tgoop.com/estifanos171/1564
Last Update:
⛪ ደብረ ታቦር ⛪
➣ቡሄ ማለት ምን ማለት ነው?
➣ችቦ በቤተ ክርስቲያን እይታ ?
➣ጅራፍ ማጮህ ምስጢሩ ምንድን ነው ?
➣ሙልሙል በቤተክርስቲያን አንድምታ እንዴት ይታደላል?
🕯... እግዚአብሔር አምላክ ምስጢሩን ጥበቡን ይግለጥልን !!!
።።።።። መልካም 🕯 ንባብ።።።።።
➣ ቡሄ
ቡሄ ብርሃን፣ ደማቅ ማለት ነው፡፡ ጌታችን እና አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ ብርሃነ መለኮቱን በደብረ ታቦር የገለጠበት በዓል የሚዘከርበት እና ለበዓሉም ችቦ ስለሚበራ የብርሃን በዓል ይሰኛል ፡፡ አንድም ደግሞ ወቅቱ የክረምት ጨለማ አልፎ የብርሃን የሚገለጥበት ሰማይ ከጭጋጋማነት ወደ ብሩህነት የሚለወጥበት የመሸጋገሪያ ወቅት ነው፡፡
አበው እንዲህ ሲሉ ወቅቱን ያመላሉ......
“ቡሄ ከዋለ የለም ክረምት ዶሮ ከጮኸ የለም ሌሊት” እንዲሉ፡፡
➣ ጅራፍ
በደብረ ታቦር በዓል በትውፊታዊ መልኩ የሚታየው ምስጢር፤ በኢየሩሳሌም ስለሚሆነው የጌታችን ምስጢራዊ ሞቱ ነው፡፡ ጅራፍ መገመድ(መጥለፍ) እና ጅራፍ ማጮኽ ሁለት ዓይነት ምስጢር የያዘ ትውፊታዊ ተግባር ነው ...
1ኛ... ግርፋቱንና ሞቱን እናስብበታለን፡፡
2ኛ.... አንድም ደግሞ ድምፁን ስንሰማ የባሕርይ አባቱን የአብን ምስክርነት ቃል እንደ ነጎድጓድ ድምፅ ያስታውሰናል፡፡
➣ችቦ
ችቦ የጌታችንን ብርሃነ መለኮት መገለጥ የሚያመለክት ነው፡፡ በምሽት ለምን ይበራል ቢሉ በብርሃኑ ድምቀት የቀኑን መምሸት ያልተረዱ እረኞች በሜዳ ቀርተዋልና ወላጆች ከመንደር ችቦ ለኩሰው ልጆቻቸውን ፍለጋ ሔደዋልና ታሪኩን እያዘከርን በዓሉት እናከብራለን፡፡ አንድም ደግሞ አንድ ምእመን ለሌላው ምእመን መካሪ አስተማሪ መሆኑን መከራ እየተቀበለም አርአያ አንድም ምሳሌ ብርሃን መሆኑን አንድም በሃይማኖትም አርአያ ምሳሌ ይሆንላቸዋል፡፡ ችቦውም በ12 ምሽት ይበራል ብርሃኑ የተገለጠው በዚችው ዕለት ነውና ፡፡
➣ ሙልሙል
በዚህች እለት በችቦ ብርሃን ልጆቻቸውን ፍለጋ የወጡ ወላጆች ዳቦ ጋግረው ይዘውላቸው ወጥተዋል፡፡ ስጦታው ቤተሰባዊነትን ፍቅርንና መተሳሰብን መግለጫ ነው፡፡ ወደ ቤታችን * ቡሄ * እያሉ ለሚመጡ አዳጊዎችም ዘምረው እንዳበቁ የሚሰጥ “ሙልሙል” ዳቦ አለ፡፡ ይህን ማድረጉ ትውፊታዊ ብቻ አይደለም እንደ መጽሐፈ ቅዱስ ሕፃናቱ የደቀመዛሙርት ምሳሌ ናቸው፡፡ መዝሙራቸው ደግሞ ሐዋርያት “የምሥራች” ይዘው የመምጣታቸው ምሳሌ ነው፡፡ ሐዋርያት በገቡበት አገር አስተምረው አጥምቀው የጸጋ ልጅነትን አሰጥተው በረከት አድለው እንደሚሔዱ ሁሉ ልጆችም ዘምረው አመስግነው መርቀው ይሄዳሉና የዚህ ምሳሌ ነው።
ስብሐት ለእግዚአብሔር !
BY + ቅዱስ እስጢፋኖስ | 𝚂𝚝 𝚂𝚝𝚎𝚙𝚑𝚎𝚗 +
Share with your friend now:
tgoop.com/estifanos171/1564