tgoop.com/eotcy/2270
Create:
Last Update:
Last Update:
ክርስቲያን ከሆንክ እነዚህን 7 ነገሮች መቼም አታድርግ
1. ለንስሐ ተዘጋጅ ወደ ቤተክርስቲያን ና ወገብህን ሱሪህን ታጠቅ
2. ነገርን ሁሉ በ3ቱ መሥፈርት ሳትመዝን አትቀበል
☞︎︎︎ መጽሐፍ ቅዱስ
☞︎︎︎ አዋልድ መጻሕፍት
☞︎︎︎ ቅዱስ ትውፊት
3. ለማብዛትም ሆነ ምን አለበት ብለህ መቼም ቢሆን
☞︎︎︎ ከአህዛብና
☞︎︎︎ ከመናፍቃን
ጋር አትተባበር። እነርሱ ካሉ እግዚአብሔር ይለይሃልና❗️
ብርሃን ከጨለማ ጋር ህብረት የለውምና❗️
4.ምንም ነገርን ከመቀበልህ ከመንቀፍህና ከመደገፍህ በፊት:-
☞︎︎︎ እንደ ክርስቲያን ለፈጣሪህ ንገር
☞︎︎︎ እንደ ሰው አገላብጠህ መርምር
5.ከእግዚአብሔር እና የርሱ የሆኑት በቀር ፈጽመህ ምስጢርህን አትግለጽ❗️
ኋላ ተወግተህ የምትሞተው ባወጣኸው ምስጢር:- አመንኩት ባልከው ሰው ነውና❗️
6.የቤተክርስቲያንን ሥርዓት ትጠብቅ ታስጠብቅም ዘንድ ቸል አትበል❗️
አጥሩ ከፈረሰ ቤቱም መፍረሱ ፣ መዘረፉም አይቀርምና❗️
7.በሰማይ ካለው እግዚአብሔር እና ወዳዶቹ በቀር በሥጋ ለባሽ አትታመን❗️ አትከተለው፣ አታድንቀው፣ አታምልከው
በዚች በተቀጥተኛዋ ሀይማኖታችን ፀንተን የመንግስቱ ወራሾች ያድርገን
ወሰብሐት ለእግዚአብሔር
"...........እነሆ፥ የተወደደው ሰዓት አሁን ነው፤ የመዳን ቀን አሁን ነው"
--2ኛ ቆሮ 6፥2
BY ኦርቶዶክሳዊ ትምህርቶች

Share with your friend now:
tgoop.com/eotcy/2270