BEMALEDANEK Telegram 2425
በማለዳ ንቁ ቁጥር ! ፪
3•  ቅዱስ ቁርባን ክፍል - ፮            3.2•  ቅዱስ ቁርባን ለምን እንውሰድ ?                       3.2.2•  በዲያቢሎስ ላይ                     ✞ የልዑል ኃይል ይጸልልሻል ✞ ሰው የእግዚአብሔር ልጅ ነው፡፡ አባቶች እግዚአብሔር አንድም በመፍጠር አባታችን ነው ይላሉ፡፡ ከክብሩ እንድንወርስ፣ ርስቱን እንድናስተዳድር፣ መልኩን እንድንመስል አድርጎ መፍጠሩ…
3•  ቅዱስ ቁርባን

   ከክፍል - ፮ የቀጠለ..

ወደ ጀመርነው ሀሳባችን እንመለስ፡፡ መልአኩ ለድንግል ማርያም "ደስ ይበልሽ ጌታ ካንቺ ጋር ነው" ብሎ አላበቃም፡፡ እንዴት እንደምትወልድ ጭምር ይነግራታል፡፡ ከተለመደው የሥጋ ፈቃድ ውጪ የምትጸንስበትን ጥበብ ያሳውቃታል፡፡ "መንፈስ ቅዱስ በአንቺ ላይ ይመጣል፥ የልዑልም ኃይል ይጸልልሻል ስለዚህ ደግሞ ከአንቺ የሚወለደው ቅዱስ የእግዚአብሔር ልጅ ይባላል" አላት፡፡

እዚህ ጋር በደንብ እናስተውል፡፡ "ከአንቺ የሚወለደው" ከሚለው በፊት የተጻፈው "መንፈስ ቅዱስ ባንቺ ላይ ይመጣል፥ የልዑልም ኃይል ይጸልልሻል" የሚለው ነው፡፡ መድኃኒታችን ከመጸነሱ አስቀድሞ የመንፈስ ቅዱስ ኃይል በእመቤታችን ላይ መጥቶአል፥ የልዑልም ኃይል ጸልሎአት አርፎአል፡፡ 'መጸለል' የሚለው ቃል አውዳዊ ፍቺው 'መጋረድ፣ መከለል፣ መጠበቅ' የሚል ትርጉም ይኖረዋል፡፡ በመሆኑም ረቂቅ የእግዚአብሔር ልጅ በምድራዊው ዓለም በግዙፍ ሥጋ ከመገለጡ አስቀድሞ የድንግሊቱን ውሳጣዊ ሕይወት ከኃጢአት ጠብቆ ማደሪያ ሲያደርገው፥ ውጪያዊ ሰውነቷን ደግሞ በመንፈስ ቅዱስ ኃይል ጋርዶታል፡፡

መንፈስ ቅዱስ በድንግል ማርያም እሳተ ክበብ ሆኖ እንደ መጋረጃ ሲከድናት፥ ቃል ሥጋ የመሆኑ ጥበብ ሚሥጢር ሆነ፡፡ የመለኮት ባሕሪይ የሰውነትን ባሕሪይ በተዋሕዶ ገንዘብ ማድረጉ 'ሚሥጥረ ሥጋዌ' የተባለው፥ ይህ ልዩ የእግዚአብሔር ጥበብ በፍጡራን ልዕልና ለመመርመርና ለመታወቅ ባለመቻሉ ነው፡፡ የልዑል ኃይል በብላቴናይቱ ላይ ከጸለለ በኋላ፥ ከዓለም የእውቅና መረጃ ርቆ የእግዚአብሔር ልጅ የሰው ልጅ ሆነ፡፡ ለመሆኑ የወልደ እግዚአብሔር በሥጋ መገለጥ ስለምን ሚሥጢር ሆነ?

      "ኃጢአትን የሚያደርግ ከዲያብሎስ ነው፥ ዲያብሎስ ከመጀመሪያ ኃጢአትን ያደርጋልና። ስለዚህ የዲያብሎስን ሥራ እንዲያፈርስ የእግዚአብሔር ልጅ ተገለጠ። ከእግዚአብሔር የተወለደ ሁሉ ኃጢአትን አያደርግም፥ ዘሩ በእርሱ ይኖራልና፤ ከእግዚአብሔርም ተወልዶአልና ኃጢአትን ሊያደርግ አይችልም።"

                                              (1ኛ የዮሐንስ መልእክት 3፥8-9)

ዲያቢሎስ ወደነአዳም በእባብ ሥጋ ተደብቆ በመሄድ በኃጢአት እንደጣላቸው ባለፉት ክፍሎች በተደጋጋሚ አውስተናል፡፡ በአካላዊ ሥጋ ተሰውሮ፥ ለባሕሪይዋ ሐሰትን የሚያማክራት የክፋት መንፈስ ስለመሆኑ ሔዋኒቱ ብታውቅ ኖሮ፥ ምክሩን እንደማትቀበል መቼም ሳይታለም የተፈታ ነው፡፡ ይሄ በሥጋ ጀርባ ተከልሎ የማጥፋት የዲያብሎስ ስልት በዘራችን ተቆራኝቶ፥ ሰዎች ሁሉ በተጨባጭ ለምናየውና ለምንሰማው እየታለልን ከቅድስና መራቅ ዕጣችን ሆነ፡፡

አባቶች ክርስቶስ በሥጋ ሚሥጢርነት ለምን እንደተገለጠ ሲያስረዱ "ሰይጣን ባሳተበት መንገድ ሄዶ ራሱን አሳተው" ይላሉ፡፡ የማይታይና የማይዳሰስ ስውር መንፈስ በሥጋ ተሸፍኖ ከዓመፃው እንዳካፈለን፥ ከሁሉ የተሰወረ እግዚአብሔር ቃል ሥጋ ሆኖ ከቅድስናው አካፈለን፡፡ ሳናውቀው ካጠፋን ጠላት እውቅና በመጥፋት፥ በባሕሪያችን ያስቀመጠውን ጥፋት አጠፋበት፡፡

ዲያቢሎስ ዓለምን በመላ ለመቆጣጠር፥ የታላላቅ ሥልጣኔዎች መሪና አድራጊ እየሆነ፣ የነገሥታትን ሕይወት ከመሠረቱ እየያዘ፣ አምልኮተ እግዚአብሔር ያልተቋረጠባቸውን የቃልኪዳን ሰዎችና ቦታዎች በትኩረት እየተፈታተነ፣ ሰውን ሁሉ ከሕግ በታች ለማድረግ ኃይል ጨምሮ እየሮጠ ባለበት ጊዜ፤ በመጀመሪያ ከእርሱ ዕይታ ርቃ ድንግል ማርያም ተወለደች፡፡ ወላጆቿ ሐና እና ኢያቄም ቅዱሳን የነበሩ፣ በአምልኮተ እግዚአብሔር ላይ ኑሮአቸውን የገነቡ፣ የእግዚአብሔርን እውነትና የተስፋ ኃይል በዘመናቸው የያዙ፣ የወለዷትን አንዲቱ ልጃቸውን ከሦስት ዓመቷ ጀምሮ ለቤተመቅደስ አሳልፈው የሰጡ መሆኑ፥ እግዚአብሔር ድንግል ማርያምን ከመነሻው ጀምሮ ለታላቅ ሥራ እንደመረጣት ያሳያል፡፡ (መዝሙረ ዳዊት 87፥5)

