tgoop.com/bilQURANnehyaa/4249
Create:
Last Update:
Last Update:
የሰው ልጅ ሥራ ባገኝ ደስታን አገኛለሁ ብሎ ያስባል፣ ሲያገኝ ዱንያ ያው ናት፡፡
ቀጥሎም አግብቼ ከዚህ የብቸኝነት ሕይወት ብወጣ እኮ ደስታን እጎናፀፋለሁ ብሎ ያስባል፤ ሲያገባ ዱንያ አሁንም ያው ናት፡፡
ቀጥሎም ልጅ ባገኝ ይላል፤ ያገኛል፡፡ ዱንያ ያው ናት፡፡
በትምህርት፣ በገንዘብ ከፍ ቢልም ዱንያ አትሞላም፡፡ እሷ ያው ናት።
የሰው ልጅ እንዲሁ እንዳለ እና እንደተመኘ ወደፊት አገኛታለሁ ብሎ ለደስታ እንደቀጠረ በመጨረሻም ቀብር ይገባል፡፡
ወዳጄ! ደስታህ ነገ ሳይሆን ዛሬ ነው፤ ፈገግታህን ለነገ አትቅጠር፡፡ ለመሳቅ በይደር አታቆይ፡፡ ዛሬ ባለው ትንሽ ነገር ያልተደሠተ ነገ ብዙ ቢያገኝም አይደሠትም፡፡
ደስታ በሀብት መብዛት ውስጥ ሳይሆን በመብቃቃት ውስጥ ነው የሚገኘው፡፡
አላህን ጤና፣ እርጋታን፣ ሰላምን፣ እርካታን ለምኑት፡፡
ወዳጄዋ!
ካልገቱት ምኞት አያረጅም፣
ካልገደቡት ፍላጎት አይቆምም።
ዱንያ እንደየባህርውሃ ጨዋማ ናት፤ ከሷ በጠጡ ቁጥር ጥሟ ይበረታል፡፡
ግና የታቀበን አላህ ያቅበዋል፡፡
አላህ መብቃቃትን ይለግሰን።
ቲስበሑ ዐላ ኸይር
https://www.tgoop.com/MuhammedSeidAbx
BY 🍃بالقرآن نحي {በቁርአን እንኖራለን
Share with your friend now:
tgoop.com/bilQURANnehyaa/4249