tgoop.com/eotcy/2344
Last Update:
#ተስፋ_የለኝም_አትበሉ
በአንድ ወቅት በዝሙት ስራዋ በከተማው የምትታወቅ ሴት የምታገኘውን ገንዘብ ትመጸውት ነበር። ቅዱስ አባ #ጳውሚን ይህን ተግባሯን ሰምቶ ሰዎችን ማጠያየቅ ጀመረ። እንዴት ነች ይህን መጥፎ ስራዎን ትታለችን? ለውጥ አላት? ቢላቸው ነገሩን አጋነው ከራሷ አልፋ ሰዎችንም ቀጥራ ቀሚ መተዳደርያዋ እንዳደረገችው ነገሩት። ይህቺ ሴት ወደ እዚህ ቅዱስ አባት መምጣት እንደምትፈልግና እንዲጸልይላት እንደምትፈልግ ነገር ግን እነዚህ ሰዎች ተፀይፈዋት እንዳላመጧትም ደረሰበት።
ይህ አባት ካለችበት ቦታ ሄደ። ከዚህ በፊት #የእግዚአብሔርን ቃል ሲጸልይ ሰምታ ስለነበር እንዳየችው #እግሩ_ስር_ወድቃ_ማልቀስ_ጀመረች። #እግዚአብሔር ይቅር እንዲለኝ ጸልይልኝ፣ ከአሁን ጀምሮ እከተልሃለሁ እያለች አምራ አለቀሰች። እሱን ተከትላ ወደ ሴቶች ገዳም ገባች። በምንኩስና መላ ዘመኗን #እግዚአብሔርን አገለገለች።
🟢🟡🔴
#ተስፋ_የለኝም: #እግዚአብሔር አይምረኝም አትበል (ይ)
ማንም ይሁን ማንነትህ አንተን የሚወድህ #እግዚአብሔር_ይቅር_ይልሃል ተስፋ አትቁረጥ።
ዱርዬ ነው: ጸጉሩን ይፈትላል: ሱሪውን ዝቅ ያደርጋል: ሜካፕ ታበዛለች: ሱሪ ትለብሳለች በሚል መደምደሚያ ከምንፈርድባቸው በፍቅር እናቅርባቸው እመኑኝ ከእኛ የተሻሉ ታዋቂ ክርስቲያኖች ይሆናሉ።
የምንሰጠው ምጽዋት ከእኛ ንፉግነት ሰርተህ አትበላም?
እጅ እግር እያለህ ብለን እየተሳደብን የሰጠነው ሳይሆን በፍቅር የሰጠነው ምጽዋት በሰማይ ዋጋ አለው
#ቆርኔሌዎስ ለሕዝብም እጅግ ምጽዋት የሚያደርግ ወደ እግዚአብሔርም ሁልጊዜ የሚጸልይ ነበረ። ሐዋ 10፣2
መልካም ቀን ይሁንላቹ
🟢🟡🔴
@eotcy
@eotcy
@eotcy
BY ኦርቶዶክሳዊ ትምህርቶች
Share with your friend now:
tgoop.com/eotcy/2344