BEMALEDANEK Telegram 2753
አንድ አማኝ ቅዱስ ቁርባን ከተቀበለበት ጊዜ በኋላ ኃጢአት ቢያስተው ይቀሠፋል የሚባለው ሙሉ ለሙሉ ሐሰት ነው፡፡ እንዲህ ቢሆንማ፥ እኔን ጨምሮ ስንት ሰው እስካሁን ተቀሥፎ አልቆ ነበረ፡፡ "እንደ ቸርነትህ እንጂ እንደ በደላችን አይሁን" ከምንልበት የቅዳሴያችን የኅብረት ተማጽኖ በተቃራኒ የተሰለፈ፥ ዲያቢሎስ የሚያራግበው የወሬ ነፋስ ነው ይሄ፡፡

ሐዋሪያው ጴጥሮስ ሊቀ ካህኑ ኢየሱስ ራሱ ባርኮ ባቀበለው ሥጋና ደሙ ስለመቀደሱ ይታወቃል፡፡ ነገር ግን የመከራዋ ለሊት ስትደርስ፥ ማታቸው ስትመጣ፥ የጨለማ ሥልጣናቸውን አግኝተው ክርስቶስን ያሰሩ ጉልበተኞች "አንተም ከእርሱ ጋር ነህ" ቢሉት ከአንድም ሦስቴ "ኸረ አላውቀውም" ሲል ካደ፡፡ (የዮሐንስ ወንጌል 18፥25 ፤ የሉቃስ ወንጌል 22፥58) ሥጋውን በልቶ፥ ደሙን ጠጥቶ አላውቀውም? እንዴት ነው ነገሩ?

ከተቆረበ በኋላ ስሕተት ሊኖር እንደሚችልና ጴጥሮስና ሐዋሪያቱ እነሆ በታሪካቸው አስተማሩ፡፡ አስቀድመው ሲከተሉት፣ ድንቅ ሥራውን ሲያዩ፣ ቃሉን ሲሰሙ የቆዩት ሥጋና ደሙን ከተቀበሉ በኋላ እንደማያውቁት ሆነው ጥለውት ሸሹ፡፡ ወደነበሩበት ሊመለሱ አፈገፈጉ፡፡ ሕብረተሰባችን መካከል ዛሬ እንደሚመላለሰው ወሬ ቢሆን፥ ሐዋሪያቱ መቀሠፍ ነበረባቸው፡፡

ነገር ግን ጴጥሮስ ሥጋና ደሙን ወስዶ ስለፈጸመው ጥፋት ንስሐ ገባ እንጂ አልተቀሠፈም፡፡ (የሉቃስ ወንጌል 22፥62) እንደውም ሦስት ጊዜ ደጋግሞ ከድቶ የነበረውን ስምዖን፥ በደልን ፈጽሞ የሚረሳው ጌታ ከትንሣኤው በኋላ ሲያገኘው "ትወደኛለህን?" አለው፡፡ ከዚህ በፊት በአስቸጋሪው ወቅት "አላውቀውም" ሲል የነበረው አገልጋይ፥ እዚህ ከንስሐ በኋላ ቋንቋው ተቀይሮ ሦስቴ "እንድወድህስ አንተ ታውቃለህ" ይለው ጀመረ፡፡ (የዮሐንስ ወንጌል 21፥15-17) ፍቅሩንም ሕይወቱንም አሳልፎ ሰጠው፡፡ ወንጌል የሚያውቀው እውነት እንግዲህ ይሄ ነው፡፡

ዛሬ አንዳንድ የንስሐ አባቶች፣ አገልጋይ ነን የሚሉ ሰዎችና ማኅበረሰብ ወጣቱን ከማስተማር ይልቅ ያርቁታል፡፡ "ወዮውልሽ" አይነት ማስፈራሪያዎች ከዛም ከዚህም ይወረወራሉ፡፡ ጫት ሲበላ ተው ትቀሠፋለህ የሚል እምብዛም የለም፡፡ መጠጥ ሲጠጣ ተው ትጠፋለህ የሚል ትንሽ ነው፡፡ ሥጋና ደሙን ልውሰድ ሲል ግን ብዙዎች ያንጎራጉራሉ፡፡ ለምን? ለምን ከሥጋና ደሙን ወጣቶችን እናርቃለን?

ወጣቶች እወቁ! ቅዱስ ቁርባንን ለመውሰድ የተቀመጠ የዕድሜ ገደብ የለም፡፡ "ወጣት ከሆንክ ስለምታጠፋ አትቁረብ" የሚሉት፤ ስለ አምልኮት ሕይወትና የክፉ መናፍስት ጥልቅ ሥራ በተግባር ያልተገነዘቡ፥ በልምድ አካሄድ የሃይማኖትን ጎዳና የጀመሩ ሰዎች እንጂ ቤተክርስቲያን አይደለችም፡፡ ቤተክርስቲያን ቅዳሴ ቀድሳ ሥጋና ደሙን አዘጋጅታ ጠቦቶቿን ከእረኛቸው ሥጋ የማካፈል አደራዋን ዘወትር ትወጣለች እንጂ ዕድሜውን ቆጥራ "አንተ አትቁረብ" የምትለው አንድም ወጣት የለም፡፡

ሲሆንማ፥ ይልቁኑ ሥጋና ደም ለማን በጣም ያስፈልጋል ካላችሁኝ ለወጣቱና ለጎልማሳው ነው ያስፈልጋል የምለው፡፡ ምክንያቱም ስሜታዊነት የሚወጣበት፣ ጉልበት የሚጠነክርበት፣ ብዙ ሥራ የሚሠራበት፣ ትዳር የሚመሠረትበትና እንደ አገርም አምራች ዜጋ የሚኮንበት የዕድሜ ክልል ስለሆነ፥ በዚህ የጉብዝና ጊዜ ነው እግዚአብሔር አብሮ መገኘት ያለበት፡፡ ስሜታዊነትን ወደ መንፈሳዊ ኃይል እንዲቀይረው፣ ጉልበታችን በመናፍስት እንዳይደክም አሊያ ለክፋት እንዳይውል፣ ሥራችን እንዲባረክ፣ ትዳራችን እንዲሰምር፣ የአገር ፍቅር ከታሪክ ቁጭት ጋር ያለው የተቀደሰ ዜጋ እንዲኖር ሥጋና ደሙ መቅረብ የነበረበት ለወጣቶች ነበረ፡፡ አልሆነም! ተገላበጠና ወጣቶች ከቅዱስ ቁርባን ሲርቁ ይኸው ነገራችንም ከብዙ እውነቶች ተገላብጦ ቁጭ አለ፡፡

#ጸባዖት_ይከተላችሁ
@bemaledanek



tgoop.com/bemaledanek/2753
Create:
Last Update:

አንድ አማኝ ቅዱስ ቁርባን ከተቀበለበት ጊዜ በኋላ ኃጢአት ቢያስተው ይቀሠፋል የሚባለው ሙሉ ለሙሉ ሐሰት ነው፡፡ እንዲህ ቢሆንማ፥ እኔን ጨምሮ ስንት ሰው እስካሁን ተቀሥፎ አልቆ ነበረ፡፡ "እንደ ቸርነትህ እንጂ እንደ በደላችን አይሁን" ከምንልበት የቅዳሴያችን የኅብረት ተማጽኖ በተቃራኒ የተሰለፈ፥ ዲያቢሎስ የሚያራግበው የወሬ ነፋስ ነው ይሄ፡፡

ሐዋሪያው ጴጥሮስ ሊቀ ካህኑ ኢየሱስ ራሱ ባርኮ ባቀበለው ሥጋና ደሙ ስለመቀደሱ ይታወቃል፡፡ ነገር ግን የመከራዋ ለሊት ስትደርስ፥ ማታቸው ስትመጣ፥ የጨለማ ሥልጣናቸውን አግኝተው ክርስቶስን ያሰሩ ጉልበተኞች "አንተም ከእርሱ ጋር ነህ" ቢሉት ከአንድም ሦስቴ "ኸረ አላውቀውም" ሲል ካደ፡፡ (የዮሐንስ ወንጌል 18፥25 ፤ የሉቃስ ወንጌል 22፥58) ሥጋውን በልቶ፥ ደሙን ጠጥቶ አላውቀውም? እንዴት ነው ነገሩ?

ከተቆረበ በኋላ ስሕተት ሊኖር እንደሚችልና ጴጥሮስና ሐዋሪያቱ እነሆ በታሪካቸው አስተማሩ፡፡ አስቀድመው ሲከተሉት፣ ድንቅ ሥራውን ሲያዩ፣ ቃሉን ሲሰሙ የቆዩት ሥጋና ደሙን ከተቀበሉ በኋላ እንደማያውቁት ሆነው ጥለውት ሸሹ፡፡ ወደነበሩበት ሊመለሱ አፈገፈጉ፡፡ ሕብረተሰባችን መካከል ዛሬ እንደሚመላለሰው ወሬ ቢሆን፥ ሐዋሪያቱ መቀሠፍ ነበረባቸው፡፡

ነገር ግን ጴጥሮስ ሥጋና ደሙን ወስዶ ስለፈጸመው ጥፋት ንስሐ ገባ እንጂ አልተቀሠፈም፡፡ (የሉቃስ ወንጌል 22፥62) እንደውም ሦስት ጊዜ ደጋግሞ ከድቶ የነበረውን ስምዖን፥ በደልን ፈጽሞ የሚረሳው ጌታ ከትንሣኤው በኋላ ሲያገኘው "ትወደኛለህን?" አለው፡፡ ከዚህ በፊት በአስቸጋሪው ወቅት "አላውቀውም" ሲል የነበረው አገልጋይ፥ እዚህ ከንስሐ በኋላ ቋንቋው ተቀይሮ ሦስቴ "እንድወድህስ አንተ ታውቃለህ" ይለው ጀመረ፡፡ (የዮሐንስ ወንጌል 21፥15-17) ፍቅሩንም ሕይወቱንም አሳልፎ ሰጠው፡፡ ወንጌል የሚያውቀው እውነት እንግዲህ ይሄ ነው፡፡

ዛሬ አንዳንድ የንስሐ አባቶች፣ አገልጋይ ነን የሚሉ ሰዎችና ማኅበረሰብ ወጣቱን ከማስተማር ይልቅ ያርቁታል፡፡ "ወዮውልሽ" አይነት ማስፈራሪያዎች ከዛም ከዚህም ይወረወራሉ፡፡ ጫት ሲበላ ተው ትቀሠፋለህ የሚል እምብዛም የለም፡፡ መጠጥ ሲጠጣ ተው ትጠፋለህ የሚል ትንሽ ነው፡፡ ሥጋና ደሙን ልውሰድ ሲል ግን ብዙዎች ያንጎራጉራሉ፡፡ ለምን? ለምን ከሥጋና ደሙን ወጣቶችን እናርቃለን?

ወጣቶች እወቁ! ቅዱስ ቁርባንን ለመውሰድ የተቀመጠ የዕድሜ ገደብ የለም፡፡ "ወጣት ከሆንክ ስለምታጠፋ አትቁረብ" የሚሉት፤ ስለ አምልኮት ሕይወትና የክፉ መናፍስት ጥልቅ ሥራ በተግባር ያልተገነዘቡ፥ በልምድ አካሄድ የሃይማኖትን ጎዳና የጀመሩ ሰዎች እንጂ ቤተክርስቲያን አይደለችም፡፡ ቤተክርስቲያን ቅዳሴ ቀድሳ ሥጋና ደሙን አዘጋጅታ ጠቦቶቿን ከእረኛቸው ሥጋ የማካፈል አደራዋን ዘወትር ትወጣለች እንጂ ዕድሜውን ቆጥራ "አንተ አትቁረብ" የምትለው አንድም ወጣት የለም፡፡

ሲሆንማ፥ ይልቁኑ ሥጋና ደም ለማን በጣም ያስፈልጋል ካላችሁኝ ለወጣቱና ለጎልማሳው ነው ያስፈልጋል የምለው፡፡ ምክንያቱም ስሜታዊነት የሚወጣበት፣ ጉልበት የሚጠነክርበት፣ ብዙ ሥራ የሚሠራበት፣ ትዳር የሚመሠረትበትና እንደ አገርም አምራች ዜጋ የሚኮንበት የዕድሜ ክልል ስለሆነ፥ በዚህ የጉብዝና ጊዜ ነው እግዚአብሔር አብሮ መገኘት ያለበት፡፡ ስሜታዊነትን ወደ መንፈሳዊ ኃይል እንዲቀይረው፣ ጉልበታችን በመናፍስት እንዳይደክም አሊያ ለክፋት እንዳይውል፣ ሥራችን እንዲባረክ፣ ትዳራችን እንዲሰምር፣ የአገር ፍቅር ከታሪክ ቁጭት ጋር ያለው የተቀደሰ ዜጋ እንዲኖር ሥጋና ደሙ መቅረብ የነበረበት ለወጣቶች ነበረ፡፡ አልሆነም! ተገላበጠና ወጣቶች ከቅዱስ ቁርባን ሲርቁ ይኸው ነገራችንም ከብዙ እውነቶች ተገላብጦ ቁጭ አለ፡፡

#ጸባዖት_ይከተላችሁ
@bemaledanek

BY በማለዳ ንቁ ቁጥር ! ፪


Share with your friend now:
tgoop.com/bemaledanek/2753

View MORE
Open in Telegram


Telegram News

Date: |

Content is editable within two days of publishing How to Create a Private or Public Channel on Telegram? best-secure-messaging-apps-shutterstock-1892950018.jpg How to create a business channel on Telegram? (Tutorial) Over 33,000 people sent out over 1,000 doxxing messages in the group. Although the administrators tried to delete all of the messages, the posting speed was far too much for them to keep up.
from us


Telegram በማለዳ ንቁ ቁጥር ! ፪
FROM American