tgoop.com/deacongetabalewamare/1829
Last Update:
🍂 #ቅዱስ_መርቆሬዎስ ሰማዕት
ህዳር 25 በዓለ ዕረፍቱ
✝️ ቅዱስ መርቆሬዎስ የነበረበት ዘመን በሶስተኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ ንጉስ ዳክዮስ የሮም ገዥ ሆኖ የነገሰበት ዘመን እንደመሆኑ በዘመኑ የተከበረ የተባለ የውትድርናን ትምህርት ተምሮ ለንጉሱ አገልጋይ ሁኖ ነበር ።
✝️ አባቱ በአደን ላይ ሳለ ሊበሉት ከመጡ ገጸ ከለባት እግዚአብሔር ስላዳነውና እንዲያውም አገልጋዮች ስላደረጋቸው በዚህ ተአምር መነሻነት ቤተሰቡ ሁሉ በክርስትና ሐይማኖት አምነው ተጠምቀዋል ።
ከጥምቀት በኋላ
አባቱ ✝️ ኖኅ
እናቱ ✝️ ታቦት
ተብለው ተሰይመዋል
✝️ቅዱሱም ፕሉፓዴር ከሚባል ከቅድሞ ስሙ መርቆሬዎስ ተብሏል። ትርጓሜውም የአምላክ አገልጋይ ማለት ነው።
🍂 ባርባርያን በሮም ላይ በጠላትነት በተነሱ ጊዜ ቅዱስ መርቆሬዎስ የጦር አዛዥ ነበርና የእግዚአብሔር መልአክ በሰጠው ሰይፍ በመዋጋት ድልን ተቀዳጅቷል። የባርባርያንን ንጉሥም ገድሎታል።
🍂 ንጉስ ዳኬዎስ ግን “ ድልን የሰጡን ጣዖታቴ ናቸው። “ በማለት ለጣዖታቱ በዓል አደረገ ። ቅዱስ መርቆሬዎስ ይህንን ድርጊት በአደባባይ ተቃወመ በንጉሱም ፊት ትጥቁንና ልብሱን ማዕረጉንም አውልቆ ወረወረው።
🍂 በዚህ የተቆጣው ንጉሡም በወታደሮች አስይዞ መከራን ያደርሱበት ዘንድ ወደ ቂሳሪያ ( ቀጰዶቅያ ) ላከው ።በዚያም የሰማዕትነት ስቃይን ከተቀበለ በኋላ ፦
✝️ በኅዳር 25 ቀን አንገቱን ተሰይፎ የሰማዕትነት ተጋድሎውን ፈጸመ ።
✝️ ቅዱስ መርቆሬዎስ ከዕረፍቱ በኋላ ጸሊም (ጥቁር) የሆነ ፈረሱ ለሰባት ዓመታት በየሀገሩ እየዞረ ስለ ክርስቶስ መስክሯል።
✝️ በንጉሡ በዑልያኖስ ዘመን ክርስቲያኖች መከራና ስቃይ በበዛባቸው ጊዜ ሊቀ ጳጳስ ባስልዮስና ጎርጎርዮስ በቅዱስ መርቆሬዎስ #ሥዕል ፊት ሲጸልዩ ሳለ
“ #አድነነ_ሥዕል_ከመ_ዘይብል_ኦሆ “
/ #ስዕሉም_እንደሚታዘዝ_ዘንበል_አለ።/
🍂በስእሉ ላይ ቅዱስ መርቆሬዎስ ከሀዲውን ንጉስ ዑልያኖስን ሲገድለው ከጦሩም ጫፍ ትኩስ ደም ሲንጠባጠብ ታየ።
ባስልዮስና ጎርጎርዮስም ከክርስቲያን ወገኖቻቸው ጋር እጅግ ተደሰቱ ። ቅዱስ መርቆሬዎስ ከሐዲውን ንጉሥ ዑልያኖስን ስላጠፋላቸው እግዚአብሔርን አመሰገኑ ።
🙏🏽የቅዱስ መርቆሬዎስ ረድኤት በረከት አይለየን
ከመከራ ከመከራ ነፍስ ይጠብቀን 🙏🏽
👉🏻#ሠዐሊ_ቀሲስ_አማረ_ክብረት እንደሣሉት
ዲያቅን ጌታባለው አማረ
የቅዱሳት ሥዕላት ሠዐሊ
@deacongetabalewamare
BY Dn Getabalew Amare Kibret /ሰዐሊ/
Share with your friend now:
tgoop.com/deacongetabalewamare/1829