BEMALEDANEK Telegram 2751
በማለዳ ንቁ ቁጥር ! ፪
3•  ቅዱስ ቁርባን    ከክፍል - ፮ የቀጠለ.. ወደ ጀመርነው ሀሳባችን እንመለስ፡፡ መልአኩ ለድንግል ማርያም "ደስ ይበልሽ ጌታ ካንቺ ጋር ነው" ብሎ አላበቃም፡፡ እንዴት እንደምትወልድ ጭምር ይነግራታል፡፡ ከተለመደው የሥጋ ፈቃድ ውጪ የምትጸንስበትን ጥበብ ያሳውቃታል፡፡ "መንፈስ ቅዱስ በአንቺ ላይ ይመጣል፥ የልዑልም ኃይል ይጸልልሻል ስለዚህ ደግሞ ከአንቺ የሚወለደው ቅዱስ የእግዚአብሔር ልጅ ይባላል"…
3•  ቅዱስ ቁርባን

  ክፍል - ፯

       3.3•  የመናፍስት ውጊያ በቅዱስ ቁርባን ላይ

ውድቀትን በባሕሪዩ የተጣባት ክፉ መንፈስ "አምላክ እኔ ነኝ" ሲል ዋሽቷል፡፡ እንደ ፈጣሪ መሆን ተስፋ አልቆርጥ ያለ ምኞቱ ነው፡፡ ስለዚህ እግዚአብሔር ወዳስገኛቸው እያመለከተ "የእኔ ናቸው" ማለትን ከጥንት ጀምሯታል፡፡ የሰውን ልጅ ጭምር!

ሰውነት ቤተመቅደስነት እንደሆነ ተነጋግረናል፡፡ ዲያቢሎስ በዚህ ቤተመቅደስ ውስጥ ነው መመለክ የሚፈልገው፡፡ የሰውን ልጅ መግዛት፣ መቆጣጠር ይፈልጋል፡፡ ልክ እንደ አምላክ "ይሄን ይሄን አትንኩ" የሚላቸውን ትእዛዛት ያሰቀምጣል፡፡ እርሱ እንደፈቀደው እንዴት መኖር እንዲገባን ደንብና ሥርዓት የሚያሳዩ ሕግጋት ያረቃል፡፡ ከእግዚአብሔር በተቃራኒ የሚሠራ መንፈስ እንደሆነ ሲታወቅ፥ ሕግ አድርጎ የሚያስቀምጣቸው ትእዛዛቱ የእግዚአብሔርን እንደሚጻረሩ እንዲሁ ለመገመት አይከብድም፡፡ ጽድቅን የሚጠሩና በጽድቅ የሚያኖሩ ማንኛቸውንም ነገራት አትንኩ ይላል፡፡

ይሄ የክፋት ኃይል አዳምን ካሳተ በኋላ ዓለምን በመላ በራሱ መስመርና ዓላማ ለመምራት ያለመታከት ሲደክም ዘመናትን አሳልፏል፡፡ ተሳክቶለትም የምድር ማዕዘናት ጽድቅን በሚቃወሙ፣ በሥጋ ድክመት ላይ በሚመኩ ሥርዓቶች እንዲተዳደሩ አስገድዷል፡፡ ከዚህም የተነሳ በምድራችን የአስተሳሰብና የኑሮ ሚዛን ቅዱስ የሆኑት ከብደው፥ ርኩሳኑ በእጅጉ ቀልለውና በዝተው ይገኛሉ፡፡

ለዚህ በቂ ማሳያ አድርገን የምንናነሳው ርእሳችንን፥ የአዲስ ኪዳኑን አማናዊ ቃልኪዳን፥ የመድኃኒታችንን ሥጋና ደም ነው፡፡

[በተለይ] ባለንበት በዚህ ዘመን፥ ቅዱስ ቁርባን ሲባል የሚጠራው የኪዳኑ ስጦታ ከሰዎች ሕይወት በእጅጉ የራቀ ጉዳይ እንደሆነ የሚታወቅ ነው፡፡ ከታዳጊነት እስከ መካከለኛው የዕድሜ እርከን ያሉ ብዙ አማንያን፥ ከሰማያዊው ማዕድ መካፈል ካቆሙ ሰነባብተዋል፡፡ ቅዱስ ቁርባን በእርጅና ጊዜ የሚወሰድ ልምዳዊ ድርጊት ወደ መሆን ከመጣ ቆየት ብሏል፡፡ ሕፃናት እስከ ዐሥራ መጀመሪያዎቹ ይቆርባሉ፤ ከዛ ሥጋና ደሙ የጠፋ እስኪመሰል ከቁርባን ጠፍተው ያድጋሉ፡፡
 
በመሆኑ ብዙው ሰው፥ "አንቱ በመቁረቢያ ዕድሜዎት እንዲህ ያደርጋሉ እንዴ?" እስከሚባልበት የጊዜ ማምሻ ድረስ ሕይወት እንደመራው፥ ኑሮ እየጣለው፥ እርሱም ሌላውን እየጣለ፥ የነፍስ እውነትን ረስቶ ይቆይና፤ የዕድሜ በረከት አግኝቶ ለሽበት ሲደርስ ቅዱስ ቁርባን ይቀበላል፡፡ ለዚህ ካልታደለም በዛው ጥቁር ጸጉር ሳለ፥ ጥቁር ኃጢአትና ጨለማ ዘመን ወርሶት፥ "ሥጋዬን የሚበላ ደሜንም የሚጠጣ እኔ በእርሱ እኖራለሁ እርሱም በእኔ ይኖራል" ያለውን፥ የክርስቶስን ወዳጅነት በወጣትነቱ ሳያገኘው ወደ መቃብር ይሸኛል፡፡

ለመሆኑ ይሄ የሆነው ለምንድነው? ስለ ቅዱስ ቁርባን ስንማር የቆየነው ቃል ምንድን ነው? በውስጣችን ተቀርጾ ያለው መንፈሳዊ ትምህርት ምን አይነት ነው? እንዴት ነው ክርስትናን የተረዳነው? የመጽሐፍ ቅዱስን ቃላት እንዴት ነው የምንመለከታቸው? ክርስቶስ በመስቀል ላይ ሞቶ ሞትን ድል ነሥቶ የዘላለም ሕይወት ሰጠን የሚለውን የድኅነት አገላለጽ እንዴት ነው የተገነዘብነው?

ክርስቲያኖች ነን ስንል መቼም በክርስቶስ አምነን ነው፡፡ በክርስቶስ ስናምን፥ የተናገራቸውን የታመኑ ቃላት እናምናለን ማለት ይሆናል፡፡ እንግዲያው "እንካችሁ፥ ብሉ ይሄ ሥጋዬ ነው፤ ሁላችሁም ከእርሱ ጠጡ፤ ስለ ብዙዎች ኃጢአት የሚፈስ የአዲስ ኪዳን ደሜ ይሄ ነው" ያለውን ቃል እንዴት ነው ያመንነው?

"ሰው ዓለሙን ሁሉ አትርፎ ነፍሱን ግን ቢያጎድል ምን ይጠቅመዋል?" የሚለው ንግግር የቅዱስ ቁርባን ልክ ይዞ ቢነገር "ክርስቲያን ነገርን ሁሉ አድርጎ የክርስቶስን ሥጋና ደም ካልተቀበለ ምን ይበጀዋል?" ሊባል ይችላል፡፡ ይህም ማለት እንኳን ዓለማዊ፥ መንፈሳዊ ጉዳዮችን ሁሉ ምእመናን አድርገው፥ ከሥጋና ደሙ ጋር ባወቀ ካልተገናኙ ትልቁን ዋጋ አጥተውታል ማለት ነው፡፡ አስተምህሮቱ "የሚሥጢራት ሁሉ ፍጻሜ ቅዱስ ቁርባን ነው" እያለ የሚያውጀው ለዚህ ነው፡፡

ታዲያ ምንድነው የምናስበው? ምንድነው ከውስጣችን ቆይቶ ለዘመናት የገዛን አመለካከት? ስለ ዘላለም ሕይወት ያለን መንፈሳዊ እይታ ርቀቱ እስከየት ይጠልቃል? ስለ መቁረብ ስናስብ ምንድነው ወደ ጭንቅላታችን አስቀድሞ የሚመጣው?
  
ብዙ ክርስቲያኖች ለቅዳሴ ይቆማሉ፡፡ የሚቆርቡት ግን ከሕፃናትና ከአዛውንት ውጪ ከእጅ ጣቶች የማይበልጡ ጥቂቶች ናቸው፡፡ ይሄም ነገር የተለመደ ከመሆን አልፎ አሁን ያልተለመደው የወጣቶች ከሕይወት እንጀራ መቁረስ ሆኗል፡፡ ለምንድነው ነው እንደዚህ የሆነው? ለምንድነው ወጣቶች ከክርስቶስ ሥጋና ደም የማይቀበሉት? ለምንድነው መምህራን ስለዚህ ነገር አበክረው የማያሳስቡት? የሚያሳስቡትንስ፥ አማኙ ሕብረተሰብ የማይሰማቸው ለምንድነው?