ይህ በእንዲህ እያለ ዲያቢሎስ ዓለምን ሸብቦ ለመያዝ ሌት ተቀን ሲከንፍ፥ ዓለም ውስጥ ያለቺው ማርያም ከዓለም ውጪ ሆና፤ እርሱን ከሚወክለው፣ ከሚስበው፣ ከሚመራውና ከሚያስፈጽመው ኃጢአት በሁለንተናዋ ተጠብቃ፤ በፍጹም የንጽሕና ኑሮ ብትመላለስ፥ እግዚአብሔር አብ አካላዊ ቃሉ ከእርሷ ሥጋ ይነሳ ዘንድ ወደዳት፡፡ እነሆም፥ ሕያው እግዚአብሔር ከዓለም ክፉ ዕውቀትና ኃይል ርቃ፥ ተሰውራ በቆየች ሴት በኩል ከዓለም ርቆ፥ ከሥጋ ዕውቀት ተሰውሮ ተወለደ፡፡ (የዮሐንስ ወንጌል 1፥10)

መድኃኒታችን ከዲያቢሎስ ሚሥጢር ሆኖ በሥጋ በመወለድ፥ ዓላማና ሥራውን እንዳያውቅበት በልዑል ኃይል ጋረደው፡፡ ይሄ ከክፉ መናፍስት ዕይታ ርቆ የተወለደበት ጥበብ እኛንም እንዲወልደን ደግሞ ቃልኪዳኑን አንድም በሥጋና ደሙ ሰጠን፡፡ እንግዲህ "ከእግዚአብሔር የተወለደ ሁሉ ኃጢአትን አያደርግም፥ ዘሩ በእርሱ ይኖራልና" የሚያሰኘው ይሄ ነው፡፡

ሆኖሞ እኛ ከመወለድ አንስቶ በእግዚአብሔር የመንፈስ ቅዱስ ኃይል ተጠብቀን እንዳንወለድ እናቶቻችን ቅዱስ ቁርባን እየወሰዱ አልጸነሱንም፡፡ ስለዚህ በቤተሰብ የኋላ ታሪክ ውስጥ የተለያየ ባዕድ አምልኮ ሲደረግለት የቆየው የግብር መንፈስ፥ በደም ትስስራችን በኩል እያቆራረጠ መጥቶ አብሮን ተጸንሶ አብሮን ተወልዶ አብሮን ያድጋል፡፡ "የዛር መንፈስ" ማለት ከስያሜው በቀላሉ እንደምንገነዘበው፤ በዘር ሐረግ ዘልቆ የሚያልፍ የርኩስ መንፈስ ስም መሆኑ ግልጽ ሆኖ ሳለ፥ ሥልጡን ዘመናችን ይሄን ከግንዛቤው ሳጥን በማውጣቱ ምክንያት ትውልዱ ከማኅፀን ጀምሮ እየተለከፈ ተወልዶ፥ በዕድሜው ሁሉ አልሰምርለት ያለ ከርታታ ሆኖ ይኸው ይሰቃያል፡፡

በነዚህ የዘር መናፍስት ተይዞ መወለዱ ጣጣው ይሄ ብቻ አይደለም፡፡ እናትና አባት የአምልኮተ እግዚአብሔር አኗኗርን ባልመሠረቱበት ኑሮ፥ ያለ ቅዱስ ቁርባን መቀደስ የሚወልዱት ልጅ፤ ከዘራቸው ሲወራረድ በመጣው መንፈስ ተጠቂ ሆኖ ያድጋል፡፡ ይኸው ልጅ፥ እያደገና እየጎለመሰ በሚመጣበት የተፈጥሮ ዑደት ውስጥ አብሮ የተወለደው የዛር መንፈስ ሌሎች የመናፍስት አይነቶችን እየሳበ በማምጣት አሊያ እንዲገቡ ጥሪ በማድረግ፤ ግለሰቡን የርኩሳን መናፍስት ዋሻ ያደርገዋል፡፡

