tgoop.com/fikrhn/1114
Last Update:
* #የዝምታ_መልስ *
ማጣትን ብቻ እያሰበ ስለነገ የሚጨነቅ ልብ ከዛሬ ተኳራፊ ነው።ማሰቧን አልጠላውም ግን ባላሰብኩት ስለምታስበው ታሳዝነኛለች....ላስረዳት ጊዜ ያስፈልገኛል::ወይ እሷ ልትረዳኝ ጊዜ ያስፈልጋታል።
አብርያት ስሆን አይኖቼን መክደን ስለሚቀናኝ...
እኔን ላለማየት ነው የምትጨፍነው አይደል ትላለች? ከሷ ውጪ እንደታወርኩኝና አለማየቴ ውስጥ እንደማያት ዘንግታ ........
በወሬዎቻችን መሃል ዝምታ ሲውጠኝ ከኔ ጋር ሁነህ ምንድነው የምታስበው? የእለቱ ጥያቄዋ ነው....መጠየቅ ትወዳለች
እኔኮ የማስበው እሷ ከሌለች የመኖሬን ምስቅልቅል ስሌት ነው።ዝም ስል የማስበው አጠገቤ በመሆኗ የአምላክን ድንቅነት ነው....ምን አድርጌ ይሆን የተሰጠችኝ እያልኩ የጸሎቴን መዳረሻ ምስጋና ሳደርስ ነው.....
ለሁለት ቀን ስልኬ ተበላሽቶ ነበር።አለመደወሌ ስህተት አልነበረም ለኔ።ማውራት ካልፈለግክ ለምን እንደዛ ታደርጋለህ? ትላለች። እኔ የነገሩን ምክንያታዊነት እንደ አጋጣሚ ተጠቀምኩኝ እንጂ በሆን የተፈጠረ አልነበረም። እነዛን ደባሪ ቀናቶች ደግሜ ማሰብ እንኳን አልፈግም ለካስ 'በነፍስ የተጣመረን በስጋ መራቅ አይገድበው ኖሯል።' ራሴን ለመፈተን ብጥር ናፍቆት ግን የፍቅሯ ባርነት ስር የጣለኝ ሎሌዋ ነበርኩኝ።
ከሌላ ሰዎች ጋር ያየችኝ ቀን በኩርፍያዋ ውስጥ ስጋቷን አየዋለው፣በድርጊቶቿ ደግሞ አትንኩብኝ ባይነቷ ያሳብቅባታል።እንዴት ላስረዳት...?
ሌሎችን ሳልፈራ እንድቀርብ የሚያደርገኝኮ የእሷ በእኔ አለም ውስጥ የመኖሯ ነጻነት ነው።ልቤም ነፍሴም ከሷ ሆኖ በደመ ስጋ ብቀርባቸው ምን ዋጋ ይኖረው ይሆን? መጨረሻዬ በሙሉ ያረፈው በክቡር ልቧ ውስጥ ነው
ግን ሁሉም ጥያቄዎቿ መልስ ነበራቸው::ዝም ያለ መልስ...
ከዚ በኋላ ማንንም መልመድ አልፈልግም።አንቺን ባጣ አንዳች የሚተርፍ ነገር አይኖረኝም አልኳት... እቅፎቿ፣ስስቷና፣ግርምቷ መልስ ነበሩ
አንድ አለምን አንድ ነፍስን ከመስጠት የላቀ ምን ይኖር ይሆን....?
በእሷነቷ የህይወት ሸራ ላይ ቀለሞቼን አሳርፌ..ትናንታችንን፣ዛሬንና፣ነገዎቻችንን በጥበብ፣ በናፍቆት እያዋዛው፤ የመኖርን፣የተፈጥሮን ሁለት ገጽ እየሳልኩኝ እንደ ብራብሮ የፍቅርን መአዛ ከመልካም ሴትነቷ ውስጥ እየተቸርኩኝ የዘመንን፣የነፍስን ቅሪት እስከ እድሜ ማምሻዬ ገፍቼ በደበዘዙት አይኖቼ ተመልክቻት አቅም ባጡት መዳፎቼ በብርቱ ይዣት እርጅና ወቅሮት በተሸበሸበው ፊቴ፣ጊዜ በራሱ ባጎደላቸው ጥርሶቼ እየፈገግኩኝ፣ ማብቂያዬን፣ ከዚህ አለም መሄጃዬን ስጠብቅ እኖራለሁ።
እሷ የመጨረሻዬ መጨረሻ ናት ሌላ ታሪክ አይኖርም........
✍.... #Jo_ሊ
@fikrhn
@fikrhn
@fikrhn
BY እኔና አንቺ
❌Photos not found?❌Click here to update cache.
Share with your friend now:
tgoop.com/fikrhn/1114