tgoop.com/eotcbete/452
Last Update:
#የታላቋ_ቅድስት_ቤተ_ክርስቲያናችንን
#ሕግና_ሥርዓት_አክብረን_እናስከብር፤
⛪️በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን።⛪️
⛪️፩. #በቅዳሴ_ጊዜ_ያሉ_ሥርዓቶች፦
🔔 “አሐዱ አብ” ሳይባል በሰዓት መድረስ፤
🔔 “በሰላም ግቡ” ሳይባል አለመውጣት፤
🔔 የግል የጸሎት መጽሐፍ አለማንበብ፤
🔔 በቅዳሴ ጊዜ ከቦታ ቦታ አለመዘዋወር፤
🔔 የግል ሰላምታ፣ ወሬና ስልክ አለማውራት፤
🔔 የቤተ ክርስቲያን ቦታን የግል አለማድረግ፤
🔔 መቅደስ ውስጥ ለልጆች ምንም ዓይነት ምግብ መስጠት አይቻልም፤ ከቅዱስ ቊርባን በኃላ ዘቢብ (በቍርባን ቀን ከደረቀ ዘቢብ በውኀና በጽዋ እየታሸ ለቈራቢዮች የሚሰጠው የክርስቶስ
ደም ዘቢብ ይባላል) ብቻ ይፈቀዳል።
⛪️፪. #የቅዳሴ_ጠበል_ሥርዓት፦
🔔 የቅዳሴ ጠበል ይዞ አለመውጣት፤
🔔 በቅዳሴ ጠበል ፊትን አለመዳበስ እንዲሁም እንዳይፈስ መጠንቀቅ፤
⛪️፫. #የአለባበስ_ሥርዓት፦
🔔 ሕፃናት ልጆችን ክርስቲያናዊ አለባበስ ማልበስ
🔔 ሴት ልጅ ረጅም ቀሚስና ነጠላ ትልበስ
🔔 ሴት ልጅ ፀጉርዋን በነጭ ሻሽ ትሸፍን፤ ሱሪም አትልበስ
🔔 ወንድ ልጅ አግባብ ያለው ሱሪ፣ ነጠላና እጀ ሙሉ የሆነ ልብስ ያድርግ
🔔 ማንኛችንም ከተፈጥሮ ውጭ የሆኑ ሜካፕ፦ ዊግ፣ ጥፍር ቀለም፣ ሊፒስቲክና ሌሎችንም ነገሮች አለመጠቀም
👉“ሴት የወንድ ልብስ አትልበስ ወንድም የሴት ልብስ አይልበስ፤ ይህን የሚያደርግ በአምላክህ በእግዚአብሔር ዘንድ የተጠላ ነው።” ዘዳ. ፳፪፥፭
👉“ሴት ራስዋን ሳትሸፍን ወደ እግዚአብሔር ልትጸልይ ይገባታልን? ወንድ ጠጉሩን ቢያስረዝም ነውር እንዲሆንበት” ፩ኛ ቆሮ. ፲፩፥፲፫-፲፬
⛪️፬. የካህናትን፣ የወንዶችንና የሴቶችን መግቢያ በር መለየት፤
⛪️፭. ለቅድስት ቤተ ክርስቲያን ክብር ስንል፦
🔔 ጫማችንንና ካልሲያችንን ከግቢ በር ማውለቅ (በፌስታል መያዝ)
🔔 የቤተ ክርስቲያናችንን ልዩ መዓዛ ለመጠበቅ መጥፎ የሰውነት ጠረንን ማጥፋት (የግል ንጽሕናን መጠበቅ)
“የቆምክባት ስፍራ የተቀደሰች መሬት ናትና ጫማህን ከእግርህ አውጣ” ዘፀ. ፫፥፭
⛪️፮. ሴት ልጅ ጠበል በቅዳት እና መዝጋት መክፈት፤ እምነት ቆፍሮ ማውጣት ስለማትችል ወንዶችን ትጠይቅ፤
⛪️፯. ከመንፈስ ቅዱስ ጸጋ፣ ከእመቤታችን አማላጅነት፣ ከቅዱሳን መላእክት ተራዳኢነት፣ ከጻድቃን ሰማዕታት እንዲሁም ከቅዱሳን አባቶቻችን በረከት እንድናገኝ፤ ቤተ ክርስቲያን እንዳንሄድ እንቅፋት ከሚሆንብን ነገሮች፤ ከቡና፣ ጫት፣ ሲጋራ፣ ስጋር፣ ሀሜት፣ ዝሙት፣ ሙስና፣ በሀሰት ከመመስከር እንዲሁም ከማንኛውም መጥፎ ነገሮች ራስን ማራቅ ይገባናል።
“የእግዚአብሔርን እና የአጋንንትን ጽዋ አንድ አድርጋችሁ መጠጣት አትችሉም።” ፩ኛ ቆሮ. ፲፥፳፩
••┈┈••●◉ ✞◉●••┈┈••✥
⛪@eotcbete✝✝✝
⛪@eotcbete✝✝✝
⛪@eotcbete✝✝
BY የተዋህዶ መንፈሳዊ ምስሎች ✝
Share with your friend now:
tgoop.com/eotcbete/452