በሐዲስ ኪዳን ግን፥ የመልአኩ ቃል "የልዑል ኃይል ይልልሻል" ካለ በኋላ "ስለዚህ የሚወለደው የእግዚአብሔር ልጅ ይባላል" ሲል ነበረ የተናገረው፡፡ ይሄ ንግግር የተቀደሰ ልጅ ወላጅ መሆንን ለሚፈልጉ ሁሉ ቢደገም እንዲህ ሊጻፍ ይችላል፦ "የመንፈስ ቅዱስ ኃይል ሲያድርባችሁ፥ የምትወልዱት ሁሉ የእግዚአብሔር ልጅ ይሆናል"፡፡

የገብርኤል መልእክት ለሰው ልጆች ባሕሪይ ሁሉ የተላከ ብሥራት መሆኑን እኛ ሳናስተውል፤ "በቅዱስ ቁርባን ኃይል በኩል ተጸልሎ የተወለደ ሁሉ የእግዚአብሔር ልጅ ይሆናል" የሚለው የኛ የጸጋ ልጅነት ስጦታ ሳይገባን፤ ካለ ሥጋና ደሙ የሚጸነሰው ልጅ ላይ የዛር መንፈስ ጸልሎበት፥ የሚወለደው የዲያቢሎስ ልጅ እየሆነ፤ ትውልዳችን ባልተረዳው መንፈሳዊ ባላጋራ ዘመኑን ተነጥቆ፥ እንደ የተናጠልም እንደ የጋራም እየተጨነቅን የክፉ ትንቢት መግለጫዎች ለመሆን ተገድደናል፡፡

ሁላችን በአጽንዖት እንድናስተውል የሚገባው፥ በመንፈስ ቅዱስ ኃይል ተጸንሰን ካልተወለድን፥ በመንፈስ ርኩስ ኃይል እንወለድ ዘንድ ያለው ዕድል ቀሪ አማራጭ ሆኖ እንደሚጠብቀን ነው፡፡ ዓለም ሦስተኛ ምርጫ የላትም ከብርሃን ካልሆንን ጨለማ ውስጥ ነን፡፡ ክፉውን ካልተቃወምን በመልካሙ አንመላለስም፡፡ ለፍቅር አንገዛም ስንል በጥላቻ የሚገዛን አለ፡፡



tgoop.com/bemaledanek/2425
Create:
Last Update:

3•  ቅዱስ ቁርባን

   ከክፍል - ፮ የቀጠለ..

ወደ ጀመርነው ሀሳባችን እንመለስ፡፡ መልአኩ ለድንግል ማርያም "ደስ ይበልሽ ጌታ ካንቺ ጋር ነው" ብሎ አላበቃም፡፡ እንዴት እንደምትወልድ ጭምር ይነግራታል፡፡ ከተለመደው የሥጋ ፈቃድ ውጪ የምትጸንስበትን ጥበብ ያሳውቃታል፡፡ "መንፈስ ቅዱስ በአንቺ ላይ ይመጣል፥ የልዑልም ኃይል ይጸልልሻል ስለዚህ ደግሞ ከአንቺ የሚወለደው ቅዱስ የእግዚአብሔር ልጅ ይባላል" አላት፡፡

እዚህ ጋር በደንብ እናስተውል፡፡ "ከአንቺ የሚወለደው" ከሚለው በፊት የተጻፈው "መንፈስ ቅዱስ ባንቺ ላይ ይመጣል፥ የልዑልም ኃይል ይጸልልሻል" የሚለው ነው፡፡ መድኃኒታችን ከመጸነሱ አስቀድሞ የመንፈስ ቅዱስ ኃይል በእመቤታችን ላይ መጥቶአል፥ የልዑልም ኃይል ጸልሎአት አርፎአል፡፡ 'መጸለል' የሚለው ቃል አውዳዊ ፍቺው 'መጋረድ፣ መከለል፣ መጠበቅ' የሚል ትርጉም ይኖረዋል፡፡ በመሆኑም ረቂቅ የእግዚአብሔር ልጅ በምድራዊው ዓለም በግዙፍ ሥጋ ከመገለጡ አስቀድሞ የድንግሊቱን ውሳጣዊ ሕይወት ከኃጢአት ጠብቆ ማደሪያ ሲያደርገው፥ ውጪያዊ ሰውነቷን ደግሞ በመንፈስ ቅዱስ ኃይል ጋርዶታል፡፡

መንፈስ ቅዱስ በድንግል ማርያም እሳተ ክበብ ሆኖ እንደ መጋረጃ ሲከድናት፥ ቃል ሥጋ የመሆኑ ጥበብ ሚሥጢር ሆነ፡፡ የመለኮት ባሕሪይ የሰውነትን ባሕሪይ በተዋሕዶ ገንዘብ ማድረጉ 'ሚሥጥረ ሥጋዌ' የተባለው፥ ይህ ልዩ የእግዚአብሔር ጥበብ በፍጡራን ልዕልና ለመመርመርና ለመታወቅ ባለመቻሉ ነው፡፡ የልዑል ኃይል በብላቴናይቱ ላይ ከጸለለ በኋላ፥ ከዓለም የእውቅና መረጃ ርቆ የእግዚአብሔር ልጅ የሰው ልጅ ሆነ፡፡ ለመሆኑ የወልደ እግዚአብሔር በሥጋ መገለጥ ስለምን ሚሥጢር ሆነ?

      "ኃጢአትን የሚያደርግ ከዲያብሎስ ነው፥ ዲያብሎስ ከመጀመሪያ ኃጢአትን ያደርጋልና። ስለዚህ የዲያብሎስን ሥራ እንዲያፈርስ የእግዚአብሔር ልጅ ተገለጠ። ከእግዚአብሔር የተወለደ ሁሉ ኃጢአትን አያደርግም፥ ዘሩ በእርሱ ይኖራልና፤ ከእግዚአብሔርም ተወልዶአልና ኃጢአትን ሊያደርግ አይችልም።"

                                              (1ኛ የዮሐንስ መልእክት 3፥8-9)

ዲያቢሎስ ወደነአዳም በእባብ ሥጋ ተደብቆ በመሄድ በኃጢአት እንደጣላቸው ባለፉት ክፍሎች በተደጋጋሚ አውስተናል፡፡ በአካላዊ ሥጋ ተሰውሮ፥ ለባሕሪይዋ ሐሰትን የሚያማክራት የክፋት መንፈስ ስለመሆኑ ሔዋኒቱ ብታውቅ ኖሮ፥ ምክሩን እንደማትቀበል መቼም ሳይታለም የተፈታ ነው፡፡ ይሄ በሥጋ ጀርባ ተከልሎ የማጥፋት የዲያብሎስ ስልት በዘራችን ተቆራኝቶ፥ ሰዎች ሁሉ በተጨባጭ ለምናየውና ለምንሰማው እየታለልን ከቅድስና መራቅ ዕጣችን ሆነ፡፡

አባቶች ክርስቶስ በሥጋ ሚሥጢርነት ለምን እንደተገለጠ ሲያስረዱ "ሰይጣን ባሳተበት መንገድ ሄዶ ራሱን አሳተው" ይላሉ፡፡ የማይታይና የማይዳሰስ ስውር መንፈስ በሥጋ ተሸፍኖ ከዓመፃው እንዳካፈለን፥ ከሁሉ የተሰወረ እግዚአብሔር ቃል ሥጋ ሆኖ ከቅድስናው አካፈለን፡፡ ሳናውቀው ካጠፋን ጠላት እውቅና በመጥፋት፥ በባሕሪያችን ያስቀመጠውን ጥፋት አጠፋበት፡፡

ዲያቢሎስ ዓለምን በመላ ለመቆጣጠር፥ የታላላቅ ሥልጣኔዎች መሪና አድራጊ እየሆነ፣ የነገሥታትን ሕይወት ከመሠረቱ እየያዘ፣ አምልኮተ እግዚአብሔር ያልተቋረጠባቸውን የቃልኪዳን ሰዎችና ቦታዎች በትኩረት እየተፈታተነ፣ ሰውን ሁሉ ከሕግ በታች ለማድረግ ኃይል ጨምሮ እየሮጠ ባለበት ጊዜ፤ በመጀመሪያ ከእርሱ ዕይታ ርቃ ድንግል ማርያም ተወለደች፡፡ ወላጆቿ ሐና እና ኢያቄም ቅዱሳን የነበሩ፣ በአምልኮተ እግዚአብሔር ላይ ኑሮአቸውን የገነቡ፣ የእግዚአብሔርን እውነትና የተስፋ ኃይል በዘመናቸው የያዙ፣ የወለዷትን አንዲቱ ልጃቸውን ከሦስት ዓመቷ ጀምሮ ለቤተመቅደስ አሳልፈው የሰጡ መሆኑ፥ እግዚአብሔር ድንግል ማርያምን ከመነሻው ጀምሮ ለታላቅ ሥራ እንደመረጣት ያሳያል፡፡ (መዝሙረ ዳዊት 87፥5)

ይህ በእንዲህ እያለ ዲያቢሎስ ዓለምን ሸብቦ ለመያዝ ሌት ተቀን ሲከንፍ፥ ዓለም ውስጥ ያለቺው ማርያም ከዓለም ውጪ ሆና፤ እርሱን ከሚወክለው፣ ከሚስበው፣ ከሚመራውና ከሚያስፈጽመው ኃጢአት በሁለንተናዋ ተጠብቃ፤ በፍጹም የንጽሕና ኑሮ ብትመላለስ፥ እግዚአብሔር አብ አካላዊ ቃሉ ከእርሷ ሥጋ ይነሳ ዘንድ ወደዳት፡፡ እነሆም፥ ሕያው እግዚአብሔር ከዓለም ክፉ ዕውቀትና ኃይል ርቃ፥ ተሰውራ በቆየች ሴት በኩል ከዓለም ርቆ፥ ከሥጋ ዕውቀት ተሰውሮ ተወለደ፡፡ (የዮሐንስ ወንጌል 1፥10)

መድኃኒታችን ከዲያቢሎስ ሚሥጢር ሆኖ በሥጋ በመወለድ፥ ዓላማና ሥራውን እንዳያውቅበት በልዑል ኃይል ጋረደው፡፡ ይሄ ከክፉ መናፍስት ዕይታ ርቆ የተወለደበት ጥበብ እኛንም እንዲወልደን ደግሞ ቃልኪዳኑን አንድም በሥጋና ደሙ ሰጠን፡፡ እንግዲህ "ከእግዚአብሔር የተወለደ ሁሉ ኃጢአትን አያደርግም፥ ዘሩ በእርሱ ይኖራልና" የሚያሰኘው ይሄ ነው፡፡

ሆኖሞ እኛ ከመወለድ አንስቶ በእግዚአብሔር የመንፈስ ቅዱስ ኃይል ተጠብቀን እንዳንወለድ እናቶቻችን ቅዱስ ቁርባን እየወሰዱ አልጸነሱንም፡፡ ስለዚህ በቤተሰብ የኋላ ታሪክ ውስጥ የተለያየ ባዕድ አምልኮ ሲደረግለት የቆየው የግብር መንፈስ፥ በደም ትስስራችን በኩል እያቆራረጠ መጥቶ አብሮን ተጸንሶ አብሮን ተወልዶ አብሮን ያድጋል፡፡ "የዛር መንፈስ" ማለት ከስያሜው በቀላሉ እንደምንገነዘበው፤ በዘር ሐረግ ዘልቆ የሚያልፍ የርኩስ መንፈስ ስም መሆኑ ግልጽ ሆኖ ሳለ፥ ሥልጡን ዘመናችን ይሄን ከግንዛቤው ሳጥን በማውጣቱ ምክንያት ትውልዱ ከማኅፀን ጀምሮ እየተለከፈ ተወልዶ፥ በዕድሜው ሁሉ አልሰምርለት ያለ ከርታታ ሆኖ ይኸው ይሰቃያል፡፡

በነዚህ የዘር መናፍስት ተይዞ መወለዱ ጣጣው ይሄ ብቻ አይደለም፡፡ እናትና አባት የአምልኮተ እግዚአብሔር አኗኗርን ባልመሠረቱበት ኑሮ፥ ያለ ቅዱስ ቁርባን መቀደስ የሚወልዱት ልጅ፤ ከዘራቸው ሲወራረድ በመጣው መንፈስ ተጠቂ ሆኖ ያድጋል፡፡ ይኸው ልጅ፥ እያደገና እየጎለመሰ በሚመጣበት የተፈጥሮ ዑደት ውስጥ አብሮ የተወለደው የዛር መንፈስ ሌሎች የመናፍስት አይነቶችን እየሳበ በማምጣት አሊያ እንዲገቡ ጥሪ በማድረግ፤ ግለሰቡን የርኩሳን መናፍስት ዋሻ ያደርገዋል፡፡

በሐዲስ ኪዳን ግን፥ የመልአኩ ቃል "የልዑል ኃይል ይልልሻል" ካለ በኋላ "ስለዚህ የሚወለደው የእግዚአብሔር ልጅ ይባላል" ሲል ነበረ የተናገረው፡፡ ይሄ ንግግር የተቀደሰ ልጅ ወላጅ መሆንን ለሚፈልጉ ሁሉ ቢደገም እንዲህ ሊጻፍ ይችላል፦ "የመንፈስ ቅዱስ ኃይል ሲያድርባችሁ፥ የምትወልዱት ሁሉ የእግዚአብሔር ልጅ ይሆናል"፡፡

የገብርኤል መልእክት ለሰው ልጆች ባሕሪይ ሁሉ የተላከ ብሥራት መሆኑን እኛ ሳናስተውል፤ "በቅዱስ ቁርባን ኃይል በኩል ተጸልሎ የተወለደ ሁሉ የእግዚአብሔር ልጅ ይሆናል" የሚለው የኛ የጸጋ ልጅነት ስጦታ ሳይገባን፤ ካለ ሥጋና ደሙ የሚጸነሰው ልጅ ላይ የዛር መንፈስ ጸልሎበት፥ የሚወለደው የዲያቢሎስ ልጅ እየሆነ፤ ትውልዳችን ባልተረዳው መንፈሳዊ ባላጋራ ዘመኑን ተነጥቆ፥ እንደ የተናጠልም እንደ የጋራም እየተጨነቅን የክፉ ትንቢት መግለጫዎች ለመሆን ተገድደናል፡፡

ሁላችን በአጽንዖት እንድናስተውል የሚገባው፥ በመንፈስ ቅዱስ ኃይል ተጸንሰን ካልተወለድን፥ በመንፈስ ርኩስ ኃይል እንወለድ ዘንድ ያለው ዕድል ቀሪ አማራጭ ሆኖ እንደሚጠብቀን ነው፡፡ ዓለም ሦስተኛ ምርጫ የላትም ከብርሃን ካልሆንን ጨለማ ውስጥ ነን፡፡ ክፉውን ካልተቃወምን በመልካሙ አንመላለስም፡፡ ለፍቅር አንገዛም ስንል በጥላቻ የሚገዛን አለ፡፡

BY በማለዳ ንቁ ቁጥር ! ፪


Share with your friend now:
tgoop.com/bemaledanek/2425

View MORE
Open in Telegram


Telegram News

Date: |

How to create a business channel on Telegram? (Tutorial) ‘Ban’ on Telegram How to Create a Private or Public Channel on Telegram? Your posting frequency depends on the topic of your channel. If you have a news channel, it’s OK to publish new content every day (or even every hour). For other industries, stick with 2-3 large posts a week.
from us


Telegram በማለዳ ንቁ ቁጥር ! ፪
FROM American