EOTCY Telegram 2272
ጉድለትህን ተጠቀምበት

ዘኪዎስ በማጠሩ ምክንያት በኢያሪኮ እያለፈ ያለውን ክርስቶሰን ለማግኘት ተቸገረ። ሕዝቡ ብዙ ነው የቆሙት ሁሉ ጌታን ከማየት ከለሉት። የሾላ ዛፍ ላይ ወጥቶ ጌታን ለማየት ሲሞክር ጌታ አሻቅቦ አየው።

እሱ ዛፍ ላይ ሊያይ እንጂ ሊታይ አልወጣም። ጌታ ሊታዩ ከሚሞክሩ ይልቅ ሊያዩት የሚሹትን ይወዳልና ዘኪዎስን ጠራው።

ከምድር ቆመን ዓይናችንን አንጋጥጠን ማረን የምንለው ጌታ ዘኪዎስን ከምድር ሆኖ ወደ ላይ እያየ ና ልማርህ አለው።
"ዛሬ በቤትህ እውል ዘንድ ይገባኛል" አለው። ጌታ ወደ ቤቱ ገባ ለዘኪዎስ ቤት መዳን ሆነለት።

ዘኪዎስ አጭር ባይሆን ኖሮ ከሰዎች ጋር እየተጋፋ ጌታን ያይ ይሆናል እንጂ በጌታው ዓይን ለመታየት የሚያበቃ ትጋት አያሳይም ነበር። ምናልባትም ሰዎችን ገለል በሉ እያለ በኩራት ሲጋፋ ከአንዱ ጋር ሊጣላ ሊቆይ ይችል ነበር።

ዘኪዎስ አጭር ባይሆን ኖሮ ከዛፍ ላይ አይወጣም ነበር።
ዘኪዎስ አጭር ባይሆን የሠራዊት አምላክ ወደ ቤቱ አይገባም ነበር። በኪሩቤል ላይ የሚቀመጠው ንጉስ በቤቱ ወንበሮች ላይ የተቀመጠው ዘኪዎስ በማጠሩ ምክንያት ነው። የዘኪዎስ ነፍስ የዳነው በቁመቱ ማጠር ነበር።
እግዚአብሔር የማዳኑን ቀን የቆጠረለት ቁመቱን ሲያሳንሰው ነበር። በምድር በመጽሐፍ ቅዱስ በሰማይ በሕይወት መዝገብ ስሙ የተጻፈው ዘኪዎስ አጭር በመሆኑ ነው።

ስለ ቁመቱ የማወራ እንዳይመስልህ።
ለነፍሳችን መዳን የሚያሳጥርብን ብዙ ነገር አለ። እንደ ዘኪዎስ ቁመትህ አጭር ባይሆን የሚያጥርህ ነገር ግን አይጠፋም።

ይሄ ጎደለኝ የምትለው ከሰዎች አነስኩበት የምትለው ነገር አንዳች ነገር የለም እሱን ማለቴ ነው። ይሄ ይጎለኛል ከሰው አንሳለሁ እያልክ አትማረር እጥረትህ መክበሪያህ ነው። ጉድለትህም መዳኛህ ነው።
ችግሮችህ የእግዚአብሔርን ቸርነት ምታባቸው መስታዎቶችህ ናቸው

እግዚአብሔር ያጎደለብህ የመሰለህ ነገር ወደ ዛፍ እንድትወጣ ምክንያትህ ይሁን። በጉድለትህ እንደ ዘኪዎስ ከፍ በልበት። ያኔ ሰዎች አንተን አንጋጠው ከማየት ውጪ አማራጭ አይኖራቸውም።
ፈጣሪ በፍቅሩ ይይህ እንጂ ሰዎች ወዳንተ ያዘነብላሉ።
በቤትህ መዳን ይሆንልሀል፡፡ ከዚያም ስላጠረህ ስለተጎዳህ ነገር ፈጣሪህን ስታመሰግነው ትኖራለህ።

እመነኝ አንዳንድ ጉድለቶች እድሎች ናቸው። ዘኪዎስ አጭር ባይሆን ይሄኔ በሾላው ዛፍ ጥርሱን እየፋቀ ይቀር ነበር።

"...........እነሆ፥ የተወደደው ሰዓት አሁን ነው፤ የመዳን ቀን አሁን ነው"
--2ኛ ቆሮ 6፥2


@eotcy
@eotcy
@eotcy



tgoop.com/eotcy/2272
Create:
Last Update:

ጉድለትህን ተጠቀምበት

ዘኪዎስ በማጠሩ ምክንያት በኢያሪኮ እያለፈ ያለውን ክርስቶሰን ለማግኘት ተቸገረ። ሕዝቡ ብዙ ነው የቆሙት ሁሉ ጌታን ከማየት ከለሉት። የሾላ ዛፍ ላይ ወጥቶ ጌታን ለማየት ሲሞክር ጌታ አሻቅቦ አየው።

እሱ ዛፍ ላይ ሊያይ እንጂ ሊታይ አልወጣም። ጌታ ሊታዩ ከሚሞክሩ ይልቅ ሊያዩት የሚሹትን ይወዳልና ዘኪዎስን ጠራው።

ከምድር ቆመን ዓይናችንን አንጋጥጠን ማረን የምንለው ጌታ ዘኪዎስን ከምድር ሆኖ ወደ ላይ እያየ ና ልማርህ አለው።
"ዛሬ በቤትህ እውል ዘንድ ይገባኛል" አለው። ጌታ ወደ ቤቱ ገባ ለዘኪዎስ ቤት መዳን ሆነለት።

ዘኪዎስ አጭር ባይሆን ኖሮ ከሰዎች ጋር እየተጋፋ ጌታን ያይ ይሆናል እንጂ በጌታው ዓይን ለመታየት የሚያበቃ ትጋት አያሳይም ነበር። ምናልባትም ሰዎችን ገለል በሉ እያለ በኩራት ሲጋፋ ከአንዱ ጋር ሊጣላ ሊቆይ ይችል ነበር።

ዘኪዎስ አጭር ባይሆን ኖሮ ከዛፍ ላይ አይወጣም ነበር።
ዘኪዎስ አጭር ባይሆን የሠራዊት አምላክ ወደ ቤቱ አይገባም ነበር። በኪሩቤል ላይ የሚቀመጠው ንጉስ በቤቱ ወንበሮች ላይ የተቀመጠው ዘኪዎስ በማጠሩ ምክንያት ነው። የዘኪዎስ ነፍስ የዳነው በቁመቱ ማጠር ነበር።
እግዚአብሔር የማዳኑን ቀን የቆጠረለት ቁመቱን ሲያሳንሰው ነበር። በምድር በመጽሐፍ ቅዱስ በሰማይ በሕይወት መዝገብ ስሙ የተጻፈው ዘኪዎስ አጭር በመሆኑ ነው።

ስለ ቁመቱ የማወራ እንዳይመስልህ።
ለነፍሳችን መዳን የሚያሳጥርብን ብዙ ነገር አለ። እንደ ዘኪዎስ ቁመትህ አጭር ባይሆን የሚያጥርህ ነገር ግን አይጠፋም።

ይሄ ጎደለኝ የምትለው ከሰዎች አነስኩበት የምትለው ነገር አንዳች ነገር የለም እሱን ማለቴ ነው። ይሄ ይጎለኛል ከሰው አንሳለሁ እያልክ አትማረር እጥረትህ መክበሪያህ ነው። ጉድለትህም መዳኛህ ነው።
ችግሮችህ የእግዚአብሔርን ቸርነት ምታባቸው መስታዎቶችህ ናቸው

እግዚአብሔር ያጎደለብህ የመሰለህ ነገር ወደ ዛፍ እንድትወጣ ምክንያትህ ይሁን። በጉድለትህ እንደ ዘኪዎስ ከፍ በልበት። ያኔ ሰዎች አንተን አንጋጠው ከማየት ውጪ አማራጭ አይኖራቸውም።
ፈጣሪ በፍቅሩ ይይህ እንጂ ሰዎች ወዳንተ ያዘነብላሉ።
በቤትህ መዳን ይሆንልሀል፡፡ ከዚያም ስላጠረህ ስለተጎዳህ ነገር ፈጣሪህን ስታመሰግነው ትኖራለህ።

እመነኝ አንዳንድ ጉድለቶች እድሎች ናቸው። ዘኪዎስ አጭር ባይሆን ይሄኔ በሾላው ዛፍ ጥርሱን እየፋቀ ይቀር ነበር።

"...........እነሆ፥ የተወደደው ሰዓት አሁን ነው፤ የመዳን ቀን አሁን ነው"
--2ኛ ቆሮ 6፥2


@eotcy
@eotcy
@eotcy

BY ኦርቶዶክሳዊ ትምህርቶች




Share with your friend now:
tgoop.com/eotcy/2272

View MORE
Open in Telegram


Telegram News

Date: |

1What is Telegram Channels? Those being doxxed include outgoing Chief Executive Carrie Lam Cheng Yuet-ngor, Chung and police assistant commissioner Joe Chan Tung, who heads police's cyber security and technology crime bureau. best-secure-messaging-apps-shutterstock-1892950018.jpg Over 33,000 people sent out over 1,000 doxxing messages in the group. Although the administrators tried to delete all of the messages, the posting speed was far too much for them to keep up. Although some crypto traders have moved toward screaming as a coping mechanism, several mental health experts call this therapy a pseudoscience. The crypto community finds its way to engage in one or the other way and share its feelings with other fellow members.
from us


Telegram ኦርቶዶክሳዊ ትምህርቶች
FROM American