ ከሆነ ሰንብቷል፡፡ ዘመዳማቾች በርስትና በንብረት ምክንያት ተጣልተው ፍርድ ቤት ሲመላለሱ መመልከት ከጀመርን ምን ያህል ጊዜ አልፎ ይሁን?

በቤተሰብ ውስጥ መተሳሰብ ሲጠፋ፣ መተጋገዝ ሲቀንስ፣ መስማማት ሲርቅ፣ መከባበር ሲለይ ወደ ቅዱስ ቁርባን እንጠጋለን፡፡ "አቤቱ የቤት ሰላም አጣሁ፣ አንድነትም ሸሸን" እያልን በጌታ ሥጋና ደም በኩል እንማጸናለን፡፡ ከሕይወት እንጀራ እየበላን ስለ ሕይወት መፍትሔ እንዲሰጠን እንለምናለን፡፡ እርሱ ከዛ በኋላ ሥራውን ይጀምራል፡፡ ከጓዳችን የራቀውን ፍቅር ይመልሰዋል፡፡ ከቤተሰባችን ውስጥ ቤተሰብ ሆኖ ክፋት የሚፈጽመውን ኃይል ዝም እንዲል ያዘዋል፡፡ አሁን፥ ቤትን ብቻ ሳይሆን መዋደድን፣ መቻቻልን፣ መደማመጥን፣ መጠባበቅን የምንጋራ በሥጋም በመንፈስም የተሳሰርን ሰዎች እንሆናለን፡፡

ሚስቶችም ባሎች አመል ሲለውጡ፣ ጠባይ ሲቀይሩ፣ መዋሸት ሲያበዙ፣ መደበቅ ሲያመጡ፣ መረበሽ ሲጀምሩ እጃቸውን በመቅደሱ መሥዋዕት በኩል ይዘረጋሉ፡፡ ትዳራቸውን ይታደግ ዘንድ የአምላክን እርዳታ ይጠይቃሉ፡፡ እግዚአብሔርም ጩኸታቸውን ይሰማል፡፡

ዛሬ ይሄ መንፈሳዊ ኃይልና ብልሃት ከግንዛቤ ዝርዝራችን ጠፍቶ፤ የቤተሰባችንን ችግር ለማቅለል ስንል የምንወስነው ውሳኔ በራሱ ባለ ችግር ሆኖ፤ ለሰላም ያወራነው ጸብ፣ ለአንድነት ያቀድነው መለያየት እየፈጠረ ግራ ያጋባናል፡፡ አለ እግዚአብሔር መንፈስ የምንከተለው መፍትሔ፥ መፍትሔ መሆን ስለማይችል፤ ትሕትና ስናሳይ ንቀት፣ ዝምታ ስንመርጥ ጥፋት፣ እሺ ስናበዛ ስሕተት ምላሽ ሆኖ እየተገለጠ በቁዘማና በብስጭት የምንኖር ብሶተኞች አድርጎናል፡፡

ወላጆች ልጆቻቸው ሲያስቸግሩአቸው፣ ምክር አሻፈረኝ ሲሉአቸው ወደ ጭቅጭቅና ቁጣ እንጂ ወደ እግዚአብሔር ኃይል አይሄዱም፡፡ ወጣቶችም ውስጣቸውን ባልተረዱበት መንፈሳዊ ስቃይ እየባተቱ፤ ከሥነ ምግባርና ግብረ ገብ ዕሴቶች በመሸሽ ስሜታዊነትን ያስቀደመ አስተሳሰብ እየተከተሉ ከቤተሰቦቻቸው ሀሳብና ፈቃድ ርቀው ይጓዛሉ፡፡ አባትና ልጅ፣ እናት ልጅ በሥጋና በደም ተካፈሉ እንጂ ከክርስቶስ ሥጋና ደም በአንድነት ስላልተካፈሉ፤ የኑሮና የጊዜ ክስተት በሚያመጧቸው ውጣ ውረዶች ምክንያትነት ተከፋፍለው ይነካከሳሉ፡፡ በአካል ተመሳስለው በሕይወት ተለያይተው ይኖራሉ፡፡

ብቻም ሳይሆን፥ ከክርስቶስ ጋር አንድ ሳይሆን በአንድ ቤት የሚኖር ቤተሰብ ወጥ የሆነ የወገናዊነት መተሳሰብ ያለበት ማኅበረሰብን፤ ከፍ ሲል አገርን ሊያስገኝ አይችልም፡፡ እግዚአብሔር በሌለበት የተሰበሰቡ ሰዎች ሰይጣን ባለበት መለያየት ይበታተኑ ዘንድ ግድ ነውና፡፡ እሺ ምን ይሻላል? ሀበነ ንኀበር ይሻላል.. አንድ እንሆን ዘንድ ከሥጋና ደምህ ስጠን!

ወደ ሥጋና ደሙ መጓዛችንን እንቀጥላለን...
#ጸባዖት_ይከተላችሁ
@bemaledanek



tgoop.com/bemaledanek/2403
Create:
Last Update:

ባለፉት ክፍሎቻችን በተደጋጋሚ እንዳወሳነው፤ የክርስቶስን ሥጋና ደም ከምንወስድበት ብዙ ምክንያቶች መካከል አንድነትን የተመለከተው ርእስ ይጠቀሳል፡፡ የኛን ሥጋን ተዋሕዶ ከእኛ ጋር አንድ የሆነ የእግዚአብሔር የባሕሪይ ልጅ፤ እኛን የሆነበትን የእርሱን ሥጋ ተዋሕደን ከእርሱ ጋር በአንድነት የምንኖርበት መንክር ጥበብ በተቀደሰው ማዕድ በኩል አካፍሎናል፡፡

ቤተሰቦች በሥጋና በደም ተዋልደው መዛመዳቸው በፍቅርና በአንድነት ስለመኖራቸው ዋስትና አይሆንም፡፡ ለዚህ ማስረጃው ማንም ሳይሆን እኛና ኑሮአችን ነን፡፡ በመልክ የተመሳሰሉ ሰዎች በቅራኔ ጠባያት ተለያይተው ለጸብ የሚፈላለጉ ሲሆኑ ማየት የጊዜያችን አንዱ ልማድ ሆኗል፡፡ ወንድማማቾች ከአንድ ማኅፀን የተወለዱ ጠላቶች ሆነው እርስ በእርስ ሲበላሉ መስማት የማይገርም ጉዳይ ከሆነ ሰንብቷል፡፡ ዘመዳማቾች በርስትና በንብረት ምክንያት ተጣልተው ፍርድ ቤት ሲመላለሱ መመልከት ከጀመርን ምን ያህል ጊዜ አልፎ ይሁን?

በቤተሰብ ውስጥ መተሳሰብ ሲጠፋ፣ መተጋገዝ ሲቀንስ፣ መስማማት ሲርቅ፣ መከባበር ሲለይ ወደ ቅዱስ ቁርባን እንጠጋለን፡፡ "አቤቱ የቤት ሰላም አጣሁ፣ አንድነትም ሸሸን" እያልን በጌታ ሥጋና ደም በኩል እንማጸናለን፡፡ ከሕይወት እንጀራ እየበላን ስለ ሕይወት መፍትሔ እንዲሰጠን እንለምናለን፡፡ እርሱ ከዛ በኋላ ሥራውን ይጀምራል፡፡ ከጓዳችን የራቀውን ፍቅር ይመልሰዋል፡፡ ከቤተሰባችን ውስጥ ቤተሰብ ሆኖ ክፋት የሚፈጽመውን ኃይል ዝም እንዲል ያዘዋል፡፡ አሁን፥ ቤትን ብቻ ሳይሆን መዋደድን፣ መቻቻልን፣ መደማመጥን፣ መጠባበቅን የምንጋራ በሥጋም በመንፈስም የተሳሰርን ሰዎች እንሆናለን፡፡

ሚስቶችም ባሎች አመል ሲለውጡ፣ ጠባይ ሲቀይሩ፣ መዋሸት ሲያበዙ፣ መደበቅ ሲያመጡ፣ መረበሽ ሲጀምሩ እጃቸውን በመቅደሱ መሥዋዕት በኩል ይዘረጋሉ፡፡ ትዳራቸውን ይታደግ ዘንድ የአምላክን እርዳታ ይጠይቃሉ፡፡ እግዚአብሔርም ጩኸታቸውን ይሰማል፡፡

ዛሬ ይሄ መንፈሳዊ ኃይልና ብልሃት ከግንዛቤ ዝርዝራችን ጠፍቶ፤ የቤተሰባችንን ችግር ለማቅለል ስንል የምንወስነው ውሳኔ በራሱ ባለ ችግር ሆኖ፤ ለሰላም ያወራነው ጸብ፣ ለአንድነት ያቀድነው መለያየት እየፈጠረ ግራ ያጋባናል፡፡ አለ እግዚአብሔር መንፈስ የምንከተለው መፍትሔ፥ መፍትሔ መሆን ስለማይችል፤ ትሕትና ስናሳይ ንቀት፣ ዝምታ ስንመርጥ ጥፋት፣ እሺ ስናበዛ ስሕተት ምላሽ ሆኖ እየተገለጠ በቁዘማና በብስጭት የምንኖር ብሶተኞች አድርጎናል፡፡

ወላጆች ልጆቻቸው ሲያስቸግሩአቸው፣ ምክር አሻፈረኝ ሲሉአቸው ወደ ጭቅጭቅና ቁጣ እንጂ ወደ እግዚአብሔር ኃይል አይሄዱም፡፡ ወጣቶችም ውስጣቸውን ባልተረዱበት መንፈሳዊ ስቃይ እየባተቱ፤ ከሥነ ምግባርና ግብረ ገብ ዕሴቶች በመሸሽ ስሜታዊነትን ያስቀደመ አስተሳሰብ እየተከተሉ ከቤተሰቦቻቸው ሀሳብና ፈቃድ ርቀው ይጓዛሉ፡፡ አባትና ልጅ፣ እናት ልጅ በሥጋና በደም ተካፈሉ እንጂ ከክርስቶስ ሥጋና ደም በአንድነት ስላልተካፈሉ፤ የኑሮና የጊዜ ክስተት በሚያመጧቸው ውጣ ውረዶች ምክንያትነት ተከፋፍለው ይነካከሳሉ፡፡ በአካል ተመሳስለው በሕይወት ተለያይተው ይኖራሉ፡፡

ብቻም ሳይሆን፥ ከክርስቶስ ጋር አንድ ሳይሆን በአንድ ቤት የሚኖር ቤተሰብ ወጥ የሆነ የወገናዊነት መተሳሰብ ያለበት ማኅበረሰብን፤ ከፍ ሲል አገርን ሊያስገኝ አይችልም፡፡ እግዚአብሔር በሌለበት የተሰበሰቡ ሰዎች ሰይጣን ባለበት መለያየት ይበታተኑ ዘንድ ግድ ነውና፡፡ እሺ ምን ይሻላል? ሀበነ ንኀበር ይሻላል.. አንድ እንሆን ዘንድ ከሥጋና ደምህ ስጠን!

ወደ ሥጋና ደሙ መጓዛችንን እንቀጥላለን...
#ጸባዖት_ይከተላችሁ
@bemaledanek

BY በማለዳ ንቁ ቁጥር ! ፪


Share with your friend now:
tgoop.com/bemaledanek/2403

View MORE
Open in Telegram


Telegram News

Date: |

The imprisonment came as Telegram said it was "surprised" by claims that privacy commissioner Ada Chung Lai-ling is seeking to block the messaging app due to doxxing content targeting police and politicians. The creator of the channel becomes its administrator by default. If you need help managing your channel, you can add more administrators from your subscriber base. You can provide each admin with limited or full rights to manage the channel. For example, you can allow an administrator to publish and edit content while withholding the right to add new subscribers. How to create a business channel on Telegram? (Tutorial) Content is editable within two days of publishing Telegram channels enable users to broadcast messages to multiple users simultaneously. Like on social media, users need to subscribe to your channel to get access to your content published by one or more administrators.
from us


Telegram በማለዳ ንቁ ቁጥር ! ፪
FROM American