BOOKFOR Telegram 1361
በዜማ ማንሰፍሰፍ፤ አበበ ብርሃኔ
(ዮናስ ታምሩ ገብሬ)
‹‹ሰደድ ነው አንገቷ፤
እንደ ዥንጉርጉሩ፣ እንደ መቀነቷ፤ [አበበ ብርሃኔ]

የኢትዮጵያ ሙዚቃ ወንዴው ባሕርይ የተጫነው እንዲሆን ዕሙን ነው፤ በሀገራችን የተቀነቀኑ የበርካታ ዘፈኖች ግጥም እና ዜማቸው ወንዳዊ ጠባይ በጉልህ የሚንጸባረቅባቸው ናቸው። ለአብነት እንኳን ከተባእት ጾታ ድግምግሞሻዊ መገለጫዎች መካከል፡- መደለቅ፣ መርገጥ፣ መጋለብ፣ ማካለብ እና ሌሎችም ተጠቃሾች ናቸው፤ የተጠቀሱ ባሕርያት በሙዚቃችን ገላ ውስጥ ጥላ ጥለው ከርመዋል። አሁን፣ አሁን በመጠኑም ቢሆን ሙዚቃችን ሴቴአዊነትን እየተላበሰ መጥቷል - ከ1980-81 ዓ.ም. ወዲህ፤ ከመደለቅ፣ ከመርገጥ እና ከመጋለብ አልፎ ወደ ሴቴአዊ መንሰፍሰፍ እያደላ መጣ ሙዚቃችን - በአበበ መለሠ። ስፓኛዊው ሰዓሊ ፐብሎ ፒካሶ ጥበብ ከውስጥ ስትመነጭ ጣዕመኛ ነች የሚላት ይትባሃል አለቺው፤ አቤም እንዲያ ነው - በሥራዎቹ የውስጣችንን ድብቅ ሚስጥር ጫር አድርጎ ያልፋል፤ በእንስፍስፍ ስልት የተብሰለሰለ ውስጣችንን ጎብኝቶ ለሌላ ተመስጦ አምነሽንሾን ሸርተት ይላል፤ ማሳተፍ ጠባዩ ሆነ ማለት ነው።

የሴት ሥነ-ልቡና የዘለቀው ሙዚቀኛ ነው አቤ፤ ወንድ ሆኖ ሳለ በሴት ይትባሃል የማንሰፍሰፍ ክኅሎት ያደለው ደራሲ። የሚደርሳቸው የዘፈን ዜማዎች ብርክ የማድረግና የማራድ ጉልበት አላቸው። ኩልል ያለ የቆለኛ ድምጽ ዓይነት ዜማዎች እና ስርቅርቅ ስልቶች በድርሰቶቹ ገላ ውስጥ ይስተዋላሉ። ከስምንት መቶ (800) በላይ የዜማ ድርሰቶችን ጀባ ብሏል። አመለ ሸጋ እና ተጫዋች ነው፤ ከዘፈን ዜማ አልፎ ክራር እና ኪቦርድ በወጉ ይጫወታል። 1978 ዓ.ም. መገባደጃ አካባቢ ከጎንደር ወደ አዲስ አበባ ተከተተ - ከፋሲለደስ የኪነት ቡድን ጋር ለወጣቶች ፌስቲቫል ወደ ኮሪያ ሊዘምት። አልሆነም ነበር ታዲያ፤ በአዲስ አበባ ቲያትር ቤቶች ሲያንዣብብ እያዩ ማንያዘዋል (የ‹‹ዕድሌ ጠማማ›› ዘፈን አቀንቃኝ) ጋር ይገናኛሉ። የ‹‹ልቤ ገራገሩ››ን ዘፈን ግጥም በአንድ ምሽት ደርሶ ጀባ ካለው በኋላ ወደ ጎንደር ይተማል - ብዙም ሳይቆይ ወደ አዲስ አበባ ተመለሰ…

…ከግጥም እና ዜማ ደራሲው ከጸጋዬ ደቦጭ ጋር ለጸጋዬ እሸት፣ ለኬኔዲ መንገሻ እና ለአሠፉ ደባልቄ በሠራቸው ሥራዎች ተወዳጅነትን አተረፈ። አቤ በግጥምና ዜማ ድርሰቶቹ ማንሰፍሰፍ ያውቅበታል፤ ወንድ ደራሲ የሴት ዓይነት ማራድን በሙዚቃ ሥራዎቹ…

…የእናት ዓይነት የአንጀት መንሰፍሰፍ እና ተብሰልስሎት በዋናነት በዜማ ድርሰቶቹ ውስጥ ይንጸባረቃሉ፤ አዚሞ ማንሰፍሰፍን ተክኖበታል። እውስጥ የሚቀሩ ዜማዎችን ለበርካታ ድምጻዊያን አበርክቷል፤ ለማሳያ ያህል፡-

1. ለጌታቸው ካሳ፡- ‹‹ቀና ብዬ ሳየው›› (ዜማ) (ግጥም ጸጋዬ ደቦጭ)
2. ለኤፍሬም ታምሩ፡- ‹‹ቢልልኝ›› (ዜማ)
3. ለሂሩት በቀለ፡- ‹‹የእኔ ዓለም››፣ ‹‹ጠላኝ እንዳልለው›› (ዜማ)
4. ለባለቤቱ/ፍቅርአዲስ፡- ‹‹እርሳኝ›› (ዜማ)፣ ‹‹አልገባኝም›› (ግጥምና ዜማ)፣ ‹‹ዝም እላለሁ›› (ዜማ) - ካሴት 1984 ዓ.ም.፣ ‹‹ላባብለው›› 1989፣ ‹‹ሳብ በለው›› 1993 ካሴቶች
5. ለአሠፉ ደባልቄ፡- ‹‹የሆዴን›› (ግጥምና ዜማ)
6. ለሰርጉዓለም ተገኝ፡- ‹‹ሳላያት አመሸሁ›› (ዜማ)
7. ለየሺእመቤት ዱባለ፡- ‹‹ለዚህ በቃሁ››፣ ‹‹ትዝ አለኝ›› (ዜማ)
8. ለጸጋዬ እሸቱ፡- ‹‹ሆዴ ክፉ ዕዳዬ›› (ዜማ)፣ ‹‹መሸ›› (ግጥምና ዜማ)፣ ‹‹ያየ አለ›› (ዜማ)፣ ‹‹ተከለከለ አሉ›› (ዜማ)
9. ለማሐሙድ አሕመድ፡- ‹‹ስንቱን አሳለፍኩት›› (ዜማ)
10. ለኬኔዲ መንጋሻ፡- ‹‹ፋንታዬ›› ካሴት - ‹‹ፋንታዬ›› ‹‹አንቺ ዓለም›› ‹‹እንግባ ሀገራችን/ከየሺእመቤት ጋር›› (ግጥምና ዜማ)
11. ለቴዎድሮስ ታደሠ እና አሠፉ ደባልቄ፡- ‹‹ላጉርስሽ›› (ዜማ)
12. ለአበበ ተካ፡- ‹‹ወፍዬ››፣ ‹‹ሰው ጥሩ/ማን አላት ሰው ሐገር›› - ካሴት ሙሉውን ዜማ (ግጥሙ የአያ ሙሌ - ሙሉጌታ ተስፋዬ ነው)
13. ለሐመልማል አባተ፡- ‹‹ይዳኘኝ ያየ›› (ዜማ)
14. ለጎሳዬ ተስፋዬ፡- ‹‹የሐመሯ›› (ዜማ)
15. ለሞኒካ ሲሳይ፡- ‹‹ቀኑ አጠረ›› (ዜማ)
16. ለይርዳው ጤናው፡- ‹‹ላፍ አርጋት›› ሙሉ ካሴት (ሶስና ታደሠ ደግሞ ሙሉ ግጥም)
17. ለጸደኒያ ገ/ማርቆስ ሙሉ ካሴት፡- ከ‹‹ላፍ አርጋት›› ካሴት ዕኩል (ሶስና ታደሠ ደግሞ ሙሉ ግጥም)
18. ለይሁኔ በላይ፡- ‹‹የሰው ሐገር›› (ግጥምና ዜማ)
19. አሁንም ለባለቤቱ፡- ‹‹ምስክር›› - ካሴት፤ ይልማ ገ/አብ እና ቢኒአሚር አሕመድ ታክለውበታል
20. ለዳዊት ጽጌ፡- ‹‹እትቱ›› (ዜማ) - ግጥም፡- ናትናኤል ግርማቸው
21. ለተመስገን ተስፋዬ፡- ‹‹ሳቢዬ›› (ዜማ) - ግጥም፡- ናትናኤል ግርማቸው

እና ሌሎች ተጠቃሾች ናቸው። ለዛሬ የሰርጉዓለም ተገኝን

‹‹ሳላያት አመሸሁ፣ ሳላያት፤
እመጣለሁ እያልኩ - እየዋሸሁ፤
ነገር አበላሸሁ - እያመሸሁ፤›› ተጋበዙልኝ።

አቤ ዕድሜና ጤና ይስጥህ፤ አመሰግናለሁ!
@Bookfor
@Bookfor



tgoop.com/bookfor/1361
Create:
Last Update:

በዜማ ማንሰፍሰፍ፤ አበበ ብርሃኔ
(ዮናስ ታምሩ ገብሬ)
‹‹ሰደድ ነው አንገቷ፤
እንደ ዥንጉርጉሩ፣ እንደ መቀነቷ፤ [አበበ ብርሃኔ]

የኢትዮጵያ ሙዚቃ ወንዴው ባሕርይ የተጫነው እንዲሆን ዕሙን ነው፤ በሀገራችን የተቀነቀኑ የበርካታ ዘፈኖች ግጥም እና ዜማቸው ወንዳዊ ጠባይ በጉልህ የሚንጸባረቅባቸው ናቸው። ለአብነት እንኳን ከተባእት ጾታ ድግምግሞሻዊ መገለጫዎች መካከል፡- መደለቅ፣ መርገጥ፣ መጋለብ፣ ማካለብ እና ሌሎችም ተጠቃሾች ናቸው፤ የተጠቀሱ ባሕርያት በሙዚቃችን ገላ ውስጥ ጥላ ጥለው ከርመዋል። አሁን፣ አሁን በመጠኑም ቢሆን ሙዚቃችን ሴቴአዊነትን እየተላበሰ መጥቷል - ከ1980-81 ዓ.ም. ወዲህ፤ ከመደለቅ፣ ከመርገጥ እና ከመጋለብ አልፎ ወደ ሴቴአዊ መንሰፍሰፍ እያደላ መጣ ሙዚቃችን - በአበበ መለሠ። ስፓኛዊው ሰዓሊ ፐብሎ ፒካሶ ጥበብ ከውስጥ ስትመነጭ ጣዕመኛ ነች የሚላት ይትባሃል አለቺው፤ አቤም እንዲያ ነው - በሥራዎቹ የውስጣችንን ድብቅ ሚስጥር ጫር አድርጎ ያልፋል፤ በእንስፍስፍ ስልት የተብሰለሰለ ውስጣችንን ጎብኝቶ ለሌላ ተመስጦ አምነሽንሾን ሸርተት ይላል፤ ማሳተፍ ጠባዩ ሆነ ማለት ነው።

የሴት ሥነ-ልቡና የዘለቀው ሙዚቀኛ ነው አቤ፤ ወንድ ሆኖ ሳለ በሴት ይትባሃል የማንሰፍሰፍ ክኅሎት ያደለው ደራሲ። የሚደርሳቸው የዘፈን ዜማዎች ብርክ የማድረግና የማራድ ጉልበት አላቸው። ኩልል ያለ የቆለኛ ድምጽ ዓይነት ዜማዎች እና ስርቅርቅ ስልቶች በድርሰቶቹ ገላ ውስጥ ይስተዋላሉ። ከስምንት መቶ (800) በላይ የዜማ ድርሰቶችን ጀባ ብሏል። አመለ ሸጋ እና ተጫዋች ነው፤ ከዘፈን ዜማ አልፎ ክራር እና ኪቦርድ በወጉ ይጫወታል። 1978 ዓ.ም. መገባደጃ አካባቢ ከጎንደር ወደ አዲስ አበባ ተከተተ - ከፋሲለደስ የኪነት ቡድን ጋር ለወጣቶች ፌስቲቫል ወደ ኮሪያ ሊዘምት። አልሆነም ነበር ታዲያ፤ በአዲስ አበባ ቲያትር ቤቶች ሲያንዣብብ እያዩ ማንያዘዋል (የ‹‹ዕድሌ ጠማማ›› ዘፈን አቀንቃኝ) ጋር ይገናኛሉ። የ‹‹ልቤ ገራገሩ››ን ዘፈን ግጥም በአንድ ምሽት ደርሶ ጀባ ካለው በኋላ ወደ ጎንደር ይተማል - ብዙም ሳይቆይ ወደ አዲስ አበባ ተመለሰ…

…ከግጥም እና ዜማ ደራሲው ከጸጋዬ ደቦጭ ጋር ለጸጋዬ እሸት፣ ለኬኔዲ መንገሻ እና ለአሠፉ ደባልቄ በሠራቸው ሥራዎች ተወዳጅነትን አተረፈ። አቤ በግጥምና ዜማ ድርሰቶቹ ማንሰፍሰፍ ያውቅበታል፤ ወንድ ደራሲ የሴት ዓይነት ማራድን በሙዚቃ ሥራዎቹ…

…የእናት ዓይነት የአንጀት መንሰፍሰፍ እና ተብሰልስሎት በዋናነት በዜማ ድርሰቶቹ ውስጥ ይንጸባረቃሉ፤ አዚሞ ማንሰፍሰፍን ተክኖበታል። እውስጥ የሚቀሩ ዜማዎችን ለበርካታ ድምጻዊያን አበርክቷል፤ ለማሳያ ያህል፡-

1. ለጌታቸው ካሳ፡- ‹‹ቀና ብዬ ሳየው›› (ዜማ) (ግጥም ጸጋዬ ደቦጭ)
2. ለኤፍሬም ታምሩ፡- ‹‹ቢልልኝ›› (ዜማ)
3. ለሂሩት በቀለ፡- ‹‹የእኔ ዓለም››፣ ‹‹ጠላኝ እንዳልለው›› (ዜማ)
4. ለባለቤቱ/ፍቅርአዲስ፡- ‹‹እርሳኝ›› (ዜማ)፣ ‹‹አልገባኝም›› (ግጥምና ዜማ)፣ ‹‹ዝም እላለሁ›› (ዜማ) - ካሴት 1984 ዓ.ም.፣ ‹‹ላባብለው›› 1989፣ ‹‹ሳብ በለው›› 1993 ካሴቶች
5. ለአሠፉ ደባልቄ፡- ‹‹የሆዴን›› (ግጥምና ዜማ)
6. ለሰርጉዓለም ተገኝ፡- ‹‹ሳላያት አመሸሁ›› (ዜማ)
7. ለየሺእመቤት ዱባለ፡- ‹‹ለዚህ በቃሁ››፣ ‹‹ትዝ አለኝ›› (ዜማ)
8. ለጸጋዬ እሸቱ፡- ‹‹ሆዴ ክፉ ዕዳዬ›› (ዜማ)፣ ‹‹መሸ›› (ግጥምና ዜማ)፣ ‹‹ያየ አለ›› (ዜማ)፣ ‹‹ተከለከለ አሉ›› (ዜማ)
9. ለማሐሙድ አሕመድ፡- ‹‹ስንቱን አሳለፍኩት›› (ዜማ)
10. ለኬኔዲ መንጋሻ፡- ‹‹ፋንታዬ›› ካሴት - ‹‹ፋንታዬ›› ‹‹አንቺ ዓለም›› ‹‹እንግባ ሀገራችን/ከየሺእመቤት ጋር›› (ግጥምና ዜማ)
11. ለቴዎድሮስ ታደሠ እና አሠፉ ደባልቄ፡- ‹‹ላጉርስሽ›› (ዜማ)
12. ለአበበ ተካ፡- ‹‹ወፍዬ››፣ ‹‹ሰው ጥሩ/ማን አላት ሰው ሐገር›› - ካሴት ሙሉውን ዜማ (ግጥሙ የአያ ሙሌ - ሙሉጌታ ተስፋዬ ነው)
13. ለሐመልማል አባተ፡- ‹‹ይዳኘኝ ያየ›› (ዜማ)
14. ለጎሳዬ ተስፋዬ፡- ‹‹የሐመሯ›› (ዜማ)
15. ለሞኒካ ሲሳይ፡- ‹‹ቀኑ አጠረ›› (ዜማ)
16. ለይርዳው ጤናው፡- ‹‹ላፍ አርጋት›› ሙሉ ካሴት (ሶስና ታደሠ ደግሞ ሙሉ ግጥም)
17. ለጸደኒያ ገ/ማርቆስ ሙሉ ካሴት፡- ከ‹‹ላፍ አርጋት›› ካሴት ዕኩል (ሶስና ታደሠ ደግሞ ሙሉ ግጥም)
18. ለይሁኔ በላይ፡- ‹‹የሰው ሐገር›› (ግጥምና ዜማ)
19. አሁንም ለባለቤቱ፡- ‹‹ምስክር›› - ካሴት፤ ይልማ ገ/አብ እና ቢኒአሚር አሕመድ ታክለውበታል
20. ለዳዊት ጽጌ፡- ‹‹እትቱ›› (ዜማ) - ግጥም፡- ናትናኤል ግርማቸው
21. ለተመስገን ተስፋዬ፡- ‹‹ሳቢዬ›› (ዜማ) - ግጥም፡- ናትናኤል ግርማቸው

እና ሌሎች ተጠቃሾች ናቸው። ለዛሬ የሰርጉዓለም ተገኝን

‹‹ሳላያት አመሸሁ፣ ሳላያት፤
እመጣለሁ እያልኩ - እየዋሸሁ፤
ነገር አበላሸሁ - እያመሸሁ፤›› ተጋበዙልኝ።

አቤ ዕድሜና ጤና ይስጥህ፤ አመሰግናለሁ!
@Bookfor
@Bookfor

BY @Book for all


Share with your friend now:
tgoop.com/bookfor/1361

View MORE
Open in Telegram


Telegram News

Date: |

Content is editable within two days of publishing 2How to set up a Telegram channel? (A step-by-step tutorial) Just at this time, Bitcoin and the broader crypto market have dropped to new 2022 lows. The Bitcoin price has tanked 10 percent dropping to $20,000. On the other hand, the altcoin space is witnessing even more brutal correction. Bitcoin has dropped nearly 60 percent year-to-date and more than 70 percent since its all-time high in November 2021. A vandalised bank during the 2019 protest. File photo: May James/HKFP. Concise
from us


Telegram @Book for all
FROM American