Forwarded from 1137439312:AAGumjHJ7pzA6vrrfVMlKoqTUsCs59GySrg
✝ ሰበታ ዓለም ገና ስለ ፀበል ቦታ ✝
ይህ ቻናል የተዓምረኛው የአለም ገና ደ/ናዝሬት ኢየሱስ እና ቅ/ድ/ማርያም ወአቡነ ተክለ ሃይማኖት ገዳም መረጃ ፣ የፈውስ አገልግሎት እና ወቅታዊ ትምህርቶችና ዝማሬዎች የሚቀርብበት ነው::
ገዳማችን ከተመሰረተ ጀምሮ እጅግ ብዙ ሰዎች በሃይማኖት ሳይገደቡ ጭምር የጸበሉን ፈዋሽነት በማመን
📌 129 ሰዎች በላይ ከዓይነ ስዉርነት
📌 95 ሰዎች በላይ ከካንሰር
📌 54ከ ሰዎች በላይ HIV
ከ6525 በላይ ከአጋንንት እስራት የተፈቱ ሲሆን
በአሁኑ ሰዓት ዓለምን የሚያስደንቅ የእግዚአብሔር ሥራ እየተገለጠ ነው ::
ከሁለት ሽህ ህዝብ በላይ በጸበሉ እየተጠመቁ አሁንም ይኖራሉ ገዳማችን አሁንም ክፍት ስለሆነ ኑ ወደ ቤታችሁ ግቡ ! ቦታውን በደንብ ለማታውቁት በቂ መረጃ እንጽፋለን :: ከዚህ ወረርሽኝ ማምለጥ የምንችለው በንስሐ ሕይወት በመመላለስ ቅዱስ ሥጋውን በመብላት ክቡር ደሙን በመጠጣት እንጂ በሌላ በምንም ነገር ሊሆን አይችልም:: በተጨማሪ በገዳማችን የሚቀርቡ መንፈሳዊ ትምህርቶች እና መዝሙሮች በአማርኛ, በኦሮሚኛ ,በጉራግኛ በ Telegram
ቻናላችን ማግኘት ይችላሉ !
ይህ ቻናል የተዓምረኛው የአለም ገና ደ/ናዝሬት ኢየሱስ እና ቅ/ድ/ማርያም ወአቡነ ተክለ ሃይማኖት ገዳም መረጃ ፣ የፈውስ አገልግሎት እና ወቅታዊ ትምህርቶችና ዝማሬዎች የሚቀርብበት ነው::
ገዳማችን ከተመሰረተ ጀምሮ እጅግ ብዙ ሰዎች በሃይማኖት ሳይገደቡ ጭምር የጸበሉን ፈዋሽነት በማመን
📌 129 ሰዎች በላይ ከዓይነ ስዉርነት
📌 95 ሰዎች በላይ ከካንሰር
📌 54ከ ሰዎች በላይ HIV
ከ6525 በላይ ከአጋንንት እስራት የተፈቱ ሲሆን
በአሁኑ ሰዓት ዓለምን የሚያስደንቅ የእግዚአብሔር ሥራ እየተገለጠ ነው ::
ከሁለት ሽህ ህዝብ በላይ በጸበሉ እየተጠመቁ አሁንም ይኖራሉ ገዳማችን አሁንም ክፍት ስለሆነ ኑ ወደ ቤታችሁ ግቡ ! ቦታውን በደንብ ለማታውቁት በቂ መረጃ እንጽፋለን :: ከዚህ ወረርሽኝ ማምለጥ የምንችለው በንስሐ ሕይወት በመመላለስ ቅዱስ ሥጋውን በመብላት ክቡር ደሙን በመጠጣት እንጂ በሌላ በምንም ነገር ሊሆን አይችልም:: በተጨማሪ በገዳማችን የሚቀርቡ መንፈሳዊ ትምህርቶች እና መዝሙሮች በአማርኛ, በኦሮሚኛ ,በጉራግኛ በ Telegram
ቻናላችን ማግኘት ይችላሉ !
Forwarded from 1137439312:AAGumjHJ7pzA6vrrfVMlKoqTUsCs59GySrg
+++ ሦስቱ ዛፎች +++
በአንድ ኮረብታ ጫፍ ላይ የተተከሉ ሦስት ዛፎች ነበሩ፡፡ እነዚህ ዛፎች የወደፊት ተስፋቸውና ሕልማቸው ምን እንደሆነና ምን መሆን እንደሚፈልጉ መወያየት ጀመሩ፡፡
የመጀመሪያው ዛፍ ‹‹ታላቅ ንጉሥ የሚተኛበት አልጋ ለመሆን እመኛለሁ፡፡ ዙሪያዬን በልዩ ቅርጽ ተሠርቼ ሰው ሁሉ እንዲያከብረኝ ዝናዬ እንዲነገር እፈልጋለሁ›› አለ፡፡
ሁለተኛው ዛፍ ይኼን ሲሰማ የራሱን የተለየ ምኞት ተናገረ፡፡ ‹‹እኔ ደግሞ የምጓጓው ታላቅ መርከብ ሆኜ ለመሠራት ነው! በዓለም ላይ እጅግ ዝነኛ የሆኑ ነገሥታት በእኔ ላይ ተሣፍረው እንዲሔዱና ከጥንካሬዬ የተነሣ ሰዎች እኔ ላይ በመሳፈራቸው ያለ ሥጋት እንዲጓዙ ነው የምፈልገው!›› አለ - መርከብ ሆኖ በባሕር ላይ ሲንሳፈፍ በዓይነ ሕሊናው እየታየው፡፡
ሦስተኛው ዛፍ ግን ‹‹ዛፍነቴን ብተው ያንዘፍዝፈኝ›› አለ፡፡ ‹‹እኔ የምፈልገው ከዚሁ ሳልነቃነቅ ረዥም ዛፍ ሆኜ ወደ ላይ ማደግ ነው፡፡ እጅግ ከፍ ብዬ አድጌ የዛፎች ሁሉ ንጉሥ ሆኜ ፣ ለሰማይ እጅግ ቅርብ ሆኜ ሰዎች በእኔ መሰላልነት ወደ ገነት እንዲገቡና እኔን ባዩ ቁጥር ፈጣሪያቸውን እንዲያስታውሱ እፈልጋለሁ›› አለና ምኞቱን ተናገረ፡፡
ይህን ተነጋግረው እንደጨረሱ አናጢዎች ወደ እነዚህ ዛፎች መጡ
አንደኛው አናጢ የንጉሥ አልጋ ለመሆን የሚመኘውን ዛፍ ቀረብ አለና ካየው በኋላ ‹‹ይኼ ዛፍ ጠንካራ ይመስላል ፤ ወስጄ ለቤት ዕቃ ሠሪዎች እሸጠዋለሁ›› አለ፡፡ ይህን የሰማው ዛፍ ‹የንጉሥ አልጋ› ሆኖ የመሠራት ሕልሙ ዕውን እንደሚሆን በመተማመን ፈነደቀ፡፡ አናጢው ወስዶ የሸጠላቸው እንጨት ሠሪዎች ግን የዛፉን ሕልም ሳይረዱ የንጉሥ አልጋ አድርገው በመሥራት ፈንታ የከብቶች የሣር ድርቆሽ ማስቀመጫ ሣጥን አድርገው ሠሩትና በአንድ በረት ውስጥ ተጣለ፡፡
ሁለተኛው አናጢ የንጉሥ መርከብ እሆናለሁ ብሎ የሚመኘውን ዛፍ ቀረብ ብሎ አየውና ‹‹ይኼ ዛፍ ጠንካራ ይመስላል ፤ መርከብ ወደሚሠሩ ሰዎች ወስጄ ባሳየው ጥሩ ዋጋ ያወጣልኛል›› አለ፡፡ ዛፉ ‹ስዕለቴ ሠመረ› ብሎ ተደሰተ፡፡ ሆኖም መርከብ ሠሪዎቹ ምኞቱን ሳያውቁ ቆራርጠው ቆራርጠው በርከት ያሉ የዓሣ ማጥመጃ ጀልባዎችን ሠሩበት፡፡ መርከብ እሆናለሁ ብሎ የተመኘው ይህ ዛፍ ዓሣ አጥማጆችን ጭኖ እየተንሳፈፈ የንጉሥ መርከብ ሲያልፍ ተመልካች ሆነ፡፡
ሦስተኛውን ዛፍም በመጥረቢያ ሲቆርጡት የዛፎች ንጉሥ ሆኖ ከፍ ብሎ የማደግ ሕልሙን አብረው ቆረጡት፡፡
ከብዙ ዓመታት በኋላ አንዲት የጸነሰች ብላቴና ከአንድ አረጋዊ ጋር ቤተልሔም በሚባል የይሁዳ ከተማ መጣች፡፡ በወቅቱ የማደሪያ ሥፍራ ስላልነበር በከብቶች በረት ውስጥ ለማደር ገቡ ፤ ጸንሳ የነበረችውንም ልጇን በበረት ውስጥ ወለደችው፡፡ የመኝታ ሥፍራ ስላልነበር ሕጻኑን የከብቶቹ የሣር ድርቆሽ በሚቀመጥበት ሳጥን ውስጥ አስተኛችው፡፡ የዚያን ቀን ለተወለደው ሕጻን ከሩቅ የመጡ ነገሥታት ሳይቀር ሥጦታን አመጡለት፡፡ የንጉሥ አልጋ መሆን ይመኝ በነበረው ያ ዛፍ ሳጥን ሆኖ ቢሠራም የነገሥታት ንጉሥ መኝታ ሆነ፡፡
ይህ ከሆነ ከሠላሳ ዓመታት በኋላ የዓሣ ማጥመጃ ሆኖ በተሠራው ጀልባ ላይ ከወትሮው በተለየ ሁኔታ ዓሥራ ሦስት ሰዎች ተሳፈሩበት፡፡ የንጉሥ መርከብ ለመሆን የተመኘው ይህ ጀልባ በጀልባነቱ ዓሥራ ሦስት ተሳፋሪዎችን ተሸክሞ ሲማረር በጉዞ መካከል ድንገት ትልቅ ማዕበል ተነሥቶ መርከቧን ያናውጻት ጀመረ፡፡ ተሳፋሪዎቹ ጀልባዋን ለመቆጣጠር ታገሉ፡፡
ከመካከላቸው ግን አንዱ ተሳፋሪ ተኝቶ ነበር፡፡ ሞገዱ እየባሰ ሲመጣ የተኛውን ተሣፋሪ ‹‹ስንጠፋ አይገድህምን?›› ብለው ቀሰቀሱት፡፡ እሱም ተነሥቶ ማዕበሉን ገሠጸው፡፡ ጀልባው ድሮ እንደተመኘው የጫነው የነገሥታትን ንጉሥ እንደሆነ ተረዳ፡፡
ይህ ከሆነ ከሁለት ዓመታት በኋላ ደግሞ የዛፎች ንጉሥ ለመሆንና ወደ ሰማይ መውጫ መሰላል ለመሆን የተመኘውን ዛፍ አምጥተው ለአንድ ወንጀል ለሌለበት ንጹሕ አሸከሙት ፣ ከተራራ ጫፍ ሲደርሱም ባሸከሙት እንጨት ሰቀሉት፡፡ እንደተሰቀለ ምድር ለሦስት ሰዓታት ጨለመች ... ብዙ ተአምራት ተፈጸሙ፡፡ ይህ ዛፍ እንደተመኘው የዕጽዋት ሁሉ ንጉሥ ሆነ ፤ ሰዎች በእሱ መሰላልነት ወደ ገነት ገቡ ፤ እሱን ያዩ ሁሉ ፈጣሪያቸውን ያስታውሳሉ፡፡
በሁላችንም ሕሊና ውስጥ የእነዚህ ዛፎች ሕልም የተበላሸው ገና ያን ጊዜ ወዳላሰቡት ሥፍራ ሲጣሉ ነበር፡፡ ነገሩ አበቃ ብለን ስናስብ ግን የሦስቱም ምኞት ተሳካ፡፡ ይህ ጥንታዊ ታሪክ ምሳሌ እንጂ እውነተኛ ታሪክ እንዳልሆነ ግልጽ ነው፡፡ በዚህ ታሪክ ውስጥ ግን አንድ እውነታ አለ፡፡ በሕይወታችን ውስጥ እኛ አበቃልን ስንል እግዚአብሔር ሥራውን ይጀምራል፡፡
‹‹የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔርም ያለቀ የተቈረጠ ነገርን በምድር ሁሉ መካከል ይፈጽማል።›› ኢሳ. 10፡23
ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ
ግንቦት 2007 ዓ ም
ኩዌት የተጻፈ [ከሞት ባሻገር በተሰኘው መጽሐፍ የታተመ]
(ይህን በሥነ ጽሑፍ ዓለም የታወቀ ጥንታዊ ትረካ ያገኘሁት Archangel Michael Coptic Orthodox Church News letter (St. Mary Coptic Orthodox Church, East Brunswick, N.J./ volume 3 Feb. 2002) ዕትም ላይ ሲሆን ሃሳቡን ብቻ በመውሰድና አንዳንድ ለውጦች በማድረግ በዚህ መልኩ አስቀምጬዋለሁ፡፡ ይህ ታሪክ ምክር አዘል ምሳሌ ብቻ እንጂ ለተባሉት ዕቃዎችም ሆነ ለመስቀል ታሪካዊ አመጣጥ የሚጠቀስ ተአማኒ ታሪክ እንዳልሆነ አስታውሳለሁ፡፡)
በአንድ ኮረብታ ጫፍ ላይ የተተከሉ ሦስት ዛፎች ነበሩ፡፡ እነዚህ ዛፎች የወደፊት ተስፋቸውና ሕልማቸው ምን እንደሆነና ምን መሆን እንደሚፈልጉ መወያየት ጀመሩ፡፡
የመጀመሪያው ዛፍ ‹‹ታላቅ ንጉሥ የሚተኛበት አልጋ ለመሆን እመኛለሁ፡፡ ዙሪያዬን በልዩ ቅርጽ ተሠርቼ ሰው ሁሉ እንዲያከብረኝ ዝናዬ እንዲነገር እፈልጋለሁ›› አለ፡፡
ሁለተኛው ዛፍ ይኼን ሲሰማ የራሱን የተለየ ምኞት ተናገረ፡፡ ‹‹እኔ ደግሞ የምጓጓው ታላቅ መርከብ ሆኜ ለመሠራት ነው! በዓለም ላይ እጅግ ዝነኛ የሆኑ ነገሥታት በእኔ ላይ ተሣፍረው እንዲሔዱና ከጥንካሬዬ የተነሣ ሰዎች እኔ ላይ በመሳፈራቸው ያለ ሥጋት እንዲጓዙ ነው የምፈልገው!›› አለ - መርከብ ሆኖ በባሕር ላይ ሲንሳፈፍ በዓይነ ሕሊናው እየታየው፡፡
ሦስተኛው ዛፍ ግን ‹‹ዛፍነቴን ብተው ያንዘፍዝፈኝ›› አለ፡፡ ‹‹እኔ የምፈልገው ከዚሁ ሳልነቃነቅ ረዥም ዛፍ ሆኜ ወደ ላይ ማደግ ነው፡፡ እጅግ ከፍ ብዬ አድጌ የዛፎች ሁሉ ንጉሥ ሆኜ ፣ ለሰማይ እጅግ ቅርብ ሆኜ ሰዎች በእኔ መሰላልነት ወደ ገነት እንዲገቡና እኔን ባዩ ቁጥር ፈጣሪያቸውን እንዲያስታውሱ እፈልጋለሁ›› አለና ምኞቱን ተናገረ፡፡
ይህን ተነጋግረው እንደጨረሱ አናጢዎች ወደ እነዚህ ዛፎች መጡ
አንደኛው አናጢ የንጉሥ አልጋ ለመሆን የሚመኘውን ዛፍ ቀረብ አለና ካየው በኋላ ‹‹ይኼ ዛፍ ጠንካራ ይመስላል ፤ ወስጄ ለቤት ዕቃ ሠሪዎች እሸጠዋለሁ›› አለ፡፡ ይህን የሰማው ዛፍ ‹የንጉሥ አልጋ› ሆኖ የመሠራት ሕልሙ ዕውን እንደሚሆን በመተማመን ፈነደቀ፡፡ አናጢው ወስዶ የሸጠላቸው እንጨት ሠሪዎች ግን የዛፉን ሕልም ሳይረዱ የንጉሥ አልጋ አድርገው በመሥራት ፈንታ የከብቶች የሣር ድርቆሽ ማስቀመጫ ሣጥን አድርገው ሠሩትና በአንድ በረት ውስጥ ተጣለ፡፡
ሁለተኛው አናጢ የንጉሥ መርከብ እሆናለሁ ብሎ የሚመኘውን ዛፍ ቀረብ ብሎ አየውና ‹‹ይኼ ዛፍ ጠንካራ ይመስላል ፤ መርከብ ወደሚሠሩ ሰዎች ወስጄ ባሳየው ጥሩ ዋጋ ያወጣልኛል›› አለ፡፡ ዛፉ ‹ስዕለቴ ሠመረ› ብሎ ተደሰተ፡፡ ሆኖም መርከብ ሠሪዎቹ ምኞቱን ሳያውቁ ቆራርጠው ቆራርጠው በርከት ያሉ የዓሣ ማጥመጃ ጀልባዎችን ሠሩበት፡፡ መርከብ እሆናለሁ ብሎ የተመኘው ይህ ዛፍ ዓሣ አጥማጆችን ጭኖ እየተንሳፈፈ የንጉሥ መርከብ ሲያልፍ ተመልካች ሆነ፡፡
ሦስተኛውን ዛፍም በመጥረቢያ ሲቆርጡት የዛፎች ንጉሥ ሆኖ ከፍ ብሎ የማደግ ሕልሙን አብረው ቆረጡት፡፡
ከብዙ ዓመታት በኋላ አንዲት የጸነሰች ብላቴና ከአንድ አረጋዊ ጋር ቤተልሔም በሚባል የይሁዳ ከተማ መጣች፡፡ በወቅቱ የማደሪያ ሥፍራ ስላልነበር በከብቶች በረት ውስጥ ለማደር ገቡ ፤ ጸንሳ የነበረችውንም ልጇን በበረት ውስጥ ወለደችው፡፡ የመኝታ ሥፍራ ስላልነበር ሕጻኑን የከብቶቹ የሣር ድርቆሽ በሚቀመጥበት ሳጥን ውስጥ አስተኛችው፡፡ የዚያን ቀን ለተወለደው ሕጻን ከሩቅ የመጡ ነገሥታት ሳይቀር ሥጦታን አመጡለት፡፡ የንጉሥ አልጋ መሆን ይመኝ በነበረው ያ ዛፍ ሳጥን ሆኖ ቢሠራም የነገሥታት ንጉሥ መኝታ ሆነ፡፡
ይህ ከሆነ ከሠላሳ ዓመታት በኋላ የዓሣ ማጥመጃ ሆኖ በተሠራው ጀልባ ላይ ከወትሮው በተለየ ሁኔታ ዓሥራ ሦስት ሰዎች ተሳፈሩበት፡፡ የንጉሥ መርከብ ለመሆን የተመኘው ይህ ጀልባ በጀልባነቱ ዓሥራ ሦስት ተሳፋሪዎችን ተሸክሞ ሲማረር በጉዞ መካከል ድንገት ትልቅ ማዕበል ተነሥቶ መርከቧን ያናውጻት ጀመረ፡፡ ተሳፋሪዎቹ ጀልባዋን ለመቆጣጠር ታገሉ፡፡
ከመካከላቸው ግን አንዱ ተሳፋሪ ተኝቶ ነበር፡፡ ሞገዱ እየባሰ ሲመጣ የተኛውን ተሣፋሪ ‹‹ስንጠፋ አይገድህምን?›› ብለው ቀሰቀሱት፡፡ እሱም ተነሥቶ ማዕበሉን ገሠጸው፡፡ ጀልባው ድሮ እንደተመኘው የጫነው የነገሥታትን ንጉሥ እንደሆነ ተረዳ፡፡
ይህ ከሆነ ከሁለት ዓመታት በኋላ ደግሞ የዛፎች ንጉሥ ለመሆንና ወደ ሰማይ መውጫ መሰላል ለመሆን የተመኘውን ዛፍ አምጥተው ለአንድ ወንጀል ለሌለበት ንጹሕ አሸከሙት ፣ ከተራራ ጫፍ ሲደርሱም ባሸከሙት እንጨት ሰቀሉት፡፡ እንደተሰቀለ ምድር ለሦስት ሰዓታት ጨለመች ... ብዙ ተአምራት ተፈጸሙ፡፡ ይህ ዛፍ እንደተመኘው የዕጽዋት ሁሉ ንጉሥ ሆነ ፤ ሰዎች በእሱ መሰላልነት ወደ ገነት ገቡ ፤ እሱን ያዩ ሁሉ ፈጣሪያቸውን ያስታውሳሉ፡፡
በሁላችንም ሕሊና ውስጥ የእነዚህ ዛፎች ሕልም የተበላሸው ገና ያን ጊዜ ወዳላሰቡት ሥፍራ ሲጣሉ ነበር፡፡ ነገሩ አበቃ ብለን ስናስብ ግን የሦስቱም ምኞት ተሳካ፡፡ ይህ ጥንታዊ ታሪክ ምሳሌ እንጂ እውነተኛ ታሪክ እንዳልሆነ ግልጽ ነው፡፡ በዚህ ታሪክ ውስጥ ግን አንድ እውነታ አለ፡፡ በሕይወታችን ውስጥ እኛ አበቃልን ስንል እግዚአብሔር ሥራውን ይጀምራል፡፡
‹‹የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔርም ያለቀ የተቈረጠ ነገርን በምድር ሁሉ መካከል ይፈጽማል።›› ኢሳ. 10፡23
ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ
ግንቦት 2007 ዓ ም
ኩዌት የተጻፈ [ከሞት ባሻገር በተሰኘው መጽሐፍ የታተመ]
(ይህን በሥነ ጽሑፍ ዓለም የታወቀ ጥንታዊ ትረካ ያገኘሁት Archangel Michael Coptic Orthodox Church News letter (St. Mary Coptic Orthodox Church, East Brunswick, N.J./ volume 3 Feb. 2002) ዕትም ላይ ሲሆን ሃሳቡን ብቻ በመውሰድና አንዳንድ ለውጦች በማድረግ በዚህ መልኩ አስቀምጬዋለሁ፡፡ ይህ ታሪክ ምክር አዘል ምሳሌ ብቻ እንጂ ለተባሉት ዕቃዎችም ሆነ ለመስቀል ታሪካዊ አመጣጥ የሚጠቀስ ተአማኒ ታሪክ እንዳልሆነ አስታውሳለሁ፡፡)
፨፨፨፨የወራት ስያሜ፨፨፨
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
ዲ/ን ሕሊና በለጠ
ከመስከረም እስከ ጳጉሜ የተሰየሙት ወሮቻችን ስያሜያቸውን ከየት እንዳገኙ ያውቃሉ? እስኪ የሚከተለውን ይመልከቱ፡፡
1
የወሩ ስም - መስከረም
የግእዝ ሥርወ ቃሉ - መሴ እና ከረም
ትርጉም - መሴ-አለፈ ፣ መሸ ፤ ከረም-ክረምት፤ ክረምት አለፈ ፣ ክረምቱ መሸ
2
የወሩ ስም - ጥቅምት
የግእዝ ሥርወ ቃሉ - ጠቀመ
ትርጉም - ሠራ፤ ጠቃሚ ጊዜ
3
የወሩ ስም - ኅዳር
የግእዝ ሥርወ ቃሉ - ኀደረ
ትርጉም - አደረ-ሰው በወርኃ አዝመራ ማሳ ውስጥ ለጥበቃ ማደሩን ይገልፃል
4
የወሩ ስም - ታኅሳስ
የግእዝ ሥርወ ቃሉ - ኀሠሠ
ትርጉም - መረመረ- በመኸር ወቅት የሰብል ምርመራን ያመለክታል ፤ ሰብዐ ሰገል በታኅሳስ ወር የተወለደውን ጌታችንን ማሰሳቸውን ፣ መፈለጋቸውንም ያመለክታል።
5
የወሩ ስም - ጥር
የግእዝ ሥርወ ቃሉ - ነጠረ ፣ አጥረየ
ትርጉም - ነጠረ - ጠረረ- ብልጭ አለ፤ ነጻ፤ የፀሐይን ግለት ወቅት ያሳያል ፤ አጥረየ - ገዛ (ከብቱም ምርቱም የሚሸጥበት የሚገዛበት ወቅት)
6
የወሩ ስም - የካቲት
የግእዝ ሥርወ ቃሉ - ከተተ ፣ ከቲት
ትርጉም - መክተቻ (እኅልን ወደ ጎተራ)
7
የወሩ ስም - መጋቢት
የግእዝ ሥርወ ቃሉ - መገበ
ትርጉም - በቁሙ የሚመግብ (በጎተራ የተከተተው የሚበላበት)
8
የወሩ ስም - ሚያዝያ
የግእዝ ሥርወ ቃሉ - መሐዘ
ትርጉም - ጎለመሰ ጎበዘ ሚስት ፈለገ (ወርኀ ሰርግ መሆኑን ሲያጠይቅ)
9
የወሩ ስም - ግንቦት
የግእዝ ሥርወ ቃሉ - ገነበ
ትርጉም - ገነባ፤ ሠራ፤ ቆፈረ፤ ሰረሰረ (ለእርሻ የመሬቱን መዘጋጀት ያሳያል)
10
የወሩ ስም - ሰኔ
የግእዝ ሥርወ ቃሉ - ሰነየ
ትርጉም - አማረ (አዝርዕቱ)
11
የወሩ ስም - ሐምሌ
የግእዝ ሥርወ ቃሉ - ሐመለ
ትርጉም - ለመለመ ፣ ሐመልማል ሆነ ፣ ለቀመ (ለጎመን)
12
የወሩ ስም - ነሐሴ
የግእዝ ሥርወ ቃሉ - አናሕስየ
ትርጉም - አቀለለ፤ ተወ (የክረምቱን እያደር መቅለል ያሳያል)
13
የወሩ ስም - ጳጉሜ
ሥርወ ቃሉ - ኤጳጉሚኖስ (ግሪክ)
ትርጉም - ተጨማሪ ማለት ነው፡፡
(1.ኅብረ አትዮጵያ፤ ከቴዎድሮስ በየነ፤ አዲስ አበባ፤ 1999ዓ.ም.፤ ገጽ 16-17
2. ከሊቃውንት አስተምህሮ)
ጳጉሜ 2006 ዓ.ም.
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
ዲ/ን ሕሊና በለጠ
ከመስከረም እስከ ጳጉሜ የተሰየሙት ወሮቻችን ስያሜያቸውን ከየት እንዳገኙ ያውቃሉ? እስኪ የሚከተለውን ይመልከቱ፡፡
1
የወሩ ስም - መስከረም
የግእዝ ሥርወ ቃሉ - መሴ እና ከረም
ትርጉም - መሴ-አለፈ ፣ መሸ ፤ ከረም-ክረምት፤ ክረምት አለፈ ፣ ክረምቱ መሸ
2
የወሩ ስም - ጥቅምት
የግእዝ ሥርወ ቃሉ - ጠቀመ
ትርጉም - ሠራ፤ ጠቃሚ ጊዜ
3
የወሩ ስም - ኅዳር
የግእዝ ሥርወ ቃሉ - ኀደረ
ትርጉም - አደረ-ሰው በወርኃ አዝመራ ማሳ ውስጥ ለጥበቃ ማደሩን ይገልፃል
4
የወሩ ስም - ታኅሳስ
የግእዝ ሥርወ ቃሉ - ኀሠሠ
ትርጉም - መረመረ- በመኸር ወቅት የሰብል ምርመራን ያመለክታል ፤ ሰብዐ ሰገል በታኅሳስ ወር የተወለደውን ጌታችንን ማሰሳቸውን ፣ መፈለጋቸውንም ያመለክታል።
5
የወሩ ስም - ጥር
የግእዝ ሥርወ ቃሉ - ነጠረ ፣ አጥረየ
ትርጉም - ነጠረ - ጠረረ- ብልጭ አለ፤ ነጻ፤ የፀሐይን ግለት ወቅት ያሳያል ፤ አጥረየ - ገዛ (ከብቱም ምርቱም የሚሸጥበት የሚገዛበት ወቅት)
6
የወሩ ስም - የካቲት
የግእዝ ሥርወ ቃሉ - ከተተ ፣ ከቲት
ትርጉም - መክተቻ (እኅልን ወደ ጎተራ)
7
የወሩ ስም - መጋቢት
የግእዝ ሥርወ ቃሉ - መገበ
ትርጉም - በቁሙ የሚመግብ (በጎተራ የተከተተው የሚበላበት)
8
የወሩ ስም - ሚያዝያ
የግእዝ ሥርወ ቃሉ - መሐዘ
ትርጉም - ጎለመሰ ጎበዘ ሚስት ፈለገ (ወርኀ ሰርግ መሆኑን ሲያጠይቅ)
9
የወሩ ስም - ግንቦት
የግእዝ ሥርወ ቃሉ - ገነበ
ትርጉም - ገነባ፤ ሠራ፤ ቆፈረ፤ ሰረሰረ (ለእርሻ የመሬቱን መዘጋጀት ያሳያል)
10
የወሩ ስም - ሰኔ
የግእዝ ሥርወ ቃሉ - ሰነየ
ትርጉም - አማረ (አዝርዕቱ)
11
የወሩ ስም - ሐምሌ
የግእዝ ሥርወ ቃሉ - ሐመለ
ትርጉም - ለመለመ ፣ ሐመልማል ሆነ ፣ ለቀመ (ለጎመን)
12
የወሩ ስም - ነሐሴ
የግእዝ ሥርወ ቃሉ - አናሕስየ
ትርጉም - አቀለለ፤ ተወ (የክረምቱን እያደር መቅለል ያሳያል)
13
የወሩ ስም - ጳጉሜ
ሥርወ ቃሉ - ኤጳጉሚኖስ (ግሪክ)
ትርጉም - ተጨማሪ ማለት ነው፡፡
(1.ኅብረ አትዮጵያ፤ ከቴዎድሮስ በየነ፤ አዲስ አበባ፤ 1999ዓ.ም.፤ ገጽ 16-17
2. ከሊቃውንት አስተምህሮ)
ጳጉሜ 2006 ዓ.ም.
✞ የወሲብ ፊልሞችና ጠንቆቻቸው ✞
ክፍል - 1
በስመ አብ፥ ወወልድ፥ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን፡፡
✞ ዝም ያለው የሚሊዮኖች ጩኸት ✞
ልቅ የሆኑ የወሲብ ፊልሞች መቼ እንደተጀመሩ በውል ባይታወቅም፤ ወደ አገራችን ኢትዮጵያ ዛሬ ላይ ተስፋፍተው፤ የወጣቱና የጎልማሳው የትውልድ ክፍለ ዘመን ፈተና ሆነው ሁሉም በየግል በየግል ከራሱ ጋር እንዲጣላና የሃይማኖት አካሄዶችን እንዲሸሽ ሰፊ ድርሻ የተጫወተ የአጥፊው ጥልቁ መልአክ አባዶን ሴራ ነው፡፡
+++
በዘመናችን በወሲብ ፊልም ያልተጠመደ ወጣትና ጎልማሳ ማግኘት አዳጋች ይሆናል፡፡ በተለይ የእጅ ስልክ በየግል በየግል አብዛኞቻችን እንደ መታወቂያ ካርድ ይዘነው የምንዞረው መለያችን ከመሆኑም ጋር ተያይዞ በቀላሉ የተለያዩ ድረገጾችን የማግኘት አጋጣሚዎች(Internet accessibility) በመኖሩ ሰዎች ሳይቸገሩ ወደ ወሲብ ፊልም ቁራኛነት በመግባት ለመውጣት ግን ተቸግረው ይስተዋላሉ፡፡
+++
የወሲብ ፊልም ሱሰኝነት በአገራችንና በዓለም አቀፍ ደረጃ ስነልቦናዊ፣ አካላዊና ማኅበራዊ ሰፊ ቀውሶችን በወጣቱ ትውልድ ላይ ለማድረስ ሆን ተብሎ በአጥፊ መናፍስቶችና የክፋት መሣሪያ በሆኑ ሰዎች የተቀናበረ የወጥመድ መረብ ሲሆን፤ ግቡንም አሳክቶ ልክ እንደ ወረርሺኝ በብዙ አገራት በመዝለቅ ሁለንተናዊ እና ዘርፈ ብዙ ቀውሶችን ከዘመን ዘመን በሚጋሽበው ትውልድ ላይ በጥልቅ መሠረት ለማስከተል ችሏል፡፡ ስለዚህም ነገር የዮሐንስ ራእይ ምን ይላል የሚለውን እንመልከት፡፡
(የዮሐንስ ራእይ ምዕ. 17)
---
3፤ በመንፈስም ወደ በረሀ ወሰደኝ፤ የስድብም ስሞች በሞሉበት፥ ሰባት ራሶችና አሥር ቀንዶችም ባሉበት በቀይ አውሬ ላይ አንዲት ሴት ተቀምጣ አየሁ።
4፤ ሴቲቱም በቀይና በሐምራዊ ልብስ ተጐናጽፋ በወርቅና በከበሩ ድንጋዮች በዕንቈችም ተሸልማ ነበር፥ በእጅዋም የሚያስጸይፍ ነገር የዝሙትዋም ርኵሰት የሞላባትን የወርቅ ጽዋ ያዘች፤
5፤ በግምባርዋም ምስጢር የሆነ ስም። ታላቂቱ ባቢሎን፥ የጋለሞታዎችና የምድር ርኵሰት እናት ተብሎ ተጻፈ።
በሴት ጾታ የተገለጸው ይህ የጥልቁ መንፈስ፤ ትውልዱን በተብለጨለጨ የዘመን ውበትና መሣሪያ አነሁልሎ፤ ዜጎች ከእግዚአብሔር አምላክ ጋር የሚኖራቸውን የቅደስና ሕይወት በመቀንጠስ፤ በታላቅ የዝሙት ማዕበል እንዲንሳፈፉ ያደረገ የጥልቁ አለቃ የአባዶን መንፈስ ምሪት ነው፡፡
ዛሬ ሲሆን የምናየው ሁሉ ምንድነው? ለምን ትውልዱ በወሲብ ግለት ነደደ? ለምን በመዝናኛው ኢንደስትሪ በኩል የሚቀርቡት ጽሑፎች፣ ዘፈኖች እና ፊልሞች ላይ የወሲብ ድርጊቶችና የራቁትነት ገጽታዎች እጅግ በዙ? ዕድሜና የአገራትን ባሕል ሳይመርጡ ለሕዝብ ያለ ማቋረጥ የሚተላለፉ የሚዲያ ውጤቶች በብዛት የዝሙት ምኞትን የሚጠሩ ስለምን ሆኑ? ለምን የአስገድዶ መድፈር ዜናዎች፣ የጽንስ ማስወረድ ድርጊቶች፣ የእርግዝና መቆጣጠሪያና ማዘግያ ዘዴዎች ከመጠን በላይ እየጨመሩ ሄዱ?
ምክንያቱም አበለጭልጫ በሐምራዊ ልብስ ተጋጊጣ የተገለጸቺው የዝሙት መንፈስ፤ የመጨረሻው ዘመነ ጊዜዋ ሆኖላታልና የሠራዊቶቿን የርኩሰት ጽዋ በዓለም ላይ ስላፈሰሰቺው ነው፡፡
+++
የወሲብ ፊልሞች ሱስ ልክ እንደ ትምባሆ፣ አልኮልና አደንዛዥ ዕፆች ሱስ ከያዘ በቀላሉ የማይለቅ፤ ቀስ በቀስ በመቆራኘትም መላ የኑሮ አቅጣጫንና የውስጥ ሕይወትን መንገድ ወደ አንድ መስመር በመሳብ፤ የኢንተርኔትና ራስን በራስ የማርካት(ግለ-ሩካቤ) ተጠማጅ የሚያድርግ ያልተነገረለት እጅግ አደገኛ የመናፍስት ማፍዘዣ ነው፡፡ የወሲብ ፊልሞችን የመመልከት ልምምዱ ቀስ በቀስ እያደገና እንደ ግል ጠባይ እየጎለበተ የዘወትር እህል ውኃ የሚሆን መላ የስሜት ሕዋስን በዝግታ እየተቆጣጠረ የሚመጣ የአእምሮ ማስከሪያ ነው፡፡ ዝሙታዊ ፊልሞችን ለመመልከት ቀላል፤ ከማየት ለመራቅ ግን ፈታኝ የሆነበት አንደኛው መሠረታዊ ምክንያት የመናፍስት ሰንሰለትና ሰይጣናዊ እገዛ ያለበት ከመሆኑ ጋር በተያያዘ፤ ግለሰቦች ከሱሱ ለመላቀቅ ብለው! ብለው! ሲሰለቻቸው፤ 'በራሱ ጊዜ ይተወኛል' እያሉ ተስፋ በማሳጣት እንዲኖሩ እያደረገ ነገን አጨልሞ ዛሬን በቁራኝነት የሚዋረስ አደንዣዥ ወረርሺኝም ነው፡፡
+++
<< ቁራኛነት >> ከርኩሳን መናፍስት ጋር በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ የሚያያዝ የጥፋት አሠራር አለው፡፡ ይህንን ጥቂት የማይባሉ ሰዎች ስለማይገነዘቡ፤ በሥጋዊ መፍትሔዎች ብቻ ተጉዘው ከጥገኝነት ችግር ለመላቀቅ በተደጋጋሚ ሲጥሩ ለጥቂት ቀናት አሊያ ሳምንታት ተሳክቶላቸው መፍትሔ ቢያገኙም፤ ዞሮ ዞሮ ወደ ተዘፈቁበት ማጥ እየወደቁ ተስፋ በመቁረጥም እንደ ልማድና አንድ የኑሮ አካል አስተናግደውት ዝም ብለው ተቀምጠዋል፡፡ ዘመናዊ ነው በሚባል በዚህኛው ትውልድም፤ ግለ-ወሲብ እንደ አንድ የሥልጣኔ ክፍል ተቆጥሮ በየትምህርት ቤቱና መሥሪያ ቤቱ ቀልድና ስላቅ እየተበጀለት፤ በውስጥ ግን እየተለቀሰለት ያለ የብዙዎች ድምፅ አልባ ዋይታ እንዲሆን የአንበሳውን ድርሻ የተጫወተው የወሲብ ፊልም ቁራኝነት ሲሆን ወጣቶች በጋራ ሲጨዋወቱ የሚስቁበት፤ በየግል በየግል ግን የሚያለቅሱበትና ራሳቸውን የሚጠሉበት አዚማዊ ጠባይ ያለው የውስጥ ድንዛዜንና ግዴየለሽነትን የሚያሰራጭ የርኩሳን መናፍስት የግብር ጭዳ የሚያደርግ የጓዳ የሚመስል የዓለም በሽታ ነው፡፡
+++
ህቡዕ ሰይጣናዊ ድርጅቶች እንደ ኢሉሚናቲ፣ ዘ ናይት ቴምፕላርስ እና ፍሬመሰንስ ያሉት አጥፊዎች፥ ቀድመው ከጠለፉት የሴራ ድርጊቶችና የትውልድ ማደንዣዎች መካከል በሰፊ ጥናትና ዘመናትን በፈጀ የሴራ ቅንብር የተተገበረው የወሲብ ፊልም የጠምዛዥነት እቅድ(project)፤ ከፍተኛና ዓለም አቀፋዊ በጀት ተበጅቶለት፤ ዛሬ ላይ ሰለጠኑ በሚባሉ አገራት ላይ ራሱን የቻለ የመዝናኛ ማዕከል(Film industry) ሆኖ፤ ገና ከማለዳው ወጣቱን እያሰረና እያጨነገፈ፤ ከታለመለት እቅደ-ንድፍም አሻግሮ በመዝለቅ ጎልማሳና በዕድሜ የገፉ ባለትዳር የልጆች ወላጅ የሆኑ ሰዎችን ጭምር ሱሰኛ አድርጎ ያስቀመጠ ሲሆን፤ መፍትሔው ተሸፋፍኖ ያስከተለው ኪሣራ ግን የተገለጠ ደንበኛ የዲያቢሎስ ቀኝ እጅ ለመሆን ችሏል፡፡
ከኢንተርኔት ድረገጾችም ውስጥ ከ50% በላይ ሽፋን ያላቸው እነዚህ የፍትወት ፊልሞች፣ ምስሎችና ድምፆች፤ ከየትኛውም በኢንተርኔት በኩል ከሚኖሩ ድረገጾች የበለጠ ተከታታይ ቋሚ ተጠቃሚ ሰዎች እያፈሩ መሆኑን ስንመለከት፤ የአጥፊው አባዶን ሠራዊት ትውልድን የማደንዘዙ ተልዕኮ ምን ያህል ዘመናትንና ትውልዶቻቸውን አንድ'ጋ ሰብስቦ የማሰር አሠራሩን በተሳካ መልኩ ማከናወን እንደቻለ እንገነዘባለን፡፡
እንደ አሜርካ ባሉ አገራት እንደ አንድ የመዝናኛው ዘርፍ አውድና ይዘት ተቆጥሮ የልቅ ወሲብ ተዋናዮችን በመመልመልና በዓለምም ፊት በመሸለም የሥራ ዘርፍ አስመስሎ እንደ ማኅብረሰባዊ ልማዶች ለማስቆጠር በተደረገው የተጋድሎ ጥረት በኩልም የተለመደና የዘመን ለውጥ አንዱ ክፍል እንደሆነ በዘዴ ለማሳሰብና በሰው ልጆች ልቦና ላይ እንዲታተም ለማስገደድ በሙዚቃውና በፊልሙ ኢንደስትሪ አማካኝነት መጠነ ሰፊ ፕሮፖ-ጋንዳ ተሠርቶለትና ሕሊናን የመቆጣጠሪያ ቴክኒክ ተቀርጾለት በየቀኑ የሚሰራጭ በመሆኑ ከላይ ከባለሥልጣናት አንስቶ እስከ ታች ያሉ የሕብረተረሰብ ክፍላትን ጨምድዶ የያዘ አይነተኛ ልክፍት እንዲሆን በቀላሉ በእጅ ስልክና በላፕቶፕ ኮምፒውተሮች የመገኘት አቅሙን በማስፋት የአየር ሞገድ ምኅዋሩን በመቆጣጠር የሄዱበት ሚስጢራዊና መናፍስታዊ አካሄድ እጅግ የበዙ የሰው ልጆችን በአጭርና በተመሳሳይ መልኩ በማጨንገፍ ተሳክቶላቸዋል፡፡
ክፍል - 1
በስመ አብ፥ ወወልድ፥ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን፡፡
✞ ዝም ያለው የሚሊዮኖች ጩኸት ✞
ልቅ የሆኑ የወሲብ ፊልሞች መቼ እንደተጀመሩ በውል ባይታወቅም፤ ወደ አገራችን ኢትዮጵያ ዛሬ ላይ ተስፋፍተው፤ የወጣቱና የጎልማሳው የትውልድ ክፍለ ዘመን ፈተና ሆነው ሁሉም በየግል በየግል ከራሱ ጋር እንዲጣላና የሃይማኖት አካሄዶችን እንዲሸሽ ሰፊ ድርሻ የተጫወተ የአጥፊው ጥልቁ መልአክ አባዶን ሴራ ነው፡፡
+++
በዘመናችን በወሲብ ፊልም ያልተጠመደ ወጣትና ጎልማሳ ማግኘት አዳጋች ይሆናል፡፡ በተለይ የእጅ ስልክ በየግል በየግል አብዛኞቻችን እንደ መታወቂያ ካርድ ይዘነው የምንዞረው መለያችን ከመሆኑም ጋር ተያይዞ በቀላሉ የተለያዩ ድረገጾችን የማግኘት አጋጣሚዎች(Internet accessibility) በመኖሩ ሰዎች ሳይቸገሩ ወደ ወሲብ ፊልም ቁራኛነት በመግባት ለመውጣት ግን ተቸግረው ይስተዋላሉ፡፡
+++
የወሲብ ፊልም ሱሰኝነት በአገራችንና በዓለም አቀፍ ደረጃ ስነልቦናዊ፣ አካላዊና ማኅበራዊ ሰፊ ቀውሶችን በወጣቱ ትውልድ ላይ ለማድረስ ሆን ተብሎ በአጥፊ መናፍስቶችና የክፋት መሣሪያ በሆኑ ሰዎች የተቀናበረ የወጥመድ መረብ ሲሆን፤ ግቡንም አሳክቶ ልክ እንደ ወረርሺኝ በብዙ አገራት በመዝለቅ ሁለንተናዊ እና ዘርፈ ብዙ ቀውሶችን ከዘመን ዘመን በሚጋሽበው ትውልድ ላይ በጥልቅ መሠረት ለማስከተል ችሏል፡፡ ስለዚህም ነገር የዮሐንስ ራእይ ምን ይላል የሚለውን እንመልከት፡፡
(የዮሐንስ ራእይ ምዕ. 17)
---
3፤ በመንፈስም ወደ በረሀ ወሰደኝ፤ የስድብም ስሞች በሞሉበት፥ ሰባት ራሶችና አሥር ቀንዶችም ባሉበት በቀይ አውሬ ላይ አንዲት ሴት ተቀምጣ አየሁ።
4፤ ሴቲቱም በቀይና በሐምራዊ ልብስ ተጐናጽፋ በወርቅና በከበሩ ድንጋዮች በዕንቈችም ተሸልማ ነበር፥ በእጅዋም የሚያስጸይፍ ነገር የዝሙትዋም ርኵሰት የሞላባትን የወርቅ ጽዋ ያዘች፤
5፤ በግምባርዋም ምስጢር የሆነ ስም። ታላቂቱ ባቢሎን፥ የጋለሞታዎችና የምድር ርኵሰት እናት ተብሎ ተጻፈ።
በሴት ጾታ የተገለጸው ይህ የጥልቁ መንፈስ፤ ትውልዱን በተብለጨለጨ የዘመን ውበትና መሣሪያ አነሁልሎ፤ ዜጎች ከእግዚአብሔር አምላክ ጋር የሚኖራቸውን የቅደስና ሕይወት በመቀንጠስ፤ በታላቅ የዝሙት ማዕበል እንዲንሳፈፉ ያደረገ የጥልቁ አለቃ የአባዶን መንፈስ ምሪት ነው፡፡
ዛሬ ሲሆን የምናየው ሁሉ ምንድነው? ለምን ትውልዱ በወሲብ ግለት ነደደ? ለምን በመዝናኛው ኢንደስትሪ በኩል የሚቀርቡት ጽሑፎች፣ ዘፈኖች እና ፊልሞች ላይ የወሲብ ድርጊቶችና የራቁትነት ገጽታዎች እጅግ በዙ? ዕድሜና የአገራትን ባሕል ሳይመርጡ ለሕዝብ ያለ ማቋረጥ የሚተላለፉ የሚዲያ ውጤቶች በብዛት የዝሙት ምኞትን የሚጠሩ ስለምን ሆኑ? ለምን የአስገድዶ መድፈር ዜናዎች፣ የጽንስ ማስወረድ ድርጊቶች፣ የእርግዝና መቆጣጠሪያና ማዘግያ ዘዴዎች ከመጠን በላይ እየጨመሩ ሄዱ?
ምክንያቱም አበለጭልጫ በሐምራዊ ልብስ ተጋጊጣ የተገለጸቺው የዝሙት መንፈስ፤ የመጨረሻው ዘመነ ጊዜዋ ሆኖላታልና የሠራዊቶቿን የርኩሰት ጽዋ በዓለም ላይ ስላፈሰሰቺው ነው፡፡
+++
የወሲብ ፊልሞች ሱስ ልክ እንደ ትምባሆ፣ አልኮልና አደንዛዥ ዕፆች ሱስ ከያዘ በቀላሉ የማይለቅ፤ ቀስ በቀስ በመቆራኘትም መላ የኑሮ አቅጣጫንና የውስጥ ሕይወትን መንገድ ወደ አንድ መስመር በመሳብ፤ የኢንተርኔትና ራስን በራስ የማርካት(ግለ-ሩካቤ) ተጠማጅ የሚያድርግ ያልተነገረለት እጅግ አደገኛ የመናፍስት ማፍዘዣ ነው፡፡ የወሲብ ፊልሞችን የመመልከት ልምምዱ ቀስ በቀስ እያደገና እንደ ግል ጠባይ እየጎለበተ የዘወትር እህል ውኃ የሚሆን መላ የስሜት ሕዋስን በዝግታ እየተቆጣጠረ የሚመጣ የአእምሮ ማስከሪያ ነው፡፡ ዝሙታዊ ፊልሞችን ለመመልከት ቀላል፤ ከማየት ለመራቅ ግን ፈታኝ የሆነበት አንደኛው መሠረታዊ ምክንያት የመናፍስት ሰንሰለትና ሰይጣናዊ እገዛ ያለበት ከመሆኑ ጋር በተያያዘ፤ ግለሰቦች ከሱሱ ለመላቀቅ ብለው! ብለው! ሲሰለቻቸው፤ 'በራሱ ጊዜ ይተወኛል' እያሉ ተስፋ በማሳጣት እንዲኖሩ እያደረገ ነገን አጨልሞ ዛሬን በቁራኝነት የሚዋረስ አደንዣዥ ወረርሺኝም ነው፡፡
+++
<< ቁራኛነት >> ከርኩሳን መናፍስት ጋር በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ የሚያያዝ የጥፋት አሠራር አለው፡፡ ይህንን ጥቂት የማይባሉ ሰዎች ስለማይገነዘቡ፤ በሥጋዊ መፍትሔዎች ብቻ ተጉዘው ከጥገኝነት ችግር ለመላቀቅ በተደጋጋሚ ሲጥሩ ለጥቂት ቀናት አሊያ ሳምንታት ተሳክቶላቸው መፍትሔ ቢያገኙም፤ ዞሮ ዞሮ ወደ ተዘፈቁበት ማጥ እየወደቁ ተስፋ በመቁረጥም እንደ ልማድና አንድ የኑሮ አካል አስተናግደውት ዝም ብለው ተቀምጠዋል፡፡ ዘመናዊ ነው በሚባል በዚህኛው ትውልድም፤ ግለ-ወሲብ እንደ አንድ የሥልጣኔ ክፍል ተቆጥሮ በየትምህርት ቤቱና መሥሪያ ቤቱ ቀልድና ስላቅ እየተበጀለት፤ በውስጥ ግን እየተለቀሰለት ያለ የብዙዎች ድምፅ አልባ ዋይታ እንዲሆን የአንበሳውን ድርሻ የተጫወተው የወሲብ ፊልም ቁራኝነት ሲሆን ወጣቶች በጋራ ሲጨዋወቱ የሚስቁበት፤ በየግል በየግል ግን የሚያለቅሱበትና ራሳቸውን የሚጠሉበት አዚማዊ ጠባይ ያለው የውስጥ ድንዛዜንና ግዴየለሽነትን የሚያሰራጭ የርኩሳን መናፍስት የግብር ጭዳ የሚያደርግ የጓዳ የሚመስል የዓለም በሽታ ነው፡፡
+++
ህቡዕ ሰይጣናዊ ድርጅቶች እንደ ኢሉሚናቲ፣ ዘ ናይት ቴምፕላርስ እና ፍሬመሰንስ ያሉት አጥፊዎች፥ ቀድመው ከጠለፉት የሴራ ድርጊቶችና የትውልድ ማደንዣዎች መካከል በሰፊ ጥናትና ዘመናትን በፈጀ የሴራ ቅንብር የተተገበረው የወሲብ ፊልም የጠምዛዥነት እቅድ(project)፤ ከፍተኛና ዓለም አቀፋዊ በጀት ተበጅቶለት፤ ዛሬ ላይ ሰለጠኑ በሚባሉ አገራት ላይ ራሱን የቻለ የመዝናኛ ማዕከል(Film industry) ሆኖ፤ ገና ከማለዳው ወጣቱን እያሰረና እያጨነገፈ፤ ከታለመለት እቅደ-ንድፍም አሻግሮ በመዝለቅ ጎልማሳና በዕድሜ የገፉ ባለትዳር የልጆች ወላጅ የሆኑ ሰዎችን ጭምር ሱሰኛ አድርጎ ያስቀመጠ ሲሆን፤ መፍትሔው ተሸፋፍኖ ያስከተለው ኪሣራ ግን የተገለጠ ደንበኛ የዲያቢሎስ ቀኝ እጅ ለመሆን ችሏል፡፡
ከኢንተርኔት ድረገጾችም ውስጥ ከ50% በላይ ሽፋን ያላቸው እነዚህ የፍትወት ፊልሞች፣ ምስሎችና ድምፆች፤ ከየትኛውም በኢንተርኔት በኩል ከሚኖሩ ድረገጾች የበለጠ ተከታታይ ቋሚ ተጠቃሚ ሰዎች እያፈሩ መሆኑን ስንመለከት፤ የአጥፊው አባዶን ሠራዊት ትውልድን የማደንዘዙ ተልዕኮ ምን ያህል ዘመናትንና ትውልዶቻቸውን አንድ'ጋ ሰብስቦ የማሰር አሠራሩን በተሳካ መልኩ ማከናወን እንደቻለ እንገነዘባለን፡፡
እንደ አሜርካ ባሉ አገራት እንደ አንድ የመዝናኛው ዘርፍ አውድና ይዘት ተቆጥሮ የልቅ ወሲብ ተዋናዮችን በመመልመልና በዓለምም ፊት በመሸለም የሥራ ዘርፍ አስመስሎ እንደ ማኅብረሰባዊ ልማዶች ለማስቆጠር በተደረገው የተጋድሎ ጥረት በኩልም የተለመደና የዘመን ለውጥ አንዱ ክፍል እንደሆነ በዘዴ ለማሳሰብና በሰው ልጆች ልቦና ላይ እንዲታተም ለማስገደድ በሙዚቃውና በፊልሙ ኢንደስትሪ አማካኝነት መጠነ ሰፊ ፕሮፖ-ጋንዳ ተሠርቶለትና ሕሊናን የመቆጣጠሪያ ቴክኒክ ተቀርጾለት በየቀኑ የሚሰራጭ በመሆኑ ከላይ ከባለሥልጣናት አንስቶ እስከ ታች ያሉ የሕብረተረሰብ ክፍላትን ጨምድዶ የያዘ አይነተኛ ልክፍት እንዲሆን በቀላሉ በእጅ ስልክና በላፕቶፕ ኮምፒውተሮች የመገኘት አቅሙን በማስፋት የአየር ሞገድ ምኅዋሩን በመቆጣጠር የሄዱበት ሚስጢራዊና መናፍስታዊ አካሄድ እጅግ የበዙ የሰው ልጆችን በአጭርና በተመሳሳይ መልኩ በማጨንገፍ ተሳክቶላቸዋል፡፡
ከላይ የቀጠለ .....
.....ርኩስ መንፈሶች የሰውን ልጅ ትውልድ ሕይወት ወደ ረከሰውና በኃጢአት ወደተጨማለቀው ለመለወጥ በተለያዩ መንገዶች በሥጋዊ ድክመቱ በመዝለቅ መንፈሳዊ ሕልውናውን ለዘመናት ተፈታትነውታል፡፡ ለአዳምና ለሔዋን የተሰጣቸው የበረከትና የጸጋ ማኅተም ውስጥ የተሰጠንን ታላቅ ረድኤተ-ቡራኬ ስጦታን ቀልብሰው ሥጋን በማርከስ እግዚአብሔር የተቀደሰበትና ስሙ የተጠራበት ሰማያዊ አኗኗር ከሰውነት እና ቤታችን አርቀው ዘባተሎ ኑሮን እንድንኖር የጽልመት መልአክት ይፋለሙናል፡፡ በመሆኑም አመንዝራነትና ሴሰኝነት ብዙዎቻችን ከማይታዩ ተጽዕኖዋቸው ግን ከሚታይ ርኩሳን መናፍስት የኃጢአት ግብር አስፈጻሚነት ጋር የሚገናኝ ሳይሆን ሰዎች በሞራላዊ የሥነ-ምግባር መዛነፍና መበላሸት ወይም በዘመኑ አመጣጥ የሚላከክ የአጉል ዘመናዊነት ጊዜ የመዝቀጥ ውጤት ብቻ አድርገነው ፈዘን ተቀምጠናል፡፡
+++
በተሰወሩ የመናፍስት ወጥመድ ሥር የመግባት አንደኛው ገጽታ፤ በወሲብ ፊልሞችና ምስሎች የመለከፍ እድል ውስጥ ለመገኘት፤ በአንዳንዶች ላይ ልክ እንደተፈጥሮ አጋጣሚ የተለመደ ሁነት አስመስሎ በሕሊና ውስጥ አሊያ በሌሎች ሰዎች ግፊት እያሳመነ እንዲመለከቱት በማለማመድ እንደ ሱስ እንዲቆራኛቸው የአእምሮ ወሳኝነትን ይቆጣጠራል፡፡ አንዴ እንዲመለከቱት አጋጣሚና ሁኔታው ከተመቻቸ፤ መናፍስቱ ከውስጥም ከውጪም ሆነው በመዋረስ፤ የሰው ልጆች ከተፈጥሮና ከእምነትም ምግባር የወጣ የጋጠወጥነትና የእንስሳት ጠባይ የሚንጸባረቅበት አረማዊ ምግባር እንደሆነ በልቦና ቢረዱም፤ በፍትወት እያቃጠለ በስሜት እንዲነዱ ሕሊናን እየተጫነ እንዲለከፉበት ያስገድዳል፡፡ በዚህ ጉዞ ውስጥም ሦስት ደረጃዎችን ያሳልፋሉ፦
➊• በምናብ ውስጥ የሚያውቁትን ወይም የማያውቁትን ሰው ምስል እየሳለ የወሲብ ስሜትን ይቀሰቅስባቸዋል፡፡ ወይም ከዚህ በፊት ያዩትን የወሲብ ፊልም ደግሞ ከውስጥ ያሳያቸዋል፡፡
➋• ከሕሊና ውስጥ ሆኖ እንደግል አሳብ እያስመሰለ ልብ ላይ የሱሰኝነቱን አዚማዊ ኃይል ስለሚጽፈው፤ ውስጣዊ ውጊያውን በተፈጥሮ ስሜት ወስዋሽነት በኩል ገፋፍቶ ገፋፍቶ በመጨረሻም እንዲመለከቱ ያደርጋቸዋል፡፡
➌• ተመልክተው ራሳቸውን በማርካትም ሲጨርሱ ወደ ልