BEMALEDANEK Telegram 2418
በማለዳ ንቁ ቁጥር ! ፪
3•  ቅዱስ ቁርባን ክፍል - ፭ የቀጠለ..             ✞ አንድ አድርገን ከራሳችን ጋር ✞    "ጥልንም በመስቀሉ ገድሎ በእርሱ ሁለታቸውን በአንድ አካል ከእግዚአብሔር ጋር ያስታርቅ ዘንድ ነው። መጥቶም ርቃችሁ ለነበራችሁ ለእናንተ ሰላምን፥ ቀርበው ለነበሩትም ሰላምን የምስራች ብሎ ሰበከ፤ በእርሱ ሥራ ሁላችን በአንድ መንፈስ ወደ አብ መግባት አለንና።"                      …
3•  ቅዱስ ቁርባን

ክፍል - ፮

           3.2•  ቅዱስ ቁርባን ለምን እንውሰድ ?

                      3.2.2•  በዲያቢሎስ ላይ

                    ✞ የልዑል ኃይል ይጸልልሻል

ሰው የእግዚአብሔር ልጅ ነው፡፡ አባቶች እግዚአብሔር አንድም በመፍጠር አባታችን ነው ይላሉ፡፡ ከክብሩ እንድንወርስ፣ ርስቱን እንድናስተዳድር፣ መልኩን እንድንመስል አድርጎ መፍጠሩ በእርግጥም ስለ አባትነቱ ይናገራል፡፡

ልጆቹ እንድንሆነው ፈቅዶ አስገኝቶናል፡፡ አምላክ ሰውን ወንድና ሴት አድርጎ ከፈጠረ በኋላ ይባርካቸዋል፡፡ "ብዙ ተባዙ በምድርም ሙሉ" ሲል ባሕሪያቸው ውስጥ የመዋለድን ሥርዓት ይጽፍባቸዋል፡፡ በዚህ መንገድ አዳምና ሔዋን የእግዚአብሔር ልጅ ሆነው የተፈጠሩበት ጥበብ እኛንም ልጆቹ ሊያደርገን በዘራችን ውስጥ በቡራኬ ተቀመጠ፡፡ ታዲያ "ውለዱ ክበዱ" ከማለቱ በፊት ባረካቸው የሚለው ይቀድማል፡፡ ይሄ የራሱ ምክንያት አለው፡፡

ስለ ቤተሰብ አንድነት ስንጨዋወት፥ አዳም በዲያቢሎስ ቃል ተሸውዶ ካስገኘው ፈቃድ ሲለይ የአምላኩ ፈቃድ ከሰጡትና ከሚሰጡትም ነገሮች አብሮ እንደተለየ አውስተን ነበር፡፡ ለምሳሌ ቀዳማውያኑ አባትና እናታችን ከገነት ተባርረው ነው የወለዱን፡፡ የአቤልና የቃየን ወላጆች ሰማያዊነትን ተገፈው ምድራዊ ሆነዋል፡፡ ከባረካቸው ከመለኮት ፍጹም ሕግ ተፋልሰዋል፤ ለመረጡት የሥጋ ሕግ ተላልፈዋል፡፡ እንግዲህ ልጆቻቸውም ለዚህ የሥጋ ሥርዓት የሚገዙ ይሆናሉ፡፡ በፈቃዱ ሆነን የምንዋለድበት የዘር ጽሕፈታችን በክፉው ድምፅ ተበላሽቷል፡፡ ከባሕሪያችን የተቆራኘ አሳች ምክር በፍጥረት የአምላክ ልጅ የምንሆንበትን የጸጋ ሥልጣን አስነጥቆናል፡፡ በእግዚአብሔር ፈቃድና ባርኮት ከምንወልድበት ሥርዓት በመውጣት፥ በራሳችን (በሥጋ) ፈቃድ ወደምንዋለድበት ሥርዓት ሄደናል፡፡

በዚህ ሁኔታ ቀጥለን ሳለ ነው ከወደ ቤተልሔም አንድ ብሥራት የተደመጠው፡፡ ከጠፋንበት የሚፈልግ፣ ወደ ወጣንበት የሚመልስ፣  ያጣነውን የሚሰጥ የምሥራች ቃል ለድንግል ማርያም ጆሮ ተሰማ፡፡ መልአኩ እንዲህ አላት፦

      "መንፈስ ቅዱስ በአንቺ ላይ ይመጣል፥ የልዑልም ኃይል ይጸልልሻል ስለዚህ ደግሞ ከአንቺ የሚወለደው ቅዱስ የእግዚአብሔር ልጅ ይባላል።"

                                                        (የሉቃስ ወንጌል 1፥35)

ተመስገን! የምንወልደው ልጅ ቅዱስ የእግዚአብሔር ልጅ መሆንን አጥቶት ነበር፡፡ እስከ መድኃኒቱ መወለድ ድረስ የወላጆቻችን ልጆች ብቻ ነበርን፡፡ በሌላ አባባል ምድርን ልንሞላ የምንባዛው ካለ እግዚአብሔር ቡራኬ ነበር፡፡ አሁን የቀደመው ተለውጦአል፤ ከእኛ የሚወለደው ቅዱሱ የእግዚአብሔር ልጅ የሚሆንበትን የባሕሪይ አለኝታ በዳዊት ከተማ አግኝተናል፡፡ እንዴት?

"አምላክ ሰው ሆነ" ብለን የእግዚአብሔር ልጅ የሰው ልጅ ሆነ ብለን በተዋሕዶ የምናምነው፤ "ሰውም አምላክ ሆነ" በሚለው ውስጥ ከእግዚአብሔር ተዋሕደን እንኖር ዘንድ ነው፡፡ ከእግዚአብሔር እንደምንዋሐድ ስናምን ደግሞ በድንግል ማርያም የተገለጸው ኪዳን በእኛም ውስጥ ይገለጻል ብለን እንቀበላለን፡፡ ዮሐንስ ይህንን ጉዳይ ያስረዳናል፦

      "ለተቀበሉት ሁሉ ግን፥ በስሙ ለሚያምኑት ለእነርሱ የእግዚአብሔር ልጆች ይሆኑ ዘንድ ሥልጣንን ሰጣቸው፤ እነርሱም ከእግዚአብሔር ተወለዱ እንጂ ከደም ወይም ከሥጋ ፈቃድ ወይም ከወንድ ፈቃድ አልተወለዱም።"

                                                       (የዮሐንስ ወንጌል 1፥13)


እመቤቲቱ "እንደ ቃልህ ይሁንልኝ" ስትል የእግዚአብሔርን [የባሕሪይ] ልጅ እንደወለደቺው፥ "እንደ ቃሉ አድርጉ" ስትል ደግሞ በእርሷ የተከናወነውን ታላቅ ሥራ በመቀበል እኛም የእግዚአብሔርን [የጸጋ] ልጅ እንድንወልድ ታስተምረናለች፡፡ ማርያም "ይሄ እንዴት ይሆናል?" ስትል ከመጠየቋ አስቀድሞ አንድ ነገር ሲመሰከርላት እንሰማለን፡፡ "መልአኩ ወደ እርስዋ ገብቶ። ደስ ይበልሽ፥ ጸጋ የሞላብሽ ሆይ፥ ጌታ ከአንቺ ጋር ነው፤ አንቺ ከሴቶች መካከል የተባረክሽ ነሽ" ብሎአታል፡፡

የርእሳችን ዋና ሀሳብ ይኸው ነው፡፡ የእግዚአብሔር ልጅ በምድር ከመወለዱ በፊት ወላጁ ከእግዚአብሔር ጋር ነበረች፡፡ በሰማይ ዘንድም ብናየው ሥጋ የሆነው ቃል አስቀድሞ በእግዚአብሔር ዘንድ የነበረ ነው፡፡ ስለዚህ ከመውለድ በፊት፥ ከአምላክ ጋር መሆን መቅደም የሚገባው መሠረታዊ ጉዳይ ነው ማለት ነው፡፡

ታዲያ ብዙዎች የሚስቱበት ቦታ እዚህ ከእግዚአብሔር ጋር ሆኖ የመውለዱ ቦታ ላይ ነው፡፡ ምእመናን በዕውቀት ተረድተውት በእምነት ተቀብለውት ይሁን አይሁን፥ በወለዱ ጊዜ ልጆቻቸውን ክርስትና ያስነሳሉ፡፡ ቤተክርስቲያን ወስደው በሥጋ ፈቃድ የወለዷቸው ልጆች በመንፈስም ፈቃድ እንዲወለዱ በ40 እና በ80 ቀን ያስጠምቋቸዋል፡፡ የእግዚአብሔር ልጆች የሚሆንበትን የስም ሥልጣን እንደተቀበሉ የሚያረጋግጥ የክርስትና ስምና ሰነድ ይዘው ወደ ቤታቸው ይመለሳሉ፡፡ መልካም!

ነገር ግን እኚሁ እናትና አባት ከመውለዳቸው አስቀድሞ ከጌታ ጋር እንደሆኑ የሚያስረግጥ የሕይወት ተክለ ቁመና የላቸውም (የራስን ቤተሰብ ያስቧል!)፡፡ ራሳቸውም ሲወለዱ ከእግዚአብሔር ጋር ካልኖሩ ወላጆች ተወልደው፤ በኑሮ መስመር በየፊናቸው ቆይተው፤ ወደ ትዳር ጊዜም ሲመጡ የኖሩበትን ልማድ ቀጥለው፤ ሃይማኖታዊ ዝግጅትና የእምነት መንፈስ ተረስቶ፥ ጋብቻቸው በፍሬ መድመቅ እንዳለበት በወሰኑበት ወቅት ላይ ልጅ ይወልዳሉ፡፡

ከጌታ ጋር ሳይሆን ከንግድ ጋራ፣ ከትምህርት ጋራ፣ ከሥጋ ዕውቀት ጋራ ቆይተን የወለድነው ልጅም፤ ከወላጆች ዘንድ መካፈል የነበረበትን መንፈሳዊ ቡራኬ አጥቶ ትናንሽ ልብሶችንና መታቀፊያ አግኝቶ ወደ ዓለም ይመጣል፡፡

እግዚአብሔርን ባጣ ኑሮ ውስጥ ያስገኘኘው ልጅ እንዲሁ እግዚአብሔርን እንደሚያጣ ሳይገባን፤ ከጌታ ጋር ሳንከርም የልዑል ኃይል እንደማይጸልልብንና መንፈስ ቅዱስም በኛ እንደማይመጣ ሳንረዳ የወለድናቸው ልጆች፤ መፍዘዝ፣ መደንገዝ፣ መጨነቅ፣ መታመም፣ እንቅልፍ ማጣት ወይም አብዝቶ መተኛት፣ መነጫነጭ በትንሽ ትልቁ ማልቀስ፣ መልፈስፈስ የማይለያቸው ግራ ግብት ያሉ ልጆች ሆነው ተወለዱ፡፡ ቁጭ በሉ ሲባሉ የሚነሡ፣ ተነሡ ሲባሉ የሚሄዱ፣ ሂዱ ሲባሉ የሚቀመጡ፣ ማስተዋልና የቤተሰብ ፍቅር የራቃቸው፣ ለመንፈሳዊ ዕውቀትና እውነት ፍላጎት የሌላቸው ሕፃናት ይዘው የሚሰቃዩ እናትና አባት በየሰፈሩና በየቤቱ በጣም ብዙ ናቸው፡፡

መንፈስ ቅዱስ በእርግጥ ልጆችን ክርስትና ባስነሳናቸው ጊዜ ይጎበኛቸዋል፡፡ ከጌታ ጋር ኖርንም አልኖርንም የእግዚአብሔር አባትነት አንድም በምሕረት ነውና፥ ቃልኪዳኑን አይተውም፡፡ እርሱን በአንደበት የወደደ በሕይወት የከዳ ሕይወትን ብንኖርንም ልጆቻችንን ልጁ የሚያደርግበትን የኪዳኑን ተስፋ አይከለክለንም፡፡ ችግሩ ልጆቻችን የክርስትና መታወቂያ አውጥተው ክርስቲያን የመሆናቸው ጉዳይ ላይ አይደለም፡፡ ችግሩ ከእግዚአብሔር መንፈስ ጋር ባልኖርበት ጊዜ ውስጥ የዲያቢሎስ መንፈስ አብሮን ኖሮ፥ በልጆቻችንም ላይ ይኖር ዘንድ አብሮአቸው የመወለዱ ጉዳይ ላይ ነው (የተሰመረበት ተደጋግሞ ይነበብማ)፡፡



tgoop.com/bemaledanek/2418
Create:
Last Update:

3•  ቅዱስ ቁርባን

ክፍል - ፮

           3.2•  ቅዱስ ቁርባን ለምን እንውሰድ ?

                      3.2.2•  በዲያቢሎስ ላይ

                    ✞ የልዑል ኃይል ይጸልልሻል

ሰው የእግዚአብሔር ልጅ ነው፡፡ አባቶች እግዚአብሔር አንድም በመፍጠር አባታችን ነው ይላሉ፡፡ ከክብሩ እንድንወርስ፣ ርስቱን እንድናስተዳድር፣ መልኩን እንድንመስል አድርጎ መፍጠሩ በእርግጥም ስለ አባትነቱ ይናገራል፡፡

ልጆቹ እንድንሆነው ፈቅዶ አስገኝቶናል፡፡ አምላክ ሰውን ወንድና ሴት አድርጎ ከፈጠረ በኋላ ይባርካቸዋል፡፡ "ብዙ ተባዙ በምድርም ሙሉ" ሲል ባሕሪያቸው ውስጥ የመዋለድን ሥርዓት ይጽፍባቸዋል፡፡ በዚህ መንገድ አዳምና ሔዋን የእግዚአብሔር ልጅ ሆነው የተፈጠሩበት ጥበብ እኛንም ልጆቹ ሊያደርገን በዘራችን ውስጥ በቡራኬ ተቀመጠ፡፡ ታዲያ "ውለዱ ክበዱ" ከማለቱ በፊት ባረካቸው የሚለው ይቀድማል፡፡ ይሄ የራሱ ምክንያት አለው፡፡

ስለ ቤተሰብ አንድነት ስንጨዋወት፥ አዳም በዲያቢሎስ ቃል ተሸውዶ ካስገኘው ፈቃድ ሲለይ የአምላኩ ፈቃድ ከሰጡትና ከሚሰጡትም ነገሮች አብሮ እንደተለየ አውስተን ነበር፡፡ ለምሳሌ ቀዳማውያኑ አባትና እናታችን ከገነት ተባርረው ነው የወለዱን፡፡ የአቤልና የቃየን ወላጆች ሰማያዊነትን ተገፈው ምድራዊ ሆነዋል፡፡ ከባረካቸው ከመለኮት ፍጹም ሕግ ተፋልሰዋል፤ ለመረጡት የሥጋ ሕግ ተላልፈዋል፡፡ እንግዲህ ልጆቻቸውም ለዚህ የሥጋ ሥርዓት የሚገዙ ይሆናሉ፡፡ በፈቃዱ ሆነን የምንዋለድበት የዘር ጽሕፈታችን በክፉው ድምፅ ተበላሽቷል፡፡ ከባሕሪያችን የተቆራኘ አሳች ምክር በፍጥረት የአምላክ ልጅ የምንሆንበትን የጸጋ ሥልጣን አስነጥቆናል፡፡ በእግዚአብሔር ፈቃድና ባርኮት ከምንወልድበት ሥርዓት በመውጣት፥ በራሳችን (በሥጋ) ፈቃድ ወደምንዋለድበት ሥርዓት ሄደናል፡፡

በዚህ ሁኔታ ቀጥለን ሳለ ነው ከወደ ቤተልሔም አንድ ብሥራት የተደመጠው፡፡ ከጠፋንበት የሚፈልግ፣ ወደ ወጣንበት የሚመልስ፣  ያጣነውን የሚሰጥ የምሥራች ቃል ለድንግል ማርያም ጆሮ ተሰማ፡፡ መልአኩ እንዲህ አላት፦

      "መንፈስ ቅዱስ በአንቺ ላይ ይመጣል፥ የልዑልም ኃይል ይጸልልሻል ስለዚህ ደግሞ ከአንቺ የሚወለደው ቅዱስ የእግዚአብሔር ልጅ ይባላል።"

                                                        (የሉቃስ ወንጌል 1፥35)

ተመስገን! የምንወልደው ልጅ ቅዱስ የእግዚአብሔር ልጅ መሆንን አጥቶት ነበር፡፡ እስከ መድኃኒቱ መወለድ ድረስ የወላጆቻችን ልጆች ብቻ ነበርን፡፡ በሌላ አባባል ምድርን ልንሞላ የምንባዛው ካለ እግዚአብሔር ቡራኬ ነበር፡፡ አሁን የቀደመው ተለውጦአል፤ ከእኛ የሚወለደው ቅዱሱ የእግዚአብሔር ልጅ የሚሆንበትን የባሕሪይ አለኝታ በዳዊት ከተማ አግኝተናል፡፡ እንዴት?

"አምላክ ሰው ሆነ" ብለን የእግዚአብሔር ልጅ የሰው ልጅ ሆነ ብለን በተዋሕዶ የምናምነው፤ "ሰውም አምላክ ሆነ" በሚለው ውስጥ ከእግዚአብሔር ተዋሕደን እንኖር ዘንድ ነው፡፡ ከእግዚአብሔር እንደምንዋሐድ ስናምን ደግሞ በድንግል ማርያም የተገለጸው ኪዳን በእኛም ውስጥ ይገለጻል ብለን እንቀበላለን፡፡ ዮሐንስ ይህንን ጉዳይ ያስረዳናል፦

      "ለተቀበሉት ሁሉ ግን፥ በስሙ ለሚያምኑት ለእነርሱ የእግዚአብሔር ልጆች ይሆኑ ዘንድ ሥልጣንን ሰጣቸው፤ እነርሱም ከእግዚአብሔር ተወለዱ እንጂ ከደም ወይም ከሥጋ ፈቃድ ወይም ከወንድ ፈቃድ አልተወለዱም።"

                                                       (የዮሐንስ ወንጌል 1፥13)


እመቤቲቱ "እንደ ቃልህ ይሁንልኝ" ስትል የእግዚአብሔርን [የባሕሪይ] ልጅ እንደወለደቺው፥ "እንደ ቃሉ አድርጉ" ስትል ደግሞ በእርሷ የተከናወነውን ታላቅ ሥራ በመቀበል እኛም የእግዚአብሔርን [የጸጋ] ልጅ እንድንወልድ ታስተምረናለች፡፡ ማርያም "ይሄ እንዴት ይሆናል?" ስትል ከመጠየቋ አስቀድሞ አንድ ነገር ሲመሰከርላት እንሰማለን፡፡ "መልአኩ ወደ እርስዋ ገብቶ። ደስ ይበልሽ፥ ጸጋ የሞላብሽ ሆይ፥ ጌታ ከአንቺ ጋር ነው፤ አንቺ ከሴቶች መካከል የተባረክሽ ነሽ" ብሎአታል፡፡

የርእሳችን ዋና ሀሳብ ይኸው ነው፡፡ የእግዚአብሔር ልጅ በምድር ከመወለዱ በፊት ወላጁ ከእግዚአብሔር ጋር ነበረች፡፡ በሰማይ ዘንድም ብናየው ሥጋ የሆነው ቃል አስቀድሞ በእግዚአብሔር ዘንድ የነበረ ነው፡፡ ስለዚህ ከመውለድ በፊት፥ ከአምላክ ጋር መሆን መቅደም የሚገባው መሠረታዊ ጉዳይ ነው ማለት ነው፡፡

ታዲያ ብዙዎች የሚስቱበት ቦታ እዚህ ከእግዚአብሔር ጋር ሆኖ የመውለዱ ቦታ ላይ ነው፡፡ ምእመናን በዕውቀት ተረድተውት በእምነት ተቀብለውት ይሁን አይሁን፥ በወለዱ ጊዜ ልጆቻቸውን ክርስትና ያስነሳሉ፡፡ ቤተክርስቲያን ወስደው በሥጋ ፈቃድ የወለዷቸው ልጆች በመንፈስም ፈቃድ እንዲወለዱ በ40 እና በ80 ቀን ያስጠምቋቸዋል፡፡ የእግዚአብሔር ልጆች የሚሆንበትን የስም ሥልጣን እንደተቀበሉ የሚያረጋግጥ የክርስትና ስምና ሰነድ ይዘው ወደ ቤታቸው ይመለሳሉ፡፡ መልካም!

ነገር ግን እኚሁ እናትና አባት ከመውለዳቸው አስቀድሞ ከጌታ ጋር እንደሆኑ የሚያስረግጥ የሕይወት ተክለ ቁመና የላቸውም (የራስን ቤተሰብ ያስቧል!)፡፡ ራሳቸውም ሲወለዱ ከእግዚአብሔር ጋር ካልኖሩ ወላጆች ተወልደው፤ በኑሮ መስመር በየፊናቸው ቆይተው፤ ወደ ትዳር ጊዜም ሲመጡ የኖሩበትን ልማድ ቀጥለው፤ ሃይማኖታዊ ዝግጅትና የእምነት መንፈስ ተረስቶ፥ ጋብቻቸው በፍሬ መድመቅ እንዳለበት በወሰኑበት ወቅት ላይ ልጅ ይወልዳሉ፡፡

ከጌታ ጋር ሳይሆን ከንግድ ጋራ፣ ከትምህርት ጋራ፣ ከሥጋ ዕውቀት ጋራ ቆይተን የወለድነው ልጅም፤ ከወላጆች ዘንድ መካፈል የነበረበትን መንፈሳዊ ቡራኬ አጥቶ ትናንሽ ልብሶችንና መታቀፊያ አግኝቶ ወደ ዓለም ይመጣል፡፡

እግዚአብሔርን ባጣ ኑሮ ውስጥ ያስገኘኘው ልጅ እንዲሁ እግዚአብሔርን እንደሚያጣ ሳይገባን፤ ከጌታ ጋር ሳንከርም የልዑል ኃይል እንደማይጸልልብንና መንፈስ ቅዱስም በኛ እንደማይመጣ ሳንረዳ የወለድናቸው ልጆች፤ መፍዘዝ፣ መደንገዝ፣ መጨነቅ፣ መታመም፣ እንቅልፍ ማጣት ወይም አብዝቶ መተኛት፣ መነጫነጭ በትንሽ ትልቁ ማልቀስ፣ መልፈስፈስ የማይለያቸው ግራ ግብት ያሉ ልጆች ሆነው ተወለዱ፡፡ ቁጭ በሉ ሲባሉ የሚነሡ፣ ተነሡ ሲባሉ የሚሄዱ፣ ሂዱ ሲባሉ የሚቀመጡ፣ ማስተዋልና የቤተሰብ ፍቅር የራቃቸው፣ ለመንፈሳዊ ዕውቀትና እውነት ፍላጎት የሌላቸው ሕፃናት ይዘው የሚሰቃዩ እናትና አባት በየሰፈሩና በየቤቱ በጣም ብዙ ናቸው፡፡

መንፈስ ቅዱስ በእርግጥ ልጆችን ክርስትና ባስነሳናቸው ጊዜ ይጎበኛቸዋል፡፡ ከጌታ ጋር ኖርንም አልኖርንም የእግዚአብሔር አባትነት አንድም በምሕረት ነውና፥ ቃልኪዳኑን አይተውም፡፡ እርሱን በአንደበት የወደደ በሕይወት የከዳ ሕይወትን ብንኖርንም ልጆቻችንን ልጁ የሚያደርግበትን የኪዳኑን ተስፋ አይከለክለንም፡፡ ችግሩ ልጆቻችን የክርስትና መታወቂያ አውጥተው ክርስቲያን የመሆናቸው ጉዳይ ላይ አይደለም፡፡ ችግሩ ከእግዚአብሔር መንፈስ ጋር ባልኖርበት ጊዜ ውስጥ የዲያቢሎስ መንፈስ አብሮን ኖሮ፥ በልጆቻችንም ላይ ይኖር ዘንድ አብሮአቸው የመወለዱ ጉዳይ ላይ ነው (የተሰመረበት ተደጋግሞ ይነበብማ)፡፡

BY በማለዳ ንቁ ቁጥር ! ፪


Share with your friend now:
tgoop.com/bemaledanek/2418

View MORE
Open in Telegram


Telegram News

Date: |

Telegram Channels requirements & features Among the requests, the Brazilian electoral Court wanted to know if they could obtain data on the origins of malicious content posted on the platform. According to the TSE, this would enable the authorities to track false content and identify the user responsible for publishing it in the first place. Today, we will address Telegram channels and how to use them for maximum benefit. Telegram message that reads: "Bear Market Screaming Therapy Group. You are only allowed to send screaming voice notes. Everything else = BAN. Text pics, videos, stickers, gif = BAN. Anything other than screaming = BAN. You think you are smart = BAN. Matt Hussey, editorial director at NEAR Protocol also responded to this news with “#meIRL”. Just as you search “Bear Market Screaming” in Telegram, you will see a Pepe frog yelling as the group’s featured image.
from us


Telegram በማለዳ ንቁ ቁጥር ! ፪
FROM American