ሥርዓተ ቅዳሴ ያለ ቅዱስ ቁርባን መሥዋዕት ቅዳሴ ይባል ዘንድ አይችልም፡፡ ዝርዝር ትንታኔ ውስጥም ሳንገባ ከስያሜው ብንጀምር "ቅዳሴ" የሚለው ቃል የሚጠቁመው አንድን ነገር የመቀደስ ሂደት ነው፡፡ ያ በምስጋና፣ በአምልኮትና በኅብረት ጸሎት የሚቀደሰው ነገር ሕብሥተ ስንዴው እና ሕብሥተ ወይኑ ነው፡፡ የተቀደሰው ማዕድ ከዛ በእምነት የሚወስዱትን ሁሉ ይቀድሳቸዋል፡፡ ከቤተልሔም እስከ ቀራኒዮ የሚገሰግሰው ቅዳሴ፥ ዋነኛ አንድምታው ይሄ ነው፡፡

ቅዳሴ የአዲስ ኪዳን ቃልኪዳን የሚፈጽምበት ሰማያዊ ሥርዓት ነው መባሉ በክርስቶስ ሥጋና ደም ምክንያት ነው፡፡ ያለ ቅዱስ ቁርባን ቅዳሴ የለም፡፡ በዚህ መሠረት ቅዳሴ አስቀድሰን ከተቀደሰው ምግብና መጠጥ የማንሳተፍ ሰዎች፥ ምን ቀድሰንና በምን ተቀድሰን እንደተመለስን ያልታወቀበት ቆይታ አድርገን ነው የመጣነው ማለት ነው፡፡

ሱታፌ ቅዳሴ ኖሮ ከቅዱስ ቁርባን አለመቀበል አግባብ እንዳልሆነ የቤተክርስቲያን አያሌ ሥርዓተ መጽሐፍት በግልጽ ይደነግጋሉ፡፡ ሌላውን እንተወውና ራሱ ቅዳሴ ከቅዱስ ቁርባን [በፍትሐ ነገሥት ከተዘረዘሩ በቂ ምክንያቶች ውጪ] ሥጋና ደሙን አለመቀበል የአምላክን ትእዛዝ መተላለፍ ስለመሆኑ ገና በመግቢያው ክፍል ላይ ያስጠነቅቃል፦

        "በቅዳሴ ጊዜ የሚገኙ ምእመናን፥ መጽሐፍተ ቅዱሳትን ባይሰሙ፣ ቅዳሴ እስኪፈጸም ድረስ ባይታገሡና ከቁርባንም ባይቀበሉ ከቤተክርስቲያን ይሰደዱ፤ ሕገ እግዚአብሔርን አፍርሰዋልና"

                                                        መጽሐፈ ቅዳሴ

የቅዳሴ ብቻ ሳይሆን የንስሐም አድራሻ ቅዱስ ቁርባን ነው፡፡ "በአዲሱ አቁማዳ አዲሱ ወይን ሊሞላ ይገባል" የሚለውን የጌታ ትእዛዝ ይዛ፥ ቤተክርስቲያን ማንኛውም ግለሰብ ሥጋና ደሙን ከመቀበሉ በፊት ንስሐ እንዲገባ ታዝዛለች፡፡ በመሆኑ ቅዳሴ ያስቀደሰ ሰው መቁረብ እንዲገባው ሁሉ፥ ንስሐውን የጨረሰ አማኝም ቅዱስ ቁርባንን መቀበል ምርጫው አይደለም፡፡ የውዴታ ግዴታው ነው፡፡ ጸድቶ የተቀመጠ ብርጭቆ ለታጠበለት አገልግሎት ካልዋለ፥ ቆሽሾ ከተቀመጠው ብርጭቆ ከመታጠቡ ባሻገር አልተለየም፡፡ ንስሐ የገባም አንድ ሰው፥ ከእግዚአብሔር መንግሥተ ማዕድ ተካፍሎ የዘላለም ሕይወትን የቃልኪዳን ማኅተም በሰውነቱ እስካልያዘ ድረስ የንስሐውን አገልግሎት ከግብ አላደረሰም፡፡ (የዮሐንስ ወንጌል 6፥51)



tgoop.com/bemaledanek/2751
Create:
Last Update:

3•  ቅዱስ ቁርባን

  ክፍል - ፯

       3.3•  የመናፍስት ውጊያ በቅዱስ ቁርባን ላይ

ውድቀትን በባሕሪዩ የተጣባት ክፉ መንፈስ "አምላክ እኔ ነኝ" ሲል ዋሽቷል፡፡ እንደ ፈጣሪ መሆን ተስፋ አልቆርጥ ያለ ምኞቱ ነው፡፡ ስለዚህ እግዚአብሔር ወዳስገኛቸው እያመለከተ "የእኔ ናቸው" ማለትን ከጥንት ጀምሯታል፡፡ የሰውን ልጅ ጭምር!

ሰውነት ቤተመቅደስነት እንደሆነ ተነጋግረናል፡፡ ዲያቢሎስ በዚህ ቤተመቅደስ ውስጥ ነው መመለክ የሚፈልገው፡፡ የሰውን ልጅ መግዛት፣ መቆጣጠር ይፈልጋል፡፡ ልክ እንደ አምላክ "ይሄን ይሄን አትንኩ" የሚላቸውን ትእዛዛት ያሰቀምጣል፡፡ እርሱ እንደፈቀደው እንዴት መኖር እንዲገባን ደንብና ሥርዓት የሚያሳዩ ሕግጋት ያረቃል፡፡ ከእግዚአብሔር በተቃራኒ የሚሠራ መንፈስ እንደሆነ ሲታወቅ፥ ሕግ አድርጎ የሚያስቀምጣቸው ትእዛዛቱ የእግዚአብሔርን እንደሚጻረሩ እንዲሁ ለመገመት አይከብድም፡፡ ጽድቅን የሚጠሩና በጽድቅ የሚያኖሩ ማንኛቸውንም ነገራት አትንኩ ይላል፡፡

ይሄ የክፋት ኃይል አዳምን ካሳተ በኋላ ዓለምን በመላ በራሱ መስመርና ዓላማ ለመምራት ያለመታከት ሲደክም ዘመናትን አሳልፏል፡፡ ተሳክቶለትም የምድር ማዕዘናት ጽድቅን በሚቃወሙ፣ በሥጋ ድክመት ላይ በሚመኩ ሥርዓቶች እንዲተዳደሩ አስገድዷል፡፡ ከዚህም የተነሳ በምድራችን የአስተሳሰብና የኑሮ ሚዛን ቅዱስ የሆኑት ከብደው፥ ርኩሳኑ በእጅጉ ቀልለውና በዝተው ይገኛሉ፡፡

ለዚህ በቂ ማሳያ አድርገን የምንናነሳው ርእሳችንን፥ የአዲስ ኪዳኑን አማናዊ ቃልኪዳን፥ የመድኃኒታችንን ሥጋና ደም ነው፡፡

[በተለይ] ባለንበት በዚህ ዘመን፥ ቅዱስ ቁርባን ሲባል የሚጠራው የኪዳኑ ስጦታ ከሰዎች ሕይወት በእጅጉ የራቀ ጉዳይ እንደሆነ የሚታወቅ ነው፡፡ ከታዳጊነት እስከ መካከለኛው የዕድሜ እርከን ያሉ ብዙ አማንያን፥ ከሰማያዊው ማዕድ መካፈል ካቆሙ ሰነባብተዋል፡፡ ቅዱስ ቁርባን በእርጅና ጊዜ የሚወሰድ ልምዳዊ ድርጊት ወደ መሆን ከመጣ ቆየት ብሏል፡፡ ሕፃናት እስከ ዐሥራ መጀመሪያዎቹ ይቆርባሉ፤ ከዛ ሥጋና ደሙ የጠፋ እስኪመሰል ከቁርባን ጠፍተው ያድጋሉ፡፡
 
በመሆኑ ብዙው ሰው፥ "አንቱ በመቁረቢያ ዕድሜዎት እንዲህ ያደርጋሉ እንዴ?" እስከሚባልበት የጊዜ ማምሻ ድረስ ሕይወት እንደመራው፥ ኑሮ እየጣለው፥ እርሱም ሌላውን እየጣለ፥ የነፍስ እውነትን ረስቶ ይቆይና፤ የዕድሜ በረከት አግኝቶ ለሽበት ሲደርስ ቅዱስ ቁርባን ይቀበላል፡፡ ለዚህ ካልታደለም በዛው ጥቁር ጸጉር ሳለ፥ ጥቁር ኃጢአትና ጨለማ ዘመን ወርሶት፥ "ሥጋዬን የሚበላ ደሜንም የሚጠጣ እኔ በእርሱ እኖራለሁ እርሱም በእኔ ይኖራል" ያለውን፥ የክርስቶስን ወዳጅነት በወጣትነቱ ሳያገኘው ወደ መቃብር ይሸኛል፡፡

ለመሆኑ ይሄ የሆነው ለምንድነው? ስለ ቅዱስ ቁርባን ስንማር የቆየነው ቃል ምንድን ነው? በውስጣችን ተቀርጾ ያለው መንፈሳዊ ትምህርት ምን አይነት ነው? እንዴት ነው ክርስትናን የተረዳነው? የመጽሐፍ ቅዱስን ቃላት እንዴት ነው የምንመለከታቸው? ክርስቶስ በመስቀል ላይ ሞቶ ሞትን ድል ነሥቶ የዘላለም ሕይወት ሰጠን የሚለውን የድኅነት አገላለጽ እንዴት ነው የተገነዘብነው?

ክርስቲያኖች ነን ስንል መቼም በክርስቶስ አምነን ነው፡፡ በክርስቶስ ስናምን፥ የተናገራቸውን የታመኑ ቃላት እናምናለን ማለት ይሆናል፡፡ እንግዲያው "እንካችሁ፥ ብሉ ይሄ ሥጋዬ ነው፤ ሁላችሁም ከእርሱ ጠጡ፤ ስለ ብዙዎች ኃጢአት የሚፈስ የአዲስ ኪዳን ደሜ ይሄ ነው" ያለውን ቃል እንዴት ነው ያመንነው?

"ሰው ዓለሙን ሁሉ አትርፎ ነፍሱን ግን ቢያጎድል ምን ይጠቅመዋል?" የሚለው ንግግር የቅዱስ ቁርባን ልክ ይዞ ቢነገር "ክርስቲያን ነገርን ሁሉ አድርጎ የክርስቶስን ሥጋና ደም ካልተቀበለ ምን ይበጀዋል?" ሊባል ይችላል፡፡ ይህም ማለት እንኳን ዓለማዊ፥ መንፈሳዊ ጉዳዮችን ሁሉ ምእመናን አድርገው፥ ከሥጋና ደሙ ጋር ባወቀ ካልተገናኙ ትልቁን ዋጋ አጥተውታል ማለት ነው፡፡ አስተምህሮቱ "የሚሥጢራት ሁሉ ፍጻሜ ቅዱስ ቁርባን ነው" እያለ የሚያውጀው ለዚህ ነው፡፡

ታዲያ ምንድነው የምናስበው? ምንድነው ከውስጣችን ቆይቶ ለዘመናት የገዛን አመለካከት? ስለ ዘላለም ሕይወት ያለን መንፈሳዊ እይታ ርቀቱ እስከየት ይጠልቃል? ስለ መቁረብ ስናስብ ምንድነው ወደ ጭንቅላታችን አስቀድሞ የሚመጣው?
  
ብዙ ክርስቲያኖች ለቅዳሴ ይቆማሉ፡፡ የሚቆርቡት ግን ከሕፃናትና ከአዛውንት ውጪ ከእጅ ጣቶች የማይበልጡ ጥቂቶች ናቸው፡፡ ይሄም ነገር የተለመደ ከመሆን አልፎ አሁን ያልተለመደው የወጣቶች ከሕይወት እንጀራ መቁረስ ሆኗል፡፡ ለምንድነው ነው እንደዚህ የሆነው? ለምንድነው ወጣቶች ከክርስቶስ ሥጋና ደም የማይቀበሉት? ለምንድነው መምህራን ስለዚህ ነገር አበክረው የማያሳስቡት? የሚያሳስቡትንስ፥ አማኙ ሕብረተሰብ የማይሰማቸው ለምንድነው?

ሥርዓተ ቅዳሴ ያለ ቅዱስ ቁርባን መሥዋዕት ቅዳሴ ይባል ዘንድ አይችልም፡፡ ዝርዝር ትንታኔ ውስጥም ሳንገባ ከስያሜው ብንጀምር "ቅዳሴ" የሚለው ቃል የሚጠቁመው አንድን ነገር የመቀደስ ሂደት ነው፡፡ ያ በምስጋና፣ በአምልኮትና በኅብረት ጸሎት የሚቀደሰው ነገር ሕብሥተ ስንዴው እና ሕብሥተ ወይኑ ነው፡፡ የተቀደሰው ማዕድ ከዛ በእምነት የሚወስዱትን ሁሉ ይቀድሳቸዋል፡፡ ከቤተልሔም እስከ ቀራኒዮ የሚገሰግሰው ቅዳሴ፥ ዋነኛ አንድምታው ይሄ ነው፡፡

ቅዳሴ የአዲስ ኪዳን ቃልኪዳን የሚፈጽምበት ሰማያዊ ሥርዓት ነው መባሉ በክርስቶስ ሥጋና ደም ምክንያት ነው፡፡ ያለ ቅዱስ ቁርባን ቅዳሴ የለም፡፡ በዚህ መሠረት ቅዳሴ አስቀድሰን ከተቀደሰው ምግብና መጠጥ የማንሳተፍ ሰዎች፥ ምን ቀድሰንና በምን ተቀድሰን እንደተመለስን ያልታወቀበት ቆይታ አድርገን ነው የመጣነው ማለት ነው፡፡

ሱታፌ ቅዳሴ ኖሮ ከቅዱስ ቁርባን አለመቀበል አግባብ እንዳልሆነ የቤተክርስቲያን አያሌ ሥርዓተ መጽሐፍት በግልጽ ይደነግጋሉ፡፡ ሌላውን እንተወውና ራሱ ቅዳሴ ከቅዱስ ቁርባን [በፍትሐ ነገሥት ከተዘረዘሩ በቂ ምክንያቶች ውጪ] ሥጋና ደሙን አለመቀበል የአምላክን ትእዛዝ መተላለፍ ስለመሆኑ ገና በመግቢያው ክፍል ላይ ያስጠነቅቃል፦

        "በቅዳሴ ጊዜ የሚገኙ ምእመናን፥ መጽሐፍተ ቅዱሳትን ባይሰሙ፣ ቅዳሴ እስኪፈጸም ድረስ ባይታገሡና ከቁርባንም ባይቀበሉ ከቤተክርስቲያን ይሰደዱ፤ ሕገ እግዚአብሔርን አፍርሰዋልና"

                                                        መጽሐፈ ቅዳሴ

የቅዳሴ ብቻ ሳይሆን የንስሐም አድራሻ ቅዱስ ቁርባን ነው፡፡ "በአዲሱ አቁማዳ አዲሱ ወይን ሊሞላ ይገባል" የሚለውን የጌታ ትእዛዝ ይዛ፥ ቤተክርስቲያን ማንኛውም ግለሰብ ሥጋና ደሙን ከመቀበሉ በፊት ንስሐ እንዲገባ ታዝዛለች፡፡ በመሆኑ ቅዳሴ ያስቀደሰ ሰው መቁረብ እንዲገባው ሁሉ፥ ንስሐውን የጨረሰ አማኝም ቅዱስ ቁርባንን መቀበል ምርጫው አይደለም፡፡ የውዴታ ግዴታው ነው፡፡ ጸድቶ የተቀመጠ ብርጭቆ ለታጠበለት አገልግሎት ካልዋለ፥ ቆሽሾ ከተቀመጠው ብርጭቆ ከመታጠቡ ባሻገር አልተለየም፡፡ ንስሐ የገባም አንድ ሰው፥ ከእግዚአብሔር መንግሥተ ማዕድ ተካፍሎ የዘላለም ሕይወትን የቃልኪዳን ማኅተም በሰውነቱ እስካልያዘ ድረስ የንስሐውን አገልግሎት ከግብ አላደረሰም፡፡ (የዮሐንስ ወንጌል 6፥51)

BY በማለዳ ንቁ ቁጥር ! ፪


Share with your friend now:
tgoop.com/bemaledanek/2751

View MORE
Open in Telegram


Telegram News

Date: |

With Bitcoin down 30% in the past week, some crypto traders have taken to Telegram to “voice” their feelings. In handing down the sentence yesterday, deputy judge Peter Hui Shiu-keung of the district court said that even if Ng did not post the messages, he cannot shirk responsibility as the owner and administrator of such a big group for allowing these messages that incite illegal behaviors to exist. During a meeting with the president of the Supreme Electoral Court (TSE) on June 6, Telegram's Vice President Ilya Perekopsky announced the initiatives. According to the executive, Brazil is the first country in the world where Telegram is introducing the features, which could be expanded to other countries facing threats to democracy through the dissemination of false content. Some Telegram Channels content management tips Hashtags
from us


Telegram በማለዳ ንቁ ቁጥር ! ፪
FROM American