tgoop.com/eotcy/2290
Last Update:
አስተማሪ መልእክት ነው አንብቧት
ልቦናውን ሰብሰቦ መጸለይ ያቃተው ወጣት አንድን አባት እንዲህ ሲሉ ይጠይቃቸዋል፣
አባቴ የጸሎት መጽሐፍ ይዤ ስጸልይ ሳነብ ልብናዬ
አይሰብልኝም። አፌ ቢያነብም ልቦናዬ አይተረጉምም
አፌ ቃል ይናገራል አዕምሮየ ግን የጎደለኝን ያጣሁትን ነገር ያሰላስላል።
እኔ ደግሞ ዝም ብዬ ሳስበው:- ቅዱሳን በፍጹም አሳባቸው እያሰቡና እያራቀቁ እንባንና ጸጸትን እየጨመሩ የደረሱትን እኔ በልቤ ላይ የዚህን አለም እያሰብኩ በአፌ ብቻ ባነበንበው እንደገደል ማሚቶ አፌ ላይ ብቻ እየነጠረ ይሄዳል እንጂ ጸሎት አይሆንልኝም።
ስለዚህ አባቴ የአፍ ብቻ ጸሎቴ ቅድመ እግዚአብሔር የማይደርስ ከሆነ ጸሎቴን ብተወው ይሻላል ወይስ ባልተወው ይሻላል? ብሎ ጠየቃቸው።
አረጋዊ አባትም:- እንዲህ ሲሉ አስረዱት
አየህ ልጄ ዐይነ ስውር ሰው በዘንጉ ምድር እየመታ ሲሄድ ከመንገድ ላይ ያለ እባብ ለጊዜው የበትሩን ድምፅ ሰምቶ ይመታኛል ብሎ ይሸሻል እንጂ ዐይነ ስውር ነው አላየኝም ብሎ ባለበት አይጠብቀውም። ስለዚህም አንተም አስተውለህ ብትጸልይ መልካም ቢሆንም ለጊዜው ግን ጭራሽ ከምታቆመው በአፍህ ውስጥ የቃለ እግዚአብሔርን መንኳኳት የሚሰሙ አጋንንት መሸሻቸው አይቀርምና መቼም ቢሆን ጸሎትህን አትተው።
........አጋንንትንም ማባረር አንድ ታላቅ ጥቅም ነውና። ብዙ ከመጸለይህም አንጻር አንዳንድ ጊዜ ልብህ የሚወድቅባት ቃል ተጠራቅማ ወደ እግዚአብሔር ታደርስሃለች።
እናም ልጄ ልብህ ምንም ዝርው ቢሆንም አፍህም የእግዚአብሔር ፍጥረት ነውና ይህንንም እንዳታቆመው።
አሁን አንዱን ይዘህ ወደ ፊት ደግሞ ሁለቱንም ለማግኘት መጣር ይኖርብሃል እንጂ አንተው በዳይ አንተው አኩራፊ ሆነህ ጭራሽ ከአምላክ ርቀህ የጠላት ሰይጣን መጫዎቻ እንዳትሆን ጸሎትህን አትተው አሉት። እኛም እኮ ብዙ መጸለይ ፈልገን በብዙ ሰበብ ሳንጸልይ እንቀራለን ፈጣሪ ግን የልባችንን ያውቃልና ሁሌም ሃሳባችንን ይሞናልናል እግዚአብሔር ሃሳባችንን ሕልማችንን እውን ያድርግልን
"...........እነሆ፥ የተወደደው ሰዓት አሁን ነው፤ የመዳን ቀን አሁን ነው"
--2ኛ ቆሮ 6፥2
Https://www.tgoop.com/eotcy
BY ኦርቶዶክሳዊ ትምህርቶች

Share with your friend now:
tgoop.com/eotcy/2290