EOTCY Telegram 2234
ኦርቶዶክሳዊ ትምህርቶች
🌹ልደታ ለማርያም🌹፦ ከዕሴይ ሥር በትር ትወጣለች በኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ግንቦት አንድ ቀን (የግንቦት ልደታ) የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም ልደት የሚከበርበት ዕለት ነው፡፡ ይህ ዕለት ቅዱስ ኤፍሬም በውዳሴ ማርያም ‹‹የመመኪያችን ዘውድ፣ የንጽሕናችንም መሰረት›› ያላት ወላዲተ አምላክ ድንግል ማርያም የተወለደችበት ነው፡፡ ነቢየ እግዚአብሔር ኢሳይያስ ‹‹ድንግል ትጸንሳለች፤ ወንድ…
[ ኦርቶዶክሳዊ ትምህርቶች ]

የብርሃን እናት ዛሬ ተወለደች

         "ሐና አንቺን ያፈራችባት
      ኢያቄምም  አንቺን ለሕይወት ያፈራባት
     የደስታ ሰዓት ምንኛ የተባረከች የተቀደሰች ናት
      የዓለሙ ሁሉ መድኃኒት አንቺ ነሽና
     አንዲት ርግቤ ሆይ ተአምርሽን አመሰግናለው "
                              ማኅሌተ ጽጌ


የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም የልደት ቀን ለክርስቲያኖች ሁሉ የደስታ ዕለት ናት ቅዱስ ያሬድ " ከኢያቄምና ከሐና ስለተወለደች ስለማርያም ልደት ዛሬ ደስታ ሆነ የብርሃን እናት በእውነት ተወለደች" እንዳለ ይህ ቀን የደስታችን ቀን ነው ለምን ቢሉ የመመኪያችን ዘውድ የንጽሕናችን መሠረት ድንግል ማርያም የተወለደችበት ዕለት ነውና፣ የነቢያት የትንቢታቸው ፍጻሜ የዓለም ብርሃን የተባለ መድኃን ዓለም ኢየሱስ ክርስቶስን የምትወልድን የብርሃን እናቱ ድንግል ማርያም የተወለደችበት ዕለት ነውና ነው ፡፡
የእመቤታችን ልደት እንደ እንግዳ ደራሽ እንደ ውሃ ፈሳሽ በድንገት የሆነ አይደለም አስቀድሞ በነቢያት ትንቢት የተነገረለት በአበው ሕይወት ውስጥ ምሳሌ የተመሰለለት ነው ለአብነትም
~ ልበ አምላክ ቅዱስ ዳዊት " መሠረቷቿ የተቀደሱ ተራሮች ናቸው "መዝ 86፡-1 ብሎ በዝማሬው የተቀኘው ስለእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ወላጆች ንጽህና ነው  የተቀደሱ ተራሮች ያለውም የእመቤታችን ሥርወ ልደት ከቤተ መንግሥትና ከቤተ ክህነት ከሆኑት ከተቀደሱት ከኢያቄምና ከሐና የመሆኑን ነገር ሲያመለክት ነው፡፡ ይህንን ትንቢትና እውነተኛውን የእመቤታችንን የትውልድ ሀረግ አስማምታ ቤተክርስቲያን ‹‹የእመቤታችን ማርያም ትውልዷ በአባቷ በኩል ከንጉሡ ከዳዊት ወገን ነው፤ በእናቷም በኩል ከካህኑ ከአሮን ወገን ነው፤ የአባቷ ስም ኢያቄም ነው፤ የእናቷም ስም ሐና ነው፡፡›› ብላ ታስተምራለች፡፡
~ ጠቢቡ ሰሎሞንም "ሙሽራዬ ሆይ ከሊባኖስ ከእኔ ጋር ነይ" መኃ 4፡8 ብሎ ሙሽራ የምትባል ድንግል ማርየም የት እንደምትወለድ ጭምር አስቀድሞ በትንቢት ነግሮናል
@eotcy
በኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መጻሕፍት መሰረት የእመቤታችን የትውልድ ስፍራ ሊባኖስ የተባለው ተራራማ ሀገር ነው፡፡ የዚህ ትንቢት ምስጢርም የእመቤታችን መካነ ልደት የሊባኖስ ተራራ ስለመሆኑ የሚያጠይቅ እንደሆነ ሊቃውንት ቤተ ክርስቲያን ያስረዳሉ ትንቢቱም ሲፈጸም ቅድስት ድንግል ማርያም ግንቦት 1 ቀን በሊባኖስ ተራራ ተወልዳለች
~ እናት እና አባቷ እርሷን ከመውለዳቸው በፊት በተቀደሰ ትዳር እየኖሩ ልጅ አጥተው እግዚአብሔርን ደጅ በመጥናት የሚኖሩ ቅዱሳን ነበሩ  እግዚአብሔር ከልጅ ሁሉ በላይ የሆነች አምላክን የምትወልድ ልጅን ሰጣቸው ስሟንም ማርያም ብለው ጠርተዋታል ጸጋ ወ ሐብት ማለት አስቀድማ ጸጋ /ስጦታ፣ ሐብት /በረከት ሆና ለእናት እና አባቷ ተሰጥታለች በፍጻሜ ግን መድኃኒት የተባለ ክርስቶስን ወልዳለች እና ለሰው ሁሉ ስጦታ ናት ነቢየ እግዚአብሔር ኢሳያስ የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር ዘርን ባያስቀርልን ኖሮ እንደ ሰዶም በሆንን ገሞራንም በመሰልን ነበር እንዳለ ጠፍተን እንዳንቀር ምክንያተ ድኂን የሆነችን ድንግል ማርያም ስጦታችን ናት ፡፡

 ቅዱስ እንድርያስ የከበረ ስለሆነው ስለ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ልደት ታላቅነት ‹‹ይህ በዓል በሐዲስና በብሉይ ኪዳን መካከል መገኛ ሆነ፡፡ ምሳሌዎቹ በእዉነታ፣ አሮጌው በአዲስ ቃል ኪዳን ተተኩ፡፡ ፍጥረት ሁሉ በደስታ ይዘምራል፤ የዚህን ቀንም ደስታ ይካፈላል፡፡ ይህ ዕለት (ጌታ) መቅደሱን የሰራበት ዕለት ነው፡፡ ይህ ዕለት ትልቅ ሕንፃ የታነጸበትና ፍጡር የፈጣሪ ማደሪያ ለመሆን የተዘጋጀበት ዕለት ነው፡፡” በማለት ገልጾታል፡፡ የእርሷ ልደት የልዑል ማደሪያው መቅደስ የተሰራበት ዕለት ነውና ሁላችን እናከብረዋለን፡፡ በዚህም ዕለት ‹‹ዮም ፍስሐ ኮነ በእንተ ልደታ ለማርያም/ እነሆ ዛሬ በእመቤታችን ልደት ደስታ ሆነ›› እያልን እንዘምራለን
   
" ኢያቄምና ሐና  በጸለዩ በአለቀሱ ጊዜ
  ለሁላችን ምእመናን መጠጊያ የምትሆን
  ኃጢአት ይቅር የምታስብል ሴት ልጅ አገኙ
  ሁለቱ ሽማግሌዎች ሰማይን ወለዱ
  ሰማያቸውም ጸሐይን አስገኘች "

                         ነግሥ ዘልደታ
@eotcy



tgoop.com/eotcy/2234
Create:
Last Update:

[ ኦርቶዶክሳዊ ትምህርቶች ]

የብርሃን እናት ዛሬ ተወለደች

         "ሐና አንቺን ያፈራችባት
      ኢያቄምም  አንቺን ለሕይወት ያፈራባት
     የደስታ ሰዓት ምንኛ የተባረከች የተቀደሰች ናት
      የዓለሙ ሁሉ መድኃኒት አንቺ ነሽና
     አንዲት ርግቤ ሆይ ተአምርሽን አመሰግናለው "
                              ማኅሌተ ጽጌ


የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም የልደት ቀን ለክርስቲያኖች ሁሉ የደስታ ዕለት ናት ቅዱስ ያሬድ " ከኢያቄምና ከሐና ስለተወለደች ስለማርያም ልደት ዛሬ ደስታ ሆነ የብርሃን እናት በእውነት ተወለደች" እንዳለ ይህ ቀን የደስታችን ቀን ነው ለምን ቢሉ የመመኪያችን ዘውድ የንጽሕናችን መሠረት ድንግል ማርያም የተወለደችበት ዕለት ነውና፣ የነቢያት የትንቢታቸው ፍጻሜ የዓለም ብርሃን የተባለ መድኃን ዓለም ኢየሱስ ክርስቶስን የምትወልድን የብርሃን እናቱ ድንግል ማርያም የተወለደችበት ዕለት ነውና ነው ፡፡
የእመቤታችን ልደት እንደ እንግዳ ደራሽ እንደ ውሃ ፈሳሽ በድንገት የሆነ አይደለም አስቀድሞ በነቢያት ትንቢት የተነገረለት በአበው ሕይወት ውስጥ ምሳሌ የተመሰለለት ነው ለአብነትም
~ ልበ አምላክ ቅዱስ ዳዊት " መሠረቷቿ የተቀደሱ ተራሮች ናቸው "መዝ 86፡-1 ብሎ በዝማሬው የተቀኘው ስለእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ወላጆች ንጽህና ነው  የተቀደሱ ተራሮች ያለውም የእመቤታችን ሥርወ ልደት ከቤተ መንግሥትና ከቤተ ክህነት ከሆኑት ከተቀደሱት ከኢያቄምና ከሐና የመሆኑን ነገር ሲያመለክት ነው፡፡ ይህንን ትንቢትና እውነተኛውን የእመቤታችንን የትውልድ ሀረግ አስማምታ ቤተክርስቲያን ‹‹የእመቤታችን ማርያም ትውልዷ በአባቷ በኩል ከንጉሡ ከዳዊት ወገን ነው፤ በእናቷም በኩል ከካህኑ ከአሮን ወገን ነው፤ የአባቷ ስም ኢያቄም ነው፤ የእናቷም ስም ሐና ነው፡፡›› ብላ ታስተምራለች፡፡
~ ጠቢቡ ሰሎሞንም "ሙሽራዬ ሆይ ከሊባኖስ ከእኔ ጋር ነይ" መኃ 4፡8 ብሎ ሙሽራ የምትባል ድንግል ማርየም የት እንደምትወለድ ጭምር አስቀድሞ በትንቢት ነግሮናል
@eotcy
በኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መጻሕፍት መሰረት የእመቤታችን የትውልድ ስፍራ ሊባኖስ የተባለው ተራራማ ሀገር ነው፡፡ የዚህ ትንቢት ምስጢርም የእመቤታችን መካነ ልደት የሊባኖስ ተራራ ስለመሆኑ የሚያጠይቅ እንደሆነ ሊቃውንት ቤተ ክርስቲያን ያስረዳሉ ትንቢቱም ሲፈጸም ቅድስት ድንግል ማርያም ግንቦት 1 ቀን በሊባኖስ ተራራ ተወልዳለች
~ እናት እና አባቷ እርሷን ከመውለዳቸው በፊት በተቀደሰ ትዳር እየኖሩ ልጅ አጥተው እግዚአብሔርን ደጅ በመጥናት የሚኖሩ ቅዱሳን ነበሩ  እግዚአብሔር ከልጅ ሁሉ በላይ የሆነች አምላክን የምትወልድ ልጅን ሰጣቸው ስሟንም ማርያም ብለው ጠርተዋታል ጸጋ ወ ሐብት ማለት አስቀድማ ጸጋ /ስጦታ፣ ሐብት /በረከት ሆና ለእናት እና አባቷ ተሰጥታለች በፍጻሜ ግን መድኃኒት የተባለ ክርስቶስን ወልዳለች እና ለሰው ሁሉ ስጦታ ናት ነቢየ እግዚአብሔር ኢሳያስ የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር ዘርን ባያስቀርልን ኖሮ እንደ ሰዶም በሆንን ገሞራንም በመሰልን ነበር እንዳለ ጠፍተን እንዳንቀር ምክንያተ ድኂን የሆነችን ድንግል ማርያም ስጦታችን ናት ፡፡

 ቅዱስ እንድርያስ የከበረ ስለሆነው ስለ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ልደት ታላቅነት ‹‹ይህ በዓል በሐዲስና በብሉይ ኪዳን መካከል መገኛ ሆነ፡፡ ምሳሌዎቹ በእዉነታ፣ አሮጌው በአዲስ ቃል ኪዳን ተተኩ፡፡ ፍጥረት ሁሉ በደስታ ይዘምራል፤ የዚህን ቀንም ደስታ ይካፈላል፡፡ ይህ ዕለት (ጌታ) መቅደሱን የሰራበት ዕለት ነው፡፡ ይህ ዕለት ትልቅ ሕንፃ የታነጸበትና ፍጡር የፈጣሪ ማደሪያ ለመሆን የተዘጋጀበት ዕለት ነው፡፡” በማለት ገልጾታል፡፡ የእርሷ ልደት የልዑል ማደሪያው መቅደስ የተሰራበት ዕለት ነውና ሁላችን እናከብረዋለን፡፡ በዚህም ዕለት ‹‹ዮም ፍስሐ ኮነ በእንተ ልደታ ለማርያም/ እነሆ ዛሬ በእመቤታችን ልደት ደስታ ሆነ›› እያልን እንዘምራለን
   
" ኢያቄምና ሐና  በጸለዩ በአለቀሱ ጊዜ
  ለሁላችን ምእመናን መጠጊያ የምትሆን
  ኃጢአት ይቅር የምታስብል ሴት ልጅ አገኙ
  ሁለቱ ሽማግሌዎች ሰማይን ወለዱ
  ሰማያቸውም ጸሐይን አስገኘች "

                         ነግሥ ዘልደታ
@eotcy

BY ኦርቶዶክሳዊ ትምህርቶች





Share with your friend now:
tgoop.com/eotcy/2234

View MORE
Open in Telegram


Telegram News

Date: |

In handing down the sentence yesterday, deputy judge Peter Hui Shiu-keung of the district court said that even if Ng did not post the messages, he cannot shirk responsibility as the owner and administrator of such a big group for allowing these messages that incite illegal behaviors to exist. Matt Hussey, editorial director at NEAR Protocol also responded to this news with “#meIRL”. Just as you search “Bear Market Screaming” in Telegram, you will see a Pepe frog yelling as the group’s featured image. Those being doxxed include outgoing Chief Executive Carrie Lam Cheng Yuet-ngor, Chung and police assistant commissioner Joe Chan Tung, who heads police's cyber security and technology crime bureau. According to media reports, the privacy watchdog was considering “blacklisting” some online platforms that have repeatedly posted doxxing information, with sources saying most messages were shared on Telegram. The creator of the channel becomes its administrator by default. If you need help managing your channel, you can add more administrators from your subscriber base. You can provide each admin with limited or full rights to manage the channel. For example, you can allow an administrator to publish and edit content while withholding the right to add new subscribers.
from us


Telegram ኦርቶዶክሳዊ ትምህርቶች
FROM American