tgoop.com/fikrhn/1110
Last Update:
🚶♂🚶♂ ❤️❤️ 🚶♀🚶♀
''የተሻለ ነገር ያለው ወደ ፊት እንጂ ወደ ኋላ አይደለም።''
ከተለያየን ከስድስት ወር በኋላ ተገናኝተን ስናወራ ነበር ኢሄን ያለችኝ፡፡ ከምትሳሳለት አለም ድንገት እንደመነጠል ጽልመት የሚያለብስ ነገር የለም የተጣጣምንባቸው ነገሮች ብዙ ቢሆኑም።ትንንሽ ኩርፍያዎቻችን አድገው ነበር ለመለያየታችን ምክንያት የሆኑት። የፍቅርን እንቅፋት በጊዜው ባለማንሳታችን የተራራ ያህል ክምር ሆኖ አላሻግር አለን...
ማምሻውን ጭርታ በሚበዛበት ጎዳና ላይ እየተጓዝን ሳለ በወሬያችን መሃል....
ጥሩ ሁነሻል።ብዙ የተለየ ነገር ስላየውብሽ ደስ ብሎኛል።አዲሱ አለምሽን በደንብ ተጠቅመሽበታል ማለት ነው..... በአሁኑም ቢሆን ይበልጥ ሳቢነትሽ እንደቀጠለ ነው...
እጆቿን ደረቷ እንዳቀፈቻቸው አይኖቿን ፊት ከምታይበት ጎዳና ወደ እኔ አዞረቻቸውና.....በሃዘኔታ አይታኝ አንተም ተለውጠሃል..... አምሮብሃል አለች ፊቷን ወደ ተቃራኒው እያዞረች:(ህመሜ ያመማት ስቃዬ የገባት ትመስላለች)
"እሱ እንኳን ውሸት ነው....ድሮነቴን ዛሬዬ እንደነጠቀኝ አውቃለው፡ የምወዳቸውን ነገሮች በግዴለሽነቴ ጠልቻቸዋለው።የሚስበኝና የምፈልገውን እንኳን መለየት ተስኖኛል ለምን እንደሆነ ግን አላውቅም...
ስራ ብዙም እንደማትገባ ጓደኞችህንም እንደራቅካቸው ማስጠንቀቅያ እንደተጻፈብህና ብዙ ብዙ ሰምቻለው ለምን እንደዛ ታደርጋለህ...ለምን? የምጠብቅህኮ እንደዚህ አልነበረም?....አይኖቿ እንባ አቀረሩ.........(ልቤን ፍርሃትና እዝነቷ ወጠሩት....ተመለከትኳት)
"አለመኖሩ ውስጥ ለሚኖር ሰው ነገኮ ዓውድ አልባ ነው።" እኔኮ ካንቺ ነፍስ ጋር አብሬ ጠፍቻለው።ስንለያይ ነበር የተከተልኩሽ... የህወቴን ጣዕም ማጣትና ናፍቆትሽ እየበረዙት መኖር ውሏ ሲጠፋብኝ ትናንትሽና ትናንቴኮ ነው እዚህ ያደረሰኝ።አግኝቼሽ የሚመጣውን ቀን ማየት ሲያቅተኝ ተመልሼ ባለፈው ውስጥ ስሆንኮ ነው የማገኝሽ አንቺን ላለመርሳትኮ ነው ምርጫዬ ያ የሆነው...እርግጥ አዎ እኔምኮ ጥሩ ደረጃ መድረስ እፈልጋለው....የተሳካለትና ትልቅ ቦታ የሚደርስ ሰው. እንደዛ መሆንን እሻለው....
የሆነው ሆኖ
'ዛሬ ስላገኘውሽ ግን ደስ ብሎኛል።'
'እኔም እንደዛው'አለች ኪሴ ውስጥ ያለውን እጄን እያቀፈች
'እንዴት መጣሽ?'......
'ስላለፈው ላላወራህ ግን ትናንታችንን ወደ ነገ ልወስደው'
'ለመሄድ የሚሰማኝን በምን ታውቂያለሽ'
'ዘወትር ድርጊትህ ስለሚነግረኝ'
'አንቺንስ በምን ላውቅሽ እችላለው'
(ግንባሮቿ ግንባሬ ላይ ናቸው)
'የመጣሁት አንተነትህ ናፍቆኝ፤መኖር አምሮኝ እንጂ እንድዋሽህ የሚያስገድደኝ አንዳች ነገር ስለሌለ.....ከራሴ ጋር መጣላትና መወሻሸት ስለሰለቸኝ፤ከዚህ በላይ ናፍቆትህን መሸከም ስላቃተኝ ካንተ ጋር መኖርን ስለጓጓው.....ለዛ ነው የመጣሁት።
'ምንም ላደርግልሽ አልችልም.......ግን ቀሪ ዘመኔን ስንከባከብሽ ልኖር ቃሌን እሰጥሻለው......በሚንቀጠቀጡት ትንፋሾቿ መሃል በቅጽበት የሚያሳሱት ከናፍሮቿን አገኘዋቸው..........
"የማልወደውን የሆንኩት የወደድኩትን ባለመሆኔ ነው አሁን ግን የምወደውን ሆኛለው።"
"የተሻለ ነገር ያለው ወደ ፊት እንጂ ወደ ኋላ አይደለም።"
✍...... #Jo_ሊ
@fikrhn
@fikrhn
@fikrhn
BY እኔና አንቺ
Share with your friend now:
tgoop.com/fikrhn/1110