BETHEL_TUBE Telegram 3493
‹‹በጒብዝናህ ወራት ፈጣሪህን አስብ›› (መክብብ ፲፪፥፩)

ያለማቋረጥ ሲሔዱም ሲቀመጡም፣ሲበሉም ሲጠጡም፣ ሲሠሩም ሲያርፉም ማሰብ ግን ሕይወትም፣ ጤናም፣ የደስታም ምንጭ ነው፡፡
እግዚአብሔርን ማሰብ – መልካም ነገርን መናገር
ማሰብ ከመናገር ጋር የአንድ ሳንቲም ገጽታ ነው፤ ሰው የሚናገረው ያሰበውን ነውና፡፡  ማሰብና መናገር ያላቸውን አንድነት ልበ አምላክ ነቢዩ ዳዊት ከተናገረው ኃይለ ቃል መረዳት ይቻላል፡፡  ‹‹አቤቱ በድንኳንህ ውስጥ ማን ያድራል? በተቀደሰውም ተራራህ ማን ይኖራል? በቅንነት የሚሄድ ጽድቅንም የሚያደርግ፣ በልቡም እውነትን የሚናገር›› በማለት የተናገረውን ቃል እናስተውል፡፡ ሰው በልቡናው ያስባል እንጂ አይናገርም፤ ሆኖም ግን በአንደበት የሚነገረው በልቡና የታሰበ ነውና በልቡም እውነትን የሚናገር ብሎ ተናገረ፡፡ (መዝ. ፲፬፥፩-፪)
በጉብዝናችን ወራት ፈጣሪያችንን እንድናስብ የሚረዳን አንደበታችን ከክፉ ከልክለን ሽንገላንም ከእኛ አርቀን ሰዎችን የሚያጽናና የሚያረጋጋ መልካም ነገርንም ብቻ ስንናገር ነው፡፡  እግዚአብሔርን የማሰብ አንዱ መገለጫ መልካም ነገር መናገር ነው፡፡  መጽሐፍ ‹‹እግዚአብሔር መልካም ነው›› ብሎ እንደተናገረ ስለ እግዚአብሔር ቸርነት፣ ታላቅነትና መጋቢነት የሚናገር መልካም ነገር ተናገረ፡፡ (ናሆ. ፩፥፯)
እግዚአብሔር ስለሚወደውና ስለሚፈቅደው ነገር ብቻ መናገር እግዚአብሔርን ማሰብ ነው፡፡  ዛሬ ላይ ብዙዎቻችን እግዚአብሔርን ማሰብ ስላቆምን ከአንደበታችን የሚወጣው ቃል ሁሉ ስድብ፣  ትችት፣  ነቀፋ፣ ሐሜት፣ ሽንገላ፣ ተረብና የመሳሰሉት ሆነዋል፡፡  ነቢዩ ዳዊት ‹‹ጉሮሮአቸው የተከፈተ መቃብር ነው፤ በምላሳቸው ሸነገሉ፤ ከከንፈራቸው በታች የእባብ መርዝ አለ፤  አፋቸው መርገምንና መራራን ተሞልቶዋል  …. እግዚአብሔርን መፍራት በዓይናቸው የለም›› ብሎ እንደተናገረው የእኛም ነገር እንዲሁ ሆኗል፡፡ (መዝ. ፲፫፥፬-፮)
እግዚአብሔርን የሚያስብ ወጣት የሚናገረውን ያውቃል፡፡ አንደበቱም የተገራና በመልካም ነገር የተቀመመ ነው፡፡ ሰውን የሚያስደነግጥ፣ የከፋውን የሚያባብስ፣  በወገኖች መካከል ልዩነትን የሚያሰፋና ጠብ የሚጭር ነገር ከአንደበቱ አይወጣም፡፡ እየጮኸ፣ ጎረቤት እያወከ፣ ሰዎችን እያሳቀቀ፣ የሰዎችን ክብር እየነካ፣ በሌላው የአካል መጉደል እያሾፈ አይናገርም፡፡ ‹‹በአፍ ይጠፉ በለፈለፉ›› እንደሚባለውም በአንደበቱ ምክንያት የማይገባውን እየተናገረ በራሱና በማኅበረሰቡም ሆነ በሀገሩ ላይ ጥፋትና መጠፋፋትን አያመጣም፡፡ የምንናገረውን ለማወቅ ፈጣሪያችን ልዑል እግዚአብሔርን እናስብ፡፡  እግዚአብሔርን ማሰብ ስላቆምን ስለተውነውም ሰዎች በድለውንም ይሁን ሳይበድሉን የስድብ ናዳ እናወርድባቸዋለን፡፡  በአንድ ሰው ስሕተት አባቱ፣ እናቱ፣ ወንድሞቹ በመጣበት ነገድ፣ የተወለደበት መንደር ሳይቀረን በስድብ እናጥረገርጋቸዋለን፡፡  እግዚአብሔርን ማሰብ ስላቆምን የምንናገረው እያንዳንዱ ነገር ሰዎች ላይ ምን ዓይነት አሉታዊ ተጽዕኖ እንደሚያሳድር በሀገርም ላይ ምን ዓይነት ጥፋት ይዞ እንደሚመጣ ማስተዋል ተስኖናል፡፡  ጥቂት የማንባል ወጣቶች እግዚአብሔርን ማሰብ እንደሞት ስለምንቆጥረው የሞት ምክንያት የሆኑ አያሌ ነገሮች ከአጠገባችን ቆመዋል፡፡  ሽማግሎዎችን እንሳደባለን፤ አካል በጎደላቸው እንሳለቃለን፤ ችሎታ የጎደለውን እናሸማቅቃለን፤  ከደረስንበት ያልደረሰውን እናቃልላለን፡፡
እግዚአብሔርን  ማሰብ- ከመከራ ሁሉ መዳኛ መንገድ ነው፡፡
ጠቢቡ ሰሎሞን ‹‹በጉብዝናህ ወራት ፈጣሪህን አስብ›› ብሎ የተናገረበትን ምክንያት ሲገልጥ የመጀመሪያ ምክንያት አድርጎ ያቀረበው ‹‹የጭንቀት ቀን ሳይመጣ›› የሚል ነው፡፡ በወጣትነት በልዩ ልዩ ምክንያቶች የሚገጥሙንን የጭንቀት ፈተናዎች የምንወጣው በተለያዩ አደንዛዥ ዕፅ ሱሶች ውስጥ በመደበቅ፣ አልኮል መጠጦችን በማብዛት፣ መፍትሔ ብለን የምንወስዳቸው ሌሎች ችግር አምጪ አማራጮች ውስጥ በመግባትና ሌሎች መሰል ድርጊቶችን በመከወን መሆን የለበትም፡፡ የጭንቀት መድኃኒቱ እግዚአብሔርን ማሰብና እንደ ፈቃዱም መመላለስ ነው፡፡ የወጣትነት ዕድሜ ካለፈ በኋላም ለሚገጥመን የሽምግልና ጭንቀት መድኃኒቱ የወጣትነት ዕድሜን አካሄድ ማስተካከል እንደሆነ የሥነ ልቡና ባለሙያዎችም ሳይቀሩ ይመክራሉ፡፡ ነቢዩ ዳዊት ‹‹ጎልማሳ መንገዱን በምን ያነጻል? ቃልህን በመጠበቅ ነው›› ብሎ እንዳስተማረውም በኋለኛው ዘመን የሚኖረንን መዳረሻ የሠመረና ትርጉም ያለው የሚያደርገው በወጣትነት ዘመናችን ከእግዚአብሔር ጋር እንዲኖረን የምናደርገው መልካም አኗኗር ነው፡፡ በወጣትነት ያልዘሩትን በሽምግልና አያጭዱትም፡፡ በጉብዝና ያላረሙትን በዕርግና አያስተካክሉትም፡፡ (መዝ. ፻፲፰፥፱)
ጠቢቡ ሰሎሞን በጉብዝና ወራት ፈጣሪን የማሰብ ምክንያት አድርጎ ያቀረበው ሌላኛው ምክንያት ‹‹ደስ አያሰኙኝም የምትላቸው ዓመታት ሳይደርሱ፤ ፀሐይና ብርሃን ጨረቃና ከዋክብትም ሳይጨልሙ፥ ደመናትም ከዝናብ በኋላ ሳይመለሱ፤……….አፈርም ወደነበረበት ምድር ሳይመለስ÷ ነፍስም ወደሰጠው ወደ እግዚአብሔር ሳይመለስ ፈጣሪህን አስብ›› የሚል ነው፡፡ በፀሐይ በጨረቃና በከዋክብት የተመሰለ ማግኘት፣ ማሸነፍ፣ ነግዶ ማትረፍ፣ ሮጦ ማምለጥ፣ ወድቆ መነሣት የሚቻልበት የወጣትነት ጊዜ በእርጅና በድካም በደዌና ከፍ ሲልም በሞት ይደመደማል፡፡ በብርሃን ጀምረን በብርሃን፤ በድል ጀምረን በድል እንድንፈጽም ታናሽ የሆነ ጅማሬያችን እጅግ የበዛ እንዲሆን በጉብዝናችን ወራት ፈጣሪያችን ልዑል እግዚአብሔርን በመንገዳችንና በተግባራችን ሁሉ እናስብ፤ ከእርሱ ጋር እንኑር፤ ስለ እርሱም እንናገር!
ወስብሐት ለእግዚአብሔር


ዛሬ ላይ ነገን ለማነጽ የቅድስት ቤተ ክርስቲያንን ድምጽ ልንገነባ ነው። #ሚዲያችንን_ይደግፉ

▭▭▭▭▭▭▭▭ ©ቤትኤል ዘተዋህዶ ሚዲያ (BZM) ▭▭▭▭▭▭▭▭



tgoop.com/bethel_tube/3493
Create:
Last Update:

‹‹በጒብዝናህ ወራት ፈጣሪህን አስብ›› (መክብብ ፲፪፥፩)

ያለማቋረጥ ሲሔዱም ሲቀመጡም፣ሲበሉም ሲጠጡም፣ ሲሠሩም ሲያርፉም ማሰብ ግን ሕይወትም፣ ጤናም፣ የደስታም ምንጭ ነው፡፡
እግዚአብሔርን ማሰብ – መልካም ነገርን መናገር
ማሰብ ከመናገር ጋር የአንድ ሳንቲም ገጽታ ነው፤ ሰው የሚናገረው ያሰበውን ነውና፡፡  ማሰብና መናገር ያላቸውን አንድነት ልበ አምላክ ነቢዩ ዳዊት ከተናገረው ኃይለ ቃል መረዳት ይቻላል፡፡  ‹‹አቤቱ በድንኳንህ ውስጥ ማን ያድራል? በተቀደሰውም ተራራህ ማን ይኖራል? በቅንነት የሚሄድ ጽድቅንም የሚያደርግ፣ በልቡም እውነትን የሚናገር›› በማለት የተናገረውን ቃል እናስተውል፡፡ ሰው በልቡናው ያስባል እንጂ አይናገርም፤ ሆኖም ግን በአንደበት የሚነገረው በልቡና የታሰበ ነውና በልቡም እውነትን የሚናገር ብሎ ተናገረ፡፡ (መዝ. ፲፬፥፩-፪)
በጉብዝናችን ወራት ፈጣሪያችንን እንድናስብ የሚረዳን አንደበታችን ከክፉ ከልክለን ሽንገላንም ከእኛ አርቀን ሰዎችን የሚያጽናና የሚያረጋጋ መልካም ነገርንም ብቻ ስንናገር ነው፡፡  እግዚአብሔርን የማሰብ አንዱ መገለጫ መልካም ነገር መናገር ነው፡፡  መጽሐፍ ‹‹እግዚአብሔር መልካም ነው›› ብሎ እንደተናገረ ስለ እግዚአብሔር ቸርነት፣ ታላቅነትና መጋቢነት የሚናገር መልካም ነገር ተናገረ፡፡ (ናሆ. ፩፥፯)
እግዚአብሔር ስለሚወደውና ስለሚፈቅደው ነገር ብቻ መናገር እግዚአብሔርን ማሰብ ነው፡፡  ዛሬ ላይ ብዙዎቻችን እግዚአብሔርን ማሰብ ስላቆምን ከአንደበታችን የሚወጣው ቃል ሁሉ ስድብ፣  ትችት፣  ነቀፋ፣ ሐሜት፣ ሽንገላ፣ ተረብና የመሳሰሉት ሆነዋል፡፡  ነቢዩ ዳዊት ‹‹ጉሮሮአቸው የተከፈተ መቃብር ነው፤ በምላሳቸው ሸነገሉ፤ ከከንፈራቸው በታች የእባብ መርዝ አለ፤  አፋቸው መርገምንና መራራን ተሞልቶዋል  …. እግዚአብሔርን መፍራት በዓይናቸው የለም›› ብሎ እንደተናገረው የእኛም ነገር እንዲሁ ሆኗል፡፡ (መዝ. ፲፫፥፬-፮)
እግዚአብሔርን የሚያስብ ወጣት የሚናገረውን ያውቃል፡፡ አንደበቱም የተገራና በመልካም ነገር የተቀመመ ነው፡፡ ሰውን የሚያስደነግጥ፣ የከፋውን የሚያባብስ፣  በወገኖች መካከል ልዩነትን የሚያሰፋና ጠብ የሚጭር ነገር ከአንደበቱ አይወጣም፡፡ እየጮኸ፣ ጎረቤት እያወከ፣ ሰዎችን እያሳቀቀ፣ የሰዎችን ክብር እየነካ፣ በሌላው የአካል መጉደል እያሾፈ አይናገርም፡፡ ‹‹በአፍ ይጠፉ በለፈለፉ›› እንደሚባለውም በአንደበቱ ምክንያት የማይገባውን እየተናገረ በራሱና በማኅበረሰቡም ሆነ በሀገሩ ላይ ጥፋትና መጠፋፋትን አያመጣም፡፡ የምንናገረውን ለማወቅ ፈጣሪያችን ልዑል እግዚአብሔርን እናስብ፡፡  እግዚአብሔርን ማሰብ ስላቆምን ስለተውነውም ሰዎች በድለውንም ይሁን ሳይበድሉን የስድብ ናዳ እናወርድባቸዋለን፡፡  በአንድ ሰው ስሕተት አባቱ፣ እናቱ፣ ወንድሞቹ በመጣበት ነገድ፣ የተወለደበት መንደር ሳይቀረን በስድብ እናጥረገርጋቸዋለን፡፡  እግዚአብሔርን ማሰብ ስላቆምን የምንናገረው እያንዳንዱ ነገር ሰዎች ላይ ምን ዓይነት አሉታዊ ተጽዕኖ እንደሚያሳድር በሀገርም ላይ ምን ዓይነት ጥፋት ይዞ እንደሚመጣ ማስተዋል ተስኖናል፡፡  ጥቂት የማንባል ወጣቶች እግዚአብሔርን ማሰብ እንደሞት ስለምንቆጥረው የሞት ምክንያት የሆኑ አያሌ ነገሮች ከአጠገባችን ቆመዋል፡፡  ሽማግሎዎችን እንሳደባለን፤ አካል በጎደላቸው እንሳለቃለን፤ ችሎታ የጎደለውን እናሸማቅቃለን፤  ከደረስንበት ያልደረሰውን እናቃልላለን፡፡
እግዚአብሔርን  ማሰብ- ከመከራ ሁሉ መዳኛ መንገድ ነው፡፡
ጠቢቡ ሰሎሞን ‹‹በጉብዝናህ ወራት ፈጣሪህን አስብ›› ብሎ የተናገረበትን ምክንያት ሲገልጥ የመጀመሪያ ምክንያት አድርጎ ያቀረበው ‹‹የጭንቀት ቀን ሳይመጣ›› የሚል ነው፡፡ በወጣትነት በልዩ ልዩ ምክንያቶች የሚገጥሙንን የጭንቀት ፈተናዎች የምንወጣው በተለያዩ አደንዛዥ ዕፅ ሱሶች ውስጥ በመደበቅ፣ አልኮል መጠጦችን በማብዛት፣ መፍትሔ ብለን የምንወስዳቸው ሌሎች ችግር አምጪ አማራጮች ውስጥ በመግባትና ሌሎች መሰል ድርጊቶችን በመከወን መሆን የለበትም፡፡ የጭንቀት መድኃኒቱ እግዚአብሔርን ማሰብና እንደ ፈቃዱም መመላለስ ነው፡፡ የወጣትነት ዕድሜ ካለፈ በኋላም ለሚገጥመን የሽምግልና ጭንቀት መድኃኒቱ የወጣትነት ዕድሜን አካሄድ ማስተካከል እንደሆነ የሥነ ልቡና ባለሙያዎችም ሳይቀሩ ይመክራሉ፡፡ ነቢዩ ዳዊት ‹‹ጎልማሳ መንገዱን በምን ያነጻል? ቃልህን በመጠበቅ ነው›› ብሎ እንዳስተማረውም በኋለኛው ዘመን የሚኖረንን መዳረሻ የሠመረና ትርጉም ያለው የሚያደርገው በወጣትነት ዘመናችን ከእግዚአብሔር ጋር እንዲኖረን የምናደርገው መልካም አኗኗር ነው፡፡ በወጣትነት ያልዘሩትን በሽምግልና አያጭዱትም፡፡ በጉብዝና ያላረሙትን በዕርግና አያስተካክሉትም፡፡ (መዝ. ፻፲፰፥፱)
ጠቢቡ ሰሎሞን በጉብዝና ወራት ፈጣሪን የማሰብ ምክንያት አድርጎ ያቀረበው ሌላኛው ምክንያት ‹‹ደስ አያሰኙኝም የምትላቸው ዓመታት ሳይደርሱ፤ ፀሐይና ብርሃን ጨረቃና ከዋክብትም ሳይጨልሙ፥ ደመናትም ከዝናብ በኋላ ሳይመለሱ፤……….አፈርም ወደነበረበት ምድር ሳይመለስ÷ ነፍስም ወደሰጠው ወደ እግዚአብሔር ሳይመለስ ፈጣሪህን አስብ›› የሚል ነው፡፡ በፀሐይ በጨረቃና በከዋክብት የተመሰለ ማግኘት፣ ማሸነፍ፣ ነግዶ ማትረፍ፣ ሮጦ ማምለጥ፣ ወድቆ መነሣት የሚቻልበት የወጣትነት ጊዜ በእርጅና በድካም በደዌና ከፍ ሲልም በሞት ይደመደማል፡፡ በብርሃን ጀምረን በብርሃን፤ በድል ጀምረን በድል እንድንፈጽም ታናሽ የሆነ ጅማሬያችን እጅግ የበዛ እንዲሆን በጉብዝናችን ወራት ፈጣሪያችን ልዑል እግዚአብሔርን በመንገዳችንና በተግባራችን ሁሉ እናስብ፤ ከእርሱ ጋር እንኑር፤ ስለ እርሱም እንናገር!
ወስብሐት ለእግዚአብሔር


ዛሬ ላይ ነገን ለማነጽ የቅድስት ቤተ ክርስቲያንን ድምጽ ልንገነባ ነው። #ሚዲያችንን_ይደግፉ

▭▭▭▭▭▭▭▭ ©ቤትኤል ዘተዋህዶ ሚዲያ (BZM) ▭▭▭▭▭▭▭▭

BY ቤትኤል ዘ-ተዋሕዶ


Share with your friend now:
tgoop.com/bethel_tube/3493

View MORE
Open in Telegram


Telegram News

Date: |

For crypto enthusiasts, there was the “gm” app, a self-described “meme app” which only allowed users to greet each other with “gm,” or “good morning,” a common acronym thrown around on Crypto Twitter and Discord. But the gm app was shut down back in September after a hacker reportedly gained access to user data. The Channel name and bio must be no more than 255 characters long End-to-end encryption is an important feature in messaging, as it's the first step in protecting users from surveillance. Other crimes that the SUCK Channel incited under Ng’s watch included using corrosive chemicals to make explosives and causing grievous bodily harm with intent. The court also found Ng responsible for calling on people to assist protesters who clashed violently with police at several universities in November 2019. Just as the Bitcoin turmoil continues, crypto traders have taken to Telegram to voice their feelings. Crypto investors can reduce their anxiety about losses by joining the “Bear Market Screaming Therapy Group” on Telegram.
from us


Telegram ቤትኤል ዘ-ተዋሕዶ
FROM American