Telegram Web
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
የዕጩ ዋና ጸሐፊ ዋሲሁን ተስፋዬ መልዕክት

“ሰላም ጤና ይስጥልኝ የተከበራችሁ የኢዜማ አባላትና ደጋፊዎች!
ዋሲሁን ተስፋዬ ነኝ፡፡

ኢዜማ በዚህ ወር መጨረሻ በሚያከናውነው ኹለተኛ መደበኛ ጉባኤ ለዋና ጸሐፊነት ለመወዳደር በዕጩነት ቀርቤያለሁ፡፡
እንደሚታወቀው ላለፉት ኹለት ሳምንታት ኢዜማን በልኩ በሚል መሪ ቃል የምረጡኝ ቅስቀሳ እያከናወንሁ ነው፡፡

የኢዜማ ልክ የዳበረ ተቋማዊ ባሕልን መገንባት ነው፡፡ ፓርቲያችን ጠንካራ የሥራ ባሕል ገንብቶ ግብ ተኮር የድርጅት መዋቅር እንዲኖረው ድርጅታዊ ዲሲፕሊን ያስፈልገዋል፡፡

ድርጅታችን ኹንተናዊ ተግባራቱን በጠንካራ አመራር እንዲያከናውን ያለኝን ልምድ ከስልታዊ ዕቅድ ጋር በማቀናጀት በሳል አመራር ለመስጠት ተዘጋጅቻለሁ፡፡

ኢዜማን በልኩ ብለን የተሰባሰብነውን አመራሮች ማለትም ዶ/ር ሙሉዓለምን ተገኘወርቅ ለሊቀመንበርነት፣ አቶ ማዕረጉ ግርማን ለምክትል ሊቀመንበርነት፣ እኔ አቶ ዋሲሁን ተስፋዬን ለዋና ጸሐፊነት እንዲሁም ወይዘሮ አሰፉ ተረፈን ለፋይናንስ/ትሬዠረር ኃላፊነት እንድትመርጡ ጥሪ አቀርባለሁ፡፡

#ኢዜማን በልኩ! ትጋት፣ ዲሲፕሊን፣ ልኅቀት”
#ኢዜማን_እንደገና
#የምረጡኝ_ቅስቀሳ

ኢዜማ እንደ ፓርቲ ኢትዮጵያ እንደ ሀገር እውነተኛ፣ ተራማጅ፣ ሀገር ወዳድ፣ የበቃ፣ የመምራት አቅም እና ፍላጎት ያለው ወጣት አመራሮችን የምትፈልግበት ወቅት ነው። ጠንካራ የፖለቲካ ድርጅት ለመድብለ ፓርቲ ስርዓትና ለዲሞክራሲ ግንባታ ወሳኛ ሚና እንዳለው እሙን ነው። ሕዝባችን እንደ ሕዝብ ከዘረኝነት፣ ከጎሰኝነት: ከኑሮ ውድነት፣ ከጦርነት፣ ከመልካም አስተዳደር ችግር፣ ከፍትህ ዕጦት፣ ከሙስና፣ ከስደት፣ ከረሀብ እና ፍራቻ ነፃ የሚያወጣው የተደራጀ ኃይል የሚፈልግበት ወቅት ነው።

ኢዜማን የዜጎችን ጥያቄ መመለስች የሚችል ለሕዝብ የወገነ ሕዝባዊ ድረጅት በማድረግ የቀደመ ገናናነቱ ሊመልስ በሚችል መልኩ በየትኛውም ዓለም የሚገኙ ኢትዮጵያዊያን ምሁራን በሀገራቸው ጉዳይ ላይ በሚስተዋሉ ችግሮች ላይ በማሰባሰብ እና በማደራጀት ለችግሮቻችን መፍትሔ የሚሆኑ ሀሳብ እንዲያቀርቡ እና በሀገራቸው ጉዳይ እንዲሳተፉ በሚያስችል መልኩ የመሪነቱን ድርሻ የሚወጣ ድርጅት እንዲሆን ማድረግ ያሰፈልጋል።

ከላይ የተጠቀሱትን ጉዳዮች ዕውን ለማድረግ ፓርቲያችን ኢዜማን እንደገና በሁሉም መስክ ማጠናከር እና ማደራጀት ተገቢ ነው። የፖለቲካ ምህዳሩ የሰጠንን አጋጣሚ ሁሉ በመጠቀም የፓርቲያችን ጥንካሬና የሕዝባችን እና የሀገራችን ህልውና ሊያረጋግጥ በሚችል መልኩ መጠቀም ተገቢ ነው ብለን እናምናለን።

ኢዜማን በሕዝብ ዘንድ ታማኝ፣ ተመራጭ፣ እና ተቀዳሚ ለማድረግ የሚያስችሉ ስራዎችን መስራት አስፈላጊ ነው። በሕዝብ ዘንድ ያለን ተቀባይነት እንዲላላ ያደረገው የምንከተለው ርዕዮተዓለም ወይም ይዘናቸው የቀረብናቸው አማራጭ ሀሳቦቻችን ሳይሆኑ ሀሳባችንን በሕዝቡ ዘንድ ሰርፀው እንዲገቡ የሚያስችሉ ስራዎች ባለመሰራታቸው ነው። ለዚህ ደግሞ ዋናውን ድርሻ የሚወጣው የሕዝብ ግንኙነት ክፍል ነው። የሕዝብ ግንኙነት ክፍል ደካማ መሆን ፓርቲውን ዋጋ አስከፍሎታል ብለን እናምናለን ። ከዚህም በተጨማሪ ፓርቲው በሊቀመንበርነት የመሩ አካለት የፓርቲውን መዋቅሮች የማጠናከሪያ ስራ ባለመስራታቸው ነው የሚል እምነት አለን። ብንመረጥ ኢዜማ ትውልድ ተሻጋሪ ፓርቲ እንዲሆን ከመሪ ክንፍ እና ሌሎች አደረጃጀቶች ጋር በመተባበር የሚከተሉትን ተግባራት እንሰራለን፡-

1. ድርጅታችን የራሱ ዋና ፅዕፈት ቤት ሕንፃ እንዲኖረው የሚያስችሉ መሠረታዊ ስራዎችን እናስጀምራለን።

2. ከሕዝብ የሚነሱ የልማት እና የዲሞክራሲ ጥያቄዎች ለመመለስ በሚያስችል መልኩ በሰው ኃይል፣ በፋይናንንስ እና በቴክኖሎጂ የተደራጅ የፖሊሲ ጥናት ክፍል እንዲኖረን እንሰራለን።

3. ከሌሎች የፖለቲካ ድርጅቶች/በአፍሪካና በሌሎች አሀጉራት ከሚገኙ/ የልማድ ልውውጥ መድረኮችን እናዘጋጃለን

4. የፓርቲውን መዋቅሮች በቴክኖሎጂ የማደራጀት ስራ እንሰራለን።

5. የአባላትን ቁጥር ለማሳደግ በበይነ መረብ የታገዘ የአባላት ምዝገባ ማድረግ የሚያስችል ስራዎችን እንሰራለን

6. የድርጅቱ የሎጅስቲክ እና በምርጫ ወቅት ስራዎችን ለማቀላጠፍ የሚያግዙ ተሽከርካሪዎች እንዲኖሩት የሚያስችሉ ሥራዎችን እንሰራለን።

7. የዜግነት ፖለቲካ እንዲያብብ ከሕዝባችን ጋር በቅርበት እንሰራለን።

8. ወቅታዊ ጎዳዮችን የሀገርን ህልውና በማይጎዳ መልኩ ለፓርቲያችን ጥቅም እንጠቀማለን።

9. የኢዜማ የፓርቲ መዋቅር ባልተዘረጋባቸው አካባቢዎች የማደራጀት ስራዎችን እንሰራለን።

10. የፓርቲውን የገንዘብ አቅም ለማሳደግ የተለያዩ ስትራቴጂዎችን ነድፈን እንቀሳቀሳለን ። የሀብት አሰባሳቢ መምሪያ በማደራጀት ራሱን የቻለ የሥራ ክፍል እንዘረጋለን። የአባላት መዋጮ በቴክኖሎጂ እንዲደገፍ እናረጋለን።

11. ለጋራ አላማ እና ግብ የቡድን ስራ/team work/ እንዲጎለብት እና በድርጅት ውስጥ ባህል እንዲሆን የሚያስችሉ ስራዎችን እንሰራለን።

12. የምርጫ ወረዳዎች የመስተባበሪያ ቢሮዎች የፈርኒቸር እና የኪራይ ክፍያዎች ችግር በሚፈታበት አግባብ እንሰራለን

13. በኢትዮጵያ 12ክልሎች፣ 70ዞኖች እና 2ከተማ መስተዳድሮች የሚገኙ ሲሆን በሁሉም ከባቢዎች አደረጃጀቶችን እንፈጥራለን።

ንቁ ዜጋ ምቹ ሀገር!
ኢዜማን ኢንደገና!

ጌታቸው ጳውሎስን በሊቀመንበርነት
ኤልሳቤት ሉቃስን በምክትል ሊቀመንበርነት ይምረጡ
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
የዕጩ የፋይናንስ/ትሬዠረር አሰፉ ተረፈ መልዕክት

“ሰላም ጤና ይስጥልኝ የተከበራችሁ የኢዜማ አባላትና ደጋፊዎች!
አሰፉ ተረፈ ነኝ፡፡

ኢዜማ በዚህ ወር መጨረሻ በሚያከናውነው ኹለተኛ መደበኛ ጉባኤ ለፋይናንስ/ትሬዠረር ኃላፊነት ለመወዳደር በዕጩነት ቀርቤያለሁ፡፡

እንደሚታወቀው ላለፉት ኹለት ሳምንታት ኢዜማን በልኩ በሚል መሪ ቃል የምረጡኝ ቅስቀሳ እያከናወንሁ ነው፡፡

ኢዜማ ከሌሎች ፓርቲዎች በተለየ መልኩ ራሱን የቻለ የሴቶች መምሪያ አለው፡፡ እኔም ፓርቲያችን ለሴቶች በሚሰጠው ልዩ ትኩረት መሠረት ንቁ ተሳትፎ ሳደርግ ቆይቻለሁ፡፡

የኢዜማ ልክ ንቁ የሴቶች ተሳትፎ ነው፡፡ ድርጅታችን አቅም ያላቸውን ሴቶች በመመልመል ብቁ የፖለቲካ አመራር እንዲኾኑ በትጋት መሥራት እንዳለበት አምናለሁ፡፡

ኢዜማ ያለውን የሰው፣ የገንዘብ፣ የቁሳቁስና የቴክኖሎጂ ሀብት በአግባቡ እንዲጠቀም እና የፋይናንስ አቅሙ እንዲጠናከር ቁርጠኛ መሪ ለመኾን ተዘጋጅቻለሁ፡፡

ኢዜማን በልኩ ብለን የተሰባሰብነውን አመራሮች ማለትም ዶ/ር ሙሉዓለም ተገኘወርቅን ለሊቀመንበርነት፣ አቶ ማዕረጉ ግርማን ለምክትል ሊቀመንበርነት፣ አቶ ዋሲሁን ተስፋዬን ለዋና ጸሐፊነት እንዲሁም እኔ ወ/ሮ አሰፉ ተረፈን ለፋይናንስ/ትሬዠረር ኃላፊነት እንድትመርጡ ጥሪ አቀርባለሁ፡፡

#ኢዜማን በልኩ! ትጋት፣ ዲሲፕሊን፣ ልኅቀት”
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
የዕጩ ሊቀመንበር ዶ/ር ሙሉዓለም ተገኘወርቅ መልዕክት

“ሰላም ጤና ይስጥልኝ የተከበራችሁ የኢዜማ አባላትና ደጋፊዎች!
ዶ/ር ሙሉዓለም ተገኘወርቅ ነኝ፡፡

ኢዜማ በዚህ ወር መጨረሻ በሚያከናውነው ኹለተኛ መደበኛ ጉባኤ ለሊቀመንበርነት ለመወዳደር በዕጩነት ቀርቤያለሁ። እንደሚታወቀው ላለፉት ኹለት ሳምንታት ኢዜማን በልኩ በሚል መሪ ቃል የምረጡኝ ቅስቀሳ እያከናወንሁ ነው፡፡

ፓርቲያችን ኢዜማ ራዕዩን መሸከም የሚችል ጥንካሬ ላይ እንዲደርስ በልኩ መንቀሳቀስ እንዳለበት አምናለሁ፡፡

የኢዜማ ልክ ትጋት፣ ዲሲፕሊን እና ልኅቀት ነው፡፡ የኢዜማ ልክ ዘመኑን የዋጀ እና ለተለዋዋጭ ሁኔታዎች ምላሽ መስጠት የሚችል ኾኖ መገኘት ነው፡፡

ኢዜማ በልኩ እንዲኾን ከዚህ ቀደም ያጋጠሙትን ተግዳሮቶችና ድርጅታዊ ድክመቶችን በመመርመር ስትራቴጂያዊ አመራር ለመስጠት ተዘጋጅቻለሁ፡፡

ኢዜማን በልኩ ብለን የተሰባሰብነውን አመራሮች ማለትም እኔ ዶ/ር ሙሉዓለም ተገኘወርቅን ለሊቀመንበርነት፣ አቶ ማዕረጉ ግርማን ለምክትል ሊቀመንበርነት፣ አቶ ዋሲሁን ተስፋዬን ለዋና ጸሐፊነት እንዲሁም ወይዘሮ አሰፉ ተረፈን ለፋይናንስ/ትሬዠረር ኃላፊነት እንድትመርጡ ጥሪ አቀርባለሁ፡፡

#ኢዜማን በልኩ! ትጋት፣ ዲሲፕሊን፣ ልኅቀት”
ኢዜማን እንደገና!

የኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዊ ፍትህ ፓርቲ-ኢዜማ ከተመሠረተበት ግንቦት 2011 ዓ.ም ጀምሮ በተለያየ ሀገራዊ እና ፖለቲካዊ ጉዳዮች በፅንሰ ሀሳብ መሪነት የሀገራችን ፖለቲካ እያዘመነ ይገኛል። ፓርቲያችን ከአመሠራረቱ ጀምሮ ከምርጫ ክልሎች ወደ ላይ የተደራጀ በመሆኑ ሁላችንም የምንኮራበትና ዜጎች ተስፋ ያደረጉበት ስብስብ መሆኑ ይታወቃል። ኢዜማ አዲስ የአደረጃጀት ቅርፅ ይዞ በመምጣት በመንግስት እና በፓርቲ ደረጃ የነበረውን ቁርኝት በመለያየት የፖለቲካ መሪ ክንፍና የፓርቲ ሊቀ መንበር ዘርፍ ለየብቻ የሚሰሩበትን አሰራር በመተግበር ለብዙ የፖለቲካ ድርጅቶች አርዓያ መሆን ችሏል።

ፓርቲያችን ሰኔ 28-29/2017 ዓ.ም በሚያደርገው 2ኛው መደበኛ ጠቅላላ ጉባዔ ለማድረግ ዝግጅቱን አጠናቅቋል። በዚህ ከመላው ኢትዮጵያ በሚወከለው ጉባዔ ላይ የፓርቲውን ትላልቅ ውሳኔዎችን እንደሚያሳልፍ ይታወቃል። በዚህ የጉባዔ ሂደት የሚያከናውነው የፓርቲው የከፍተኛ አመራሮች ምርጫ አንዱ ነው። በዚህ የጉባዔ ተመራጮች ላይ በአስመራጭ ኮሚቴው ተመልምለው ለውድድር የቀረቡ ዕጩዎች ለፓርቲያችን አባላትና ለጉባዔ ተሳታፊዎች ራሳቸውን እና የሚሰሩትን ስራ አስተዋውቀው ወደ ምርጫ ሂደቱ ይገባሉ።

እኛ 'ኢዜማን እንደገና!' በሚል መሪ ቃል የተሰባሰብን ዕጩ ተወዳዳሪዎች ለፓርቲያችን ዘመን ተሻጋሪነት ያስፈልጋሉ የሚሉ ሀሳቦችን ይዘን ቀርበናል።

ከላይ የተጠቀሱትን ሀሳቦች: ጥያቄዎችና ዕጩ አመራሮቻችን በአጭሩ የሚገልፅልን የጋራ የቃል ኪዳን ሰነድ በማስፈለጉ ለተከበሩ የኢዜማ አባላትና የጠቅላላ ጉባዔ ተሳታፊዎች ይህንን ሰነድ አቅርበናል።

https://drive.google.com/file/d/1wscQokq5GqXMs6ORl5XiXsPUWuFzDdRn/view?usp=drivesdk

ኢዜማን እንደገና!

ጌታቸው ጳውሎስ - ዕጩ ሊቀመንበር
ኤልሳቤጥ ሉቃስ- ዕጩ ምክትል ሊቀመንበር
ዶ/ር ካሳሁን ደለነ- ዕጩ ዋና ፀሐፊ
የኢዜማ እንደገና ማሻሻያዎች

ኢዜማን እንደገና ለማሻሻል በጠቅላላ ጉባዔው ይሁንታን ካገኘንና ፓርቲያችንን የምናሻሽልበት አጋጣሚው ከተፈጠረ ምን ዓይነት ማሻሻያዎችን ለማድረግ አስበናል? የምናሻሽልበት ምክንያቶቻችን ላይ ከተስማማን ለምን እንደምናሻሽል ከተግባባን በቀጣይ ደግሞ ዋና ዋና ማሻሻያዎቻችን ምንድን ናቸው?

ከምርጫ ክልል ጀምሮ መሠረቱን ያፀና ትልቅ ሀገር አቀፍ የፖለቲካ ፓርቲ በየጊዜው ራሱን እያሻሻለ እስካልሄደ ድርስ ከግብ መድረስ አይቻለውም። ይህን ተከትሎ እኛ በመረጮቻችን በጎ ፍቃድ የፓርቲ ማሻሻያ ስራ እንድንሰራ አደራው ከተሰጠን በቀጣይ

1, ፖለቲካዊ ማሻሻያዎች
2, ድርጅታዊ (መዋቅራዊ) ማሻሻያዎች
3, ተቋማዊ ማሻሻያዎችን እንተገብራለን።

በሦስቱ ዓበይት የማሻሻያ ሀሳቦቻችን ዝርዝር ትንታኔዎችን የምንሰጥ ሲሆን ለአንባቢ በሚጠቅም መልኩ በአጭሩ ለማብራራት እንወዳለን።

1, ፖለቲካዊ ማሻሻያዎቻችን

ኢዜማ በፖለቲካ መስመር ጥራትና ቁርጠኝነት በሰፊው ህዝብ ዘንድ የታመነበት ፓርቲ መሆኑ ይታወቃል። ይህ የጠራ የፖለቲካ አረዳድ እና አቅጣጫ ላይ የተመሰረተ የተሀድሶ አተገባበር ይከተላል። በጥንቃቄ የሚመራ የፖለቲካ ተሀድሶ ዋና መዳረሻው የዜግነት ፖለቲካ እና የማህበራዊ ፍትህ ማስፈን ሲሆን በሀገራዊ ሉዓላዊነት ላይና በዜጎች ደህንነት ላይ የተመረኮዘ ይሆናል። ኢዜማ በተሃድሶ ፕሮግራሙ የውስጠ ፓርቲ ፍትሃዊነትን: ስብጥርንና ዝግጁነትን ከግምት ውስጥ ባስገባ መልኩ የአርቆ አሳቢዎች ቡድን (Think Tank) ቡድኖች ጋር በትብብር የሚሰራ: የማህበራዊ ፍትህ ተደራሽነትን በገለልተኝነት የሚከታተል አካል እና የኢትዮጵያን ሰላማዊ የውጭ ግንኙነቶችን የሚደግፍ የተልዕኮ ማዕቀፍ ያስፈልገዋል። ይህን ማድረጉ በቀጣይ ጊዜውን ለሚመጥን የፖሊሲ ዝግጅት ግብዓት ይሆነናል። ኢዜማ ያሉትን ፖሊሲዎችን ለአባላት ከማሳወቁ በፊት ከአሰላሳይ ቡድኖች ጋር በመምከር ለሀገር ያለውን ጠቀሜታ በዝርዝር ለየመዋቅሮቾ እንዲያደርስ እናደርጋለን።

ኢዜማን እንደገና ለማደስ የተሃድሶ ስትራቴጂ ቀርፀን ፓርቲው የነበሩበትን ክፍተቶችን በማስተካከል ለአዲሱ የፖለቲካ ትውልድ መዳራሻ እናደርገዋለን። የጠቅላላ ጉባዔዎች ውሳኔዎቻችን እንደገና በመገምገም ከጊዜውና ከወቅቱ ጋር የሚሄዱትንና ከእኛ የሚጠበቁትን ውሳኔዎቻችን እናስቀጥላለን። በህዝብ ዘንድ ቅቡልነት ያሳጡንን ውሳኔዎች ካገኘን የህዝብን ድምፅ በማክበር ውሳኔዎቻችን ዳግም እናጤናቸዋለን።

ፓርቲያችን የመሃል ከተማ ፓርቲ ብቻ እንዳይሆን ወደ ተለያዩ የኢትዮጵያ አካባቢዎች በመቅረብ ሰላማዊ ስልጡን ፖለቲካን እናራምዳለን። አባላት ብቻ ሳይሆኑ ደጋፊዎቻችንም በቀጣይ ስትራቴጂካዊ ዕቅዶቻችን ላይ አሻራቸውን እንዲያኖሩ ሁኔታዎችን እናመቻቻለን።

በሀገራችን ከሚገኙ ከተለያዩ አሰላሳይ ቡድኖች ጋር በመተባበር ኢዜማን ከሚገዳደሩ የዘርና የጎሳ ፖለቲካ ትርክቶች የሚያስወጡንን አሰላሳዮችን በማድመጥ ለሀገራችን ዘላቂ ሰላምና ዴሞክራሲ እንተጋለን።

2, ድርጅታዊ ( መዋቅራዊ) ማሻሻያዎች

የፓርቲያችን ህልውና የሚፀናው ባለን መዋቅራዊ አደረጃጀቶች እንደሆኑ ይታወቃል። የኢዜማ አደረጃጀት ከምርጫ ክልል የሚጀምር እና በተያዩ ደጋፊ: አስተባባሪና አጋዥ መዋቅሮች መደገፋቸው ፓርቲውን የሚያጠነክረው አካሄድ ነው ብለን እናምናለን። ለዚህ የሥራ ዘርፍ ሃላፊነት የሚታጨው አመራር ግን በብስአኮ የሚሾም ከሚሆን በፓርቲያችን የጠቅላላ ጉባዔ ተመራጭ ሆኖ ተወዳድሮ እንዲመረጥ ምክረ ሀሳብ እናቀርባለን። የድርጅት ጉዳይ ዘርፍን የሚመራው አካል የጉባዔ ተመራጭ ሆኖ በምርጫ እንዲሰየም እንጠይቃለን። ይህን የፓርቲያችን የጀርባ አጥንት የሚመራው አካል እንደሌሎች የስራ ክፍሎች በግለሰቦች በጎ ፍቃድ ላይ መወሰኑን አግባብነት የሌለው እንደሆነ እንረዳለን።

ፓርቲያችን በሚያንቀሳቅሳቸው የመዋቅር አደረጃጀቶች በሙሉ የምንስማማበት ሲሆን በተጨማሪነት የሚርጫ ክልሎችንና ለአሰራር እንዲመች ተብለው የተደራጁ የዞን ማስተባበሪያዎችን በቅርበት የሚያግዝ በክልል እና በከተማ አስተዳደሮች የሚንቀሳቀስ ተጨማሪ አጋዥ ጽ/ቤቶችን በመክፈት በቅርበት የምናግዝበት መንገድ እንፈጥራለን። ይህን በማድረግ በቀጣይ ለሚከናወነው ሀገር አቀፍና ክልላዊ ምርጫ ብቡ አጋዥ መዋቅር እናደራጃለን።

የአዳዲስ አባላት ምልመላና ጥሪ ግብዣን በቋሚነት በየመንፈቅ ዓመቱ በየመዋቅሩ በዘመቻ መልክ እንዲሰራ እናደርጋለን። ጠቅላላ ጉባዔው ለሚቀጥሉት ጊዜያት በትጋት እንድናገለግለው ይሁንታ ከሰጠን በአባልነት መስፈርቶች ላይ ማሻሻያ እናደርጋለን። ለአብነት ያኽል ዕድሜያቸው ከ18 ዓመት በላይ ለሆኑ ተማሪዎች ካለባቸው የፋይናንስ እጥረት በመነሳት በየምርጫ ክልላቸው ከሌሎች አባላት በግማሽ ያነሰ የአባልነት መዋጮ እንዲከፍሉ በማድረግ የወጣቶችን ተሳትፎ እናበረታታለን። ይህ ኢዜማ በአዲሱ ትውልድ ላይ ለሚሰራው የፖለቲካ ስራ አመቺ ሁኔታዎችን ከመፍጠር አኳያ እንተገብረዋለን።

ዓለም ከደረሰበት የቴክኖሎጂ ለውጥ አብዛኛው የሰው ልጅ ህልውና በዲጂታል ስርዓት የታገዘ በመሆኑ እኛ ከተመረጥን 'ዲጂታል ኢዜማ' የሚል ፕሮግራም በመቅረፅ ሰፊዎን መራጭ ህዝብ በስነ ዜጋ: በምርጫ: በዴሞክራሲ: በመብቶችና ሌሎች የፖለቲካ ፓርቲ ስራዎች ላይ በተከታታይ የሚሰራ ሀገር አቀፍ የዲጂታል ንቅናቄ በፓርቲ ደረጃ እንተገብራለን። የፓርቲው ድረ ገፅ በቀላሉ ከማሰራት በተጨማሪም አባላት በቀጥታ ስለፓርቲያቸው ሙሉ መረጃ የሚያገኙበትን መንገድ እንፈጥራለን። የሞባይል መተግበሪያዎችን በማሰራት የአባልነት ጋር ተያይዞ የሚሰሩ ማናቸውም ነገሮች በዲጂታል ኢዜማ ክፍል እንዲሰራ እናስደርጋለን። በፓርቲያችን ዋና ጽ/ቤት የመረጃ ማከማቻ ቋት Cloud Archive ወደ ስራ በማስገባት ከወረቀት ንክኪ ነፃ የሆነ አገልግሎት እንዲሰጥ እናደርጋለን።

3, ተቋማዊ ማሻሻያዎች

ፓርቲያችን እስካሁን የመጣበትን ተቋማዊ ቅርፅ የበለጠ ጉልህና የሚታይ ለማድረግ የተወሰኑ ማሻሻያዎችን ማድረግ ተገቢ ነው ብለን እናምናለን። ለዚህ እንዲረዳ ተቋሙ በዋና ቢሮ ያሉትን የመምሪያ እና የስራ ክፍሎችን አዲስ በምናዋቅረው አጋዥ የክልሎችና የከተማ አስተዳድሮች ጽ/ቤቶች እናስፋፋለን። እነዚህ የጎንዮሽ ትዪዩ መምሪያዎች ወደ አጋዥ ቅርንጫፍ መዋቅሮቻችን የሚተባበሩበትንና በትስስር የሚሰሩበትን መመሪያዎችን የፓርቲያችን የህገ ደንብ ተርጓሚና አስፈፃሚ ኮሚቴ ካፀደቀልን ወደ ተግባር እንገባለን።

የሚደራጁ ጽ/ቤቶች ተቋሚ ይዘታቸውን ሳይለቁ ፈጣን ተደራሽ የመረጃ መለዋወጫ መስመር በመዘርጋት በየመዋቅሩ የሚደረጉ ፖለቲካዊ ተሳትፎአችን እናጠናክራል። በየደረጃው ያሉ መመሪያዎች: ደንቦና አሠራሮችን እጅግ ፈጣንና ለስራ ምቹ በሚሆኑ መልኩ ማሻሻያ እናስደርግባቸዋለን።

ኢዜማ እስከዛሬ ድረስ የፓርቲውን ፋይናንስ ስራ ከሌሎች አቻ ፓርቲዎች በተሻለ ሁኔታ እየሰራ መሆኑ ይታወቃል። ነገር ግን የኢዜማ የፋይናንስና ንብረት አስተዳደር (Treasurer) በሁለት የተከፈለ ስራ ሲኖረው የፋይናንስ እና የንብረት አስተዳደር ክፍሎች ብቻ ናቸው። ይህ በሁለት ዘርፎች የተከፈለውን አሰራር በነበረበት በባለሙያ ብቻ እንዲመራ በማድረግ መምሪያውን ከፖለቲካ ወገንተኝነት በፀዳ መልኩ የባለሙያ ስራ እናደርገዋለን። ከዚህ ጋር በተቀራረበ ሁኔታ አብሮት የሚሰራ 'የሀብት አሰባሳቢ መምሪያ' ራሱን ችሎ እንዲደራጅና እንደሌሎች የሥራ ክፍሎች የሙሉ ጊዜ ስራው የኢዜማን ገቢ የማሳደግና ሀብት የማሰባሰብ ስራን የሚሰራ ራሱን የቻለ መምሪያ እንዲኖር እንሰራለን።
የፋይናንስና ንብረት አስተዳደር ሃላፊን ከፖለቲካ አመራርነት ይልቅ በብቁ ባለሙያዎች እንዲመሩት እናስደርጋለን። የፋይናንስ ሃላፊውም ከጉባዔ ተመራጭነታቸው ይልቅ በሙያ ታምኖባቸው በግልፅ የማስታወቅያ የሚቀጠሩ የዘርፉ ሀላፊ እንዲኖሩት የጠቅላላ ጉባዔውን እንጠይቃለን።

ኢዜማን እንደገና!

ጌታቸው ጳውሎስ-ዕጩ ሊቀመንበር
ኤልሳቤጥ ሉቃስ-ዕጩ ምክትል ሊቀመንበር
ዶ/ር ካሣሁን ደለነ-ዕጩ ዋና ፀሐፊ

የቃል ኪዳን ሰነዳችን ሙሉውን ለማንበብ ከታች በተቀመጠው የቴሌግራም መስፈንጠሪያ በመግባት ማገኘት ይችላሉ።

https://www.tgoop.com/ethzema/4751

https://drive.google.com/file/d/1wscQokq5GqXMs6ORl5XiXsPUWuFzDdRn/view?usp=drivesdk
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
#ኢዜማ ን በልኩ ከተሠጡ የድጋፍ ድምፆች በጥቂቱ ይመልከቱ።
ሐ/ ደረጀውን የጠበቀ የጎንዮሽ ትስስር ከተለያዩ መምሪያዎች ጋር እፈጥራለሁ። ለአብነት ያኽል የህዝብ ግንኙነት መምሪያ: የፋይናንስና ንብረት አስተዳደር መምሪያ: የወጣቶች ሴቶችና አካል ጉዳተኞች መምሪያ: የሙያና የሠራተኛ ማህበራት መምሪያዎችና ሌሎች መምሪያዎች ጋር የጠበቀ የሥራ ግንኙነት በማድረግ ለትጋት እታትራለሁ

መ/ በዋና ቢሯችን የዲጂታል መረጃ አርካይቭ በማደራጀት ከዚህ በኋላ ያሉ ማንኛውም የኢዜማ ስራዎችን በዲጂታል መልኩ እንዲቀመጥና በተፈለገ ሰዓት አገልግሎት ላይ እንዲውል አደርጋለሁ።

ሠ/ በየሩብ ዓመቱ የጽ/ቤት ስራዎችን ምዘና ለብስአኮ እና ለአባላት ይፋ በማድረግ ግልፀኝነትን አሰፍናለው።

ረ/ በክልል ደረጃ ለሚደራጁ አጋዥ ጽ/ቤቶች የተሟላ ቁሳቁስ እንዲኖር ከረድዔት ድርጅቶችን ረጂ ግለሰቦች ጋር በመነጋገር ሁሉም የኢዜማ መዋቅር አጋዥ ጽ/ቤቶች የቢሮ ቁሳቁስ እንዲሟላ እሰራለሁ።

ሰ/ አዲስ ለምናዋቅራቸው የክልል አጋዥ ጽ/ቤቶች ድጋፍ የሚውሉ 'መቶ ብር ለፍትህ!' የሚል ዘመቻ በማስተባበር በየአካባቢው ከሚገኙ አባላት እና ደጋፊዎች ጋር የገቢ ማሰባሰቢያ በማድረግ ጽ/ቤቶቹ እንዲጠናከሩ እሰራለሁ!

ሸ/ የፓርቲያችን የሆሉም ጽ/ቤት ፀሐፊዎች በየ4 ወሩ በኢዜማ አካዳሚ የአቅም ማጎልበቻ ስልጠና እንዲወስዱና ተመሳሳይ ግንዛቤ እንዲጨብጡ እሰራለሁ።

የተከበራችሁ የኢዜማ 2ኛ መደበኛ ጉባዔ ተሳታፊዎች

ከላይ በመግቢያዬ ለመጥቀስ እንደሞከርኩት ይህ የእኔ ህልም ብቻ ሳይሆን የሁሉም ኢዜማዊ የጋራ ራዕይ ነውና ይህን ዕቅዳችን ለመተግበርና አተገባበሩን ለመከታተል በጉባዔው ዕለት በሚደረገው የዋና ፀሐፊነት ቦታ ላይ እንድትመርጡኝ ስል በታላቅ ትህትና እጠይቃችኋለሁ!

ኢዜማን እንደገና!

ዶ/ር ካሣሁን ደለነ
ዕጩ ዋና ፀሐፊ

የቃል ኪዳን ሰነዱን ለማገኘት

https://www.tgoop.com/ethzema/4751

https://drive.google.com/file/d/1wscQokq5GqXMs6ORl5XiXsPUWuFzDdRn/view?usp=drivesdk
2025/07/10 06:23:27
Back to Top
HTML Embed Code: