BEMALEDANEK Telegram 2419
ቃየን አባትና እናቱ ከእግዚአብሔር ተለይተው የወለዱት ልጅ ነው፡፡ በኋላም ታሪኩ እንደሚተርከው በቅናት ተነሳስቶ ወንድሙን በሜዳ የገደለ ኃጢአት በደጁ ያደባችበት ሰው ነው፡፡ አዳም ከተከለከለው የዛፍ ፍሬ ሲበላ 'እነሆ ክፉውንና ደጉን ያውቅ ዘንድ ሆነ' ሲል አምላክ ተናግሮ ነበር፡፡ በአዳም ባሕሪይ ውስጥ ሁለት ተቃራኒ የሆኑ ዕውቀቶች ይዞታ አግኝተው ተቀምጠዋል፡፡ ይሄም በባሕሪይ ውስጥ የተገኘ ልዩነት በወለዳቸው ሁለቱ ልጆች ላይ በተጨባጭ ሲገለጥ እናያለን፡፡ ደጉ ዕውቀት በክፉው እንዲጠፋ ተፈርዶበታል፡፡ መልካሙ አቤል ሞቷል፡፡ እነሆ የቃየን ዘር በምድር ቀረ፤ ክፉውን ዕውቀት የገለጠው የነፍሰ ገዳዩ ዘር! ነፍሰ ገዳይን በተመለከተ ጌታ ሲናገር ፦

     "እናንተ ከአባታችሁ ከዲያብሎስ ናችሁ የአባታችሁንም ምኞት ልታደርጉ ትወዳላችሁ። እርሱ ከመጀመሪያ ነፍሰ ገዳይ ነበረ፤ እውነትም በእርሱ ስለ ሌለ በእውነት አልቆመም። ሐሰትን ሲናገር ከራሱ ይናገራል፥ ሐሰተኛ የሐሰትም አባት ነውና።"

                                                       (የዮሐንስ ወንጌል 8፥44)

ዘፍጥረት ምዕ.4 እንደሚነግረን የመጀመሪያው ነፍሰ ገዳይ ቃየን ነበረ /አበው ከግብሩ ተነሥተው የቃየንን የስም ትርጉም ሲፈቱ በኩረ ቀታልያን ይሉታል/፡፡ ይሄን የምንለው ክስተቱን በሥጋ የተረክነው እንደሆነ ነው፡፡ በሥጋ የምናየው ቃየንን ነው፡፡ ከቃየን ውስጥ ያለውን ገዳይ መንፈስ ለማየት የጌታ ዓይኖች ያስፈልጋሉ፡፡ ከሥጋ ባሻገር ያለውን ለመመልከት በክርስቶስ መነጽር መመልከት ያሻል፡፡ የአቤል ደም እንዲፈስ የኃጢአት ኃይልና ግፊት የነበረው፥ የሰውን ሥጋ ተከናንቦ የተቀመጠው የቃየንን መንፈስ "ዲያቢሎስ ከመጀመሪያ ነፍሰ ገዳይ ነበረ" ሲል ጌታ ገልጦታል፡፡ አባቶችም ቃየን ወንድሙን የገደለበትን ታሪክ ባሰፈሩበት የትርጓሜ መጽሐፋቸው ላይ የመግደሉን ምክር ሹክ ያለው ሰይጣን ስለመሆኑና ሲያልፍም በሰውና በቁራ አምሳል በመገለጽ፥ ሰውየው ቁራውን ድንጋይ ወርውሮ ሲገድለው እንዳሳየው አስፍረዋል፡፡ (ኦሪት ዘልደት አንድምታ)

መጽሐፍ ቃየን ወንድሙን የገደለበት ፍርድ ከተቀበለ በኋላ አስከትሎ እንዲህ ሆነ ይላል ፦

    "ቃየንም ከእግዚአብሔር ፊት ወጣ፤ ከዔድንም ወደ ምሥራቅ በኖድ ምድር ተቀመጠ። ቃየንም ሚስቱን አወቀ፤ ፀነሰችም፥ ሄኖሕንም ወለደች። ከተማም ሠራ፥ የከተማይቱንም ስም በልጁ ስም ሄኖሕ አላት። ሄኖሕም ጋይዳድን ወለደ፤ ጋይዳድም ሜኤልን ወለደ፤ ሜኤልም ማቱሣኤልን ወለደ፤ ማቱሣኤልም ላሜሕን ወለደ.. "

                                                (ኦሪት ዘፍጥረት 4፥16-18)

ቤተሰቦቹ ከእግዚአብሔር ፈቃድ ወጥተው የወለዱት ቃየን፥ እርሱም የራሱን ዓመፃ ጨምሮ ከእግዚአብሔር ፊት በመለየት ወለደ፡፡ በዚህ ዓመፃ በተጣባው ልደት ውስጥ የአምላክ ቅዱስ መንፈስ ይገኛል ማለት መቼም ድፍረትም ጭምር ነው፡፡ ይልቅስ በአንጻሩ የኃጢአት መሠረትና መነሻ የሆነው የዲያቢሎስ መንፈስ በቃየን ዘር ውስጥ ዘልቆ ቁራኛ በመሆን ከማኅፀን ጀምሮ ልክፍት በመሆን የቁጥጥር አድማሱን ያጠነክራል፡፡

መናፍስት አብረው ይወለዳሉ ማለት በወላጆች ላይ አስቀድመው የነበሩ መንፈሶች የዘር ሐረግ ውስጥ ዘልቀው በመዋረስ፤ የሚወለዱት ልጆች ላይ ልክፍት በመሆን ከማኅፀን ሳለ ተዋሕደው የሰብአዊውን ሰው ማንነት በመጋራት፤ ሳጥን ውስጥ እንደ ተቀመጠ አንዳች ዕቃ ወይንም ጓንት እንዳጠለቀ እጅ ሆነው ግለሰቡን ይዳበላሉ ማለት ነው፡፡

በተለይም የዛር መናፍስት (በዘር ውስጥ የሚወራረሱ መንፈሶች) የቤተሰብን የኋላ ትከሻ በመቆጣጠር፤ በቀጣይነት በሚመጡት ትውልዶች ላይ ከእናትና ከአባት ውስጥ ሆነው ወደ ልጆች በመሻገር በባሕሪይ ውስጥ ገብተው፥ ተመሳስለው ያድጋሉ፡፡ አብረው ስለሚያድጉ መናፍስት ወንጌል ሲጠቁም፦

       "አባቱንም። ይህ ከያዘው ስንት ዘመን ነው? ብሎ ጠየቀው። እርሱም። ከሕፃንነቱ ጀምሮ ነው"

                                                     (የማርቆስ ወንጌል 9፥21)


ከቅድመ አያትና ከዛም በላይ ባለ የቤተሰብ ሰንሰለት ውስጥ ከጣዖት መናፍስት ጋር ቁርኝት ያላቸው ሰዎች በልጆቻቸው ላይ መንፈሶቹ እየተወራረሱ አብረው በመወለድ፤ ጠባይን፣ ጊዜን፣ ዕድልንና የኑሮ ገጽታን ተዋሕደው ይኖራሉ፡፡

የመናፍስት በዘር ትውልድ ውስጥ የመተላለፍ እውነታ እንዴት ነው ስንል፦

1ኛ•  አንድ ቤተሰብ በተለያዩ የባዕድ አምልኮቶች ውስጥ በመገኘት እንደ ጨሌ፣ አቴቴ፣ አዳል ሞቲ፣ ወሰን ገፊ፣ ወሰን ገላ፣ ውቃቢ፣ አዳኝ ወርቁ፣ አውሊያ፣ ታዬ ከራማ፣ አርሜት፣ ደማሜት፣ ራሔሎ፣ ሐጎስ፣ የአሩሲዋ እመቤት፣ አመቺሳ፣ ጠቋርና ወዘተ.. ተብለው በተለያየ መጠሪያ ለተሾሙ መንፈሶች ከባሕል፣ ከዘልማድ ወግና ከሥጋዊ ጥቅም ጋር የተያያዘ መናፍስታዊ ግብሮችን ሲገብር የቆየ ከሆነ፤ ከቤተሰቡ የዘር ትውልድ በሚገኙ ልጆች ሁሉ መንፈሶቹ እየተወራረሱ ልክፍት በመሆን አብረው ይወለዳሉ፡፡ ከእነዚህ መናፍስት ጋር ግንኙነት የነበረው የትውልድ ዘር፤ ባዕድ አምልኮቱን ቢያቆምም፣ ጨሌውን ቢጥልም፣ አንካሴውን ቢሰብርም፣ ጀበናና ልብሱን ቢጥልም፣ የመናፍስቱን ንብረቶች ቢያቃጥልም፣ ግብሩን ቢያስቀርም፣ በሞት ከዚህ ዓለም ቢለይም መንፈሶቹ እስካልተነቃባቸው ድረስ ልጆች ላይ አብረው ከመወለድ አያቆሙም፡፡

2ኛ• በመተት፣ በዓይነጥላ፣ በቡዳና በሌሎችም የተለያዩ መናፍስት የታሠረ ቤተሰብ ከሆነ፤ እንደ መስተፋቅር፣ መስተባርር፣ ዕፀ ፋሪስ፣ አረማዊ መፍትሔ ሥራይ እና ሌሎችም በርካታ የመናፍስት የአሠራር ድጋፎች ላይ በመሳተፍ የቆየ ቤተሰብ ከሆነ፤ ዛር የሚያነግሥ ቤተሰብ ባይሆን እንኳ፥ ዛሩ የተመለከበት ቤት አሊያም አካባቢ ውስጥ የሚኖር ከሆነ፤ የሌሎች ሰዎች መንፈስ በማየት፣ በመንካት፣ በምግብና በመጠጥ ተዋርሶ ወደ ቤተሰቡ የመጣ ከሆነ፤ በዓይን የማይታየው መንፈስ ገና በጽንስ ላይ ያለ ልጅን ለመያዝ ምንም አያግደውም፡፡ እነዚህኞቹ እንደ ግብር ፈላጊዎቹ ተሿሚ የዛር መናፍስት ረጅም የትውልድ ሐረግን አቆራርጠው ላይመጡ ይችላሉ፡፡ ከወላጆች ወደ ልጆች፥ ከሌሎች ሰዎች ወደ ልጆች ግን ይሻገራሉ፡፡

"ዘመናዊ" የተባለው የዛሬው ትውልድ ሊረዳው ያልቻለው ትልቁ የችግር መጀመሪያችን ይሄ ነው፡፡ ከተወለድንባት ዕለት ጀምሮ አብሮ የተገኘ ሌላ ክፉ ፍጡር እንዳለ ለመገንዘብ እንዳንችል ሥጋዊ ዕውቀትና የቁስ ሕይወት ከለላ ሆኖብናል፡፡ ግን በሚያሳዝን ሁኔታ ሰዉ በነዚህ ውርስ መናፍስት አረንቋ ሥር ተይዞ ይገኛል፡፡ ቀደም ሲል በነበረው የማኅበረሰብ ልማድ በተለያየ ባሕላዊ ምክንያቶች የተሸፈነ የባዕድ አምልኮት ሥርዓት ነበር (አለም!)፡፡ በሰፊውና በጥልቀት የቁጥር መረጃዎችን ዋቢ ያደረገ ጥናት ቢደረግ፤ የጣዖት መናፍስት ትስስር በሕብረተሰባችን መካከል ሰርጎ እንደገባ የሚያመላክት እጅግ አስደንጋጭ የሆነ አዕዛዊ ማስረጃ እናገኝ ነበር፡፡

እዚህ ጋር ምእመናን ግር የሚያሰኛቸው አንድ ጥያቄ ሊኖር ይችላል፡፡ ቤተሰቦች ከእግዚአብሔር ጋር ሳይኖሩ በመቆየታቸው ምክንያትነት በተቃራኒው የሚኖረው የዲያብሎስ መንፈስ በተጠመቀ ልጃቸው ላይ እንዴት ሊዋረስ እንደተቻለው ጥያቄ ሊሆንባቸው ይችላል፡፡



tgoop.com/bemaledanek/2419
Create:
Last Update:

ቃየን አባትና እናቱ ከእግዚአብሔር ተለይተው የወለዱት ልጅ ነው፡፡ በኋላም ታሪኩ እንደሚተርከው በቅናት ተነሳስቶ ወንድሙን በሜዳ የገደለ ኃጢአት በደጁ ያደባችበት ሰው ነው፡፡ አዳም ከተከለከለው የዛፍ ፍሬ ሲበላ 'እነሆ ክፉውንና ደጉን ያውቅ ዘንድ ሆነ' ሲል አምላክ ተናግሮ ነበር፡፡ በአዳም ባሕሪይ ውስጥ ሁለት ተቃራኒ የሆኑ ዕውቀቶች ይዞታ አግኝተው ተቀምጠዋል፡፡ ይሄም በባሕሪይ ውስጥ የተገኘ ልዩነት በወለዳቸው ሁለቱ ልጆች ላይ በተጨባጭ ሲገለጥ እናያለን፡፡ ደጉ ዕውቀት በክፉው እንዲጠፋ ተፈርዶበታል፡፡ መልካሙ አቤል ሞቷል፡፡ እነሆ የቃየን ዘር በምድር ቀረ፤ ክፉውን ዕውቀት የገለጠው የነፍሰ ገዳዩ ዘር! ነፍሰ ገዳይን በተመለከተ ጌታ ሲናገር ፦

     "እናንተ ከአባታችሁ ከዲያብሎስ ናችሁ የአባታችሁንም ምኞት ልታደርጉ ትወዳላችሁ። እርሱ ከመጀመሪያ ነፍሰ ገዳይ ነበረ፤ እውነትም በእርሱ ስለ ሌለ በእውነት አልቆመም። ሐሰትን ሲናገር ከራሱ ይናገራል፥ ሐሰተኛ የሐሰትም አባት ነውና።"

                                                       (የዮሐንስ ወንጌል 8፥44)

ዘፍጥረት ምዕ.4 እንደሚነግረን የመጀመሪያው ነፍሰ ገዳይ ቃየን ነበረ /አበው ከግብሩ ተነሥተው የቃየንን የስም ትርጉም ሲፈቱ በኩረ ቀታልያን ይሉታል/፡፡ ይሄን የምንለው ክስተቱን በሥጋ የተረክነው እንደሆነ ነው፡፡ በሥጋ የምናየው ቃየንን ነው፡፡ ከቃየን ውስጥ ያለውን ገዳይ መንፈስ ለማየት የጌታ ዓይኖች ያስፈልጋሉ፡፡ ከሥጋ ባሻገር ያለውን ለመመልከት በክርስቶስ መነጽር መመልከት ያሻል፡፡ የአቤል ደም እንዲፈስ የኃጢአት ኃይልና ግፊት የነበረው፥ የሰውን ሥጋ ተከናንቦ የተቀመጠው የቃየንን መንፈስ "ዲያቢሎስ ከመጀመሪያ ነፍሰ ገዳይ ነበረ" ሲል ጌታ ገልጦታል፡፡ አባቶችም ቃየን ወንድሙን የገደለበትን ታሪክ ባሰፈሩበት የትርጓሜ መጽሐፋቸው ላይ የመግደሉን ምክር ሹክ ያለው ሰይጣን ስለመሆኑና ሲያልፍም በሰውና በቁራ አምሳል በመገለጽ፥ ሰውየው ቁራውን ድንጋይ ወርውሮ ሲገድለው እንዳሳየው አስፍረዋል፡፡ (ኦሪት ዘልደት አንድምታ)

መጽሐፍ ቃየን ወንድሙን የገደለበት ፍርድ ከተቀበለ በኋላ አስከትሎ እንዲህ ሆነ ይላል ፦

    "ቃየንም ከእግዚአብሔር ፊት ወጣ፤ ከዔድንም ወደ ምሥራቅ በኖድ ምድር ተቀመጠ። ቃየንም ሚስቱን አወቀ፤ ፀነሰችም፥ ሄኖሕንም ወለደች። ከተማም ሠራ፥ የከተማይቱንም ስም በልጁ ስም ሄኖሕ አላት። ሄኖሕም ጋይዳድን ወለደ፤ ጋይዳድም ሜኤልን ወለደ፤ ሜኤልም ማቱሣኤልን ወለደ፤ ማቱሣኤልም ላሜሕን ወለደ.. "

                                                (ኦሪት ዘፍጥረት 4፥16-18)

ቤተሰቦቹ ከእግዚአብሔር ፈቃድ ወጥተው የወለዱት ቃየን፥ እርሱም የራሱን ዓመፃ ጨምሮ ከእግዚአብሔር ፊት በመለየት ወለደ፡፡ በዚህ ዓመፃ በተጣባው ልደት ውስጥ የአምላክ ቅዱስ መንፈስ ይገኛል ማለት መቼም ድፍረትም ጭምር ነው፡፡ ይልቅስ በአንጻሩ የኃጢአት መሠረትና መነሻ የሆነው የዲያቢሎስ መንፈስ በቃየን ዘር ውስጥ ዘልቆ ቁራኛ በመሆን ከማኅፀን ጀምሮ ልክፍት በመሆን የቁጥጥር አድማሱን ያጠነክራል፡፡

መናፍስት አብረው ይወለዳሉ ማለት በወላጆች ላይ አስቀድመው የነበሩ መንፈሶች የዘር ሐረግ ውስጥ ዘልቀው በመዋረስ፤ የሚወለዱት ልጆች ላይ ልክፍት በመሆን ከማኅፀን ሳለ ተዋሕደው የሰብአዊውን ሰው ማንነት በመጋራት፤ ሳጥን ውስጥ እንደ ተቀመጠ አንዳች ዕቃ ወይንም ጓንት እንዳጠለቀ እጅ ሆነው ግለሰቡን ይዳበላሉ ማለት ነው፡፡

በተለይም የዛር መናፍስት (በዘር ውስጥ የሚወራረሱ መንፈሶች) የቤተሰብን የኋላ ትከሻ በመቆጣጠር፤ በቀጣይነት በሚመጡት ትውልዶች ላይ ከእናትና ከአባት ውስጥ ሆነው ወደ ልጆች በመሻገር በባሕሪይ ውስጥ ገብተው፥ ተመሳስለው ያድጋሉ፡፡ አብረው ስለሚያድጉ መናፍስት ወንጌል ሲጠቁም፦

       "አባቱንም። ይህ ከያዘው ስንት ዘመን ነው? ብሎ ጠየቀው። እርሱም። ከሕፃንነቱ ጀምሮ ነው"

                                                     (የማርቆስ ወንጌል 9፥21)


ከቅድመ አያትና ከዛም በላይ ባለ የቤተሰብ ሰንሰለት ውስጥ ከጣዖት መናፍስት ጋር ቁርኝት ያላቸው ሰዎች በልጆቻቸው ላይ መንፈሶቹ እየተወራረሱ አብረው በመወለድ፤ ጠባይን፣ ጊዜን፣ ዕድልንና የኑሮ ገጽታን ተዋሕደው ይኖራሉ፡፡

የመናፍስት በዘር ትውልድ ውስጥ የመተላለፍ እውነታ እንዴት ነው ስንል፦

1ኛ•  አንድ ቤተሰብ በተለያዩ የባዕድ አምልኮቶች ውስጥ በመገኘት እንደ ጨሌ፣ አቴቴ፣ አዳል ሞቲ፣ ወሰን ገፊ፣ ወሰን ገላ፣ ውቃቢ፣ አዳኝ ወርቁ፣ አውሊያ፣ ታዬ ከራማ፣ አርሜት፣ ደማሜት፣ ራሔሎ፣ ሐጎስ፣ የአሩሲዋ እመቤት፣ አመቺሳ፣ ጠቋርና ወዘተ.. ተብለው በተለያየ መጠሪያ ለተሾሙ መንፈሶች ከባሕል፣ ከዘልማድ ወግና ከሥጋዊ ጥቅም ጋር የተያያዘ መናፍስታዊ ግብሮችን ሲገብር የቆየ ከሆነ፤ ከቤተሰቡ የዘር ትውልድ በሚገኙ ልጆች ሁሉ መንፈሶቹ እየተወራረሱ ልክፍት በመሆን አብረው ይወለዳሉ፡፡ ከእነዚህ መናፍስት ጋር ግንኙነት የነበረው የትውልድ ዘር፤ ባዕድ አምልኮቱን ቢያቆምም፣ ጨሌውን ቢጥልም፣ አንካሴውን ቢሰብርም፣ ጀበናና ልብሱን ቢጥልም፣ የመናፍስቱን ንብረቶች ቢያቃጥልም፣ ግብሩን ቢያስቀርም፣ በሞት ከዚህ ዓለም ቢለይም መንፈሶቹ እስካልተነቃባቸው ድረስ ልጆች ላይ አብረው ከመወለድ አያቆሙም፡፡

2ኛ• በመተት፣ በዓይነጥላ፣ በቡዳና በሌሎችም የተለያዩ መናፍስት የታሠረ ቤተሰብ ከሆነ፤ እንደ መስተፋቅር፣ መስተባርር፣ ዕፀ ፋሪስ፣ አረማዊ መፍትሔ ሥራይ እና ሌሎችም በርካታ የመናፍስት የአሠራር ድጋፎች ላይ በመሳተፍ የቆየ ቤተሰብ ከሆነ፤ ዛር የሚያነግሥ ቤተሰብ ባይሆን እንኳ፥ ዛሩ የተመለከበት ቤት አሊያም አካባቢ ውስጥ የሚኖር ከሆነ፤ የሌሎች ሰዎች መንፈስ በማየት፣ በመንካት፣ በምግብና በመጠጥ ተዋርሶ ወደ ቤተሰቡ የመጣ ከሆነ፤ በዓይን የማይታየው መንፈስ ገና በጽንስ ላይ ያለ ልጅን ለመያዝ ምንም አያግደውም፡፡ እነዚህኞቹ እንደ ግብር ፈላጊዎቹ ተሿሚ የዛር መናፍስት ረጅም የትውልድ ሐረግን አቆራርጠው ላይመጡ ይችላሉ፡፡ ከወላጆች ወደ ልጆች፥ ከሌሎች ሰዎች ወደ ልጆች ግን ይሻገራሉ፡፡

"ዘመናዊ" የተባለው የዛሬው ትውልድ ሊረዳው ያልቻለው ትልቁ የችግር መጀመሪያችን ይሄ ነው፡፡ ከተወለድንባት ዕለት ጀምሮ አብሮ የተገኘ ሌላ ክፉ ፍጡር እንዳለ ለመገንዘብ እንዳንችል ሥጋዊ ዕውቀትና የቁስ ሕይወት ከለላ ሆኖብናል፡፡ ግን በሚያሳዝን ሁኔታ ሰዉ በነዚህ ውርስ መናፍስት አረንቋ ሥር ተይዞ ይገኛል፡፡ ቀደም ሲል በነበረው የማኅበረሰብ ልማድ በተለያየ ባሕላዊ ምክንያቶች የተሸፈነ የባዕድ አምልኮት ሥርዓት ነበር (አለም!)፡፡ በሰፊውና በጥልቀት የቁጥር መረጃዎችን ዋቢ ያደረገ ጥናት ቢደረግ፤ የጣዖት መናፍስት ትስስር በሕብረተሰባችን መካከል ሰርጎ እንደገባ የሚያመላክት እጅግ አስደንጋጭ የሆነ አዕዛዊ ማስረጃ እናገኝ ነበር፡፡

እዚህ ጋር ምእመናን ግር የሚያሰኛቸው አንድ ጥያቄ ሊኖር ይችላል፡፡ ቤተሰቦች ከእግዚአብሔር ጋር ሳይኖሩ በመቆየታቸው ምክንያትነት በተቃራኒው የሚኖረው የዲያብሎስ መንፈስ በተጠመቀ ልጃቸው ላይ እንዴት ሊዋረስ እንደተቻለው ጥያቄ ሊሆንባቸው ይችላል፡፡

BY በማለዳ ንቁ ቁጥር ! ፪


Share with your friend now:
tgoop.com/bemaledanek/2419

View MORE
Open in Telegram


Telegram News

Date: |

6How to manage your Telegram channel? Done! Now you’re the proud owner of a Telegram channel. The next step is to set up and customize your channel. “Hey degen, are you stressed? Just let it all out,” he wrote, along with a link to join the group. 2How to set up a Telegram channel? (A step-by-step tutorial)
from us


Telegram በማለዳ ንቁ ቁጥር ! ፪
FROM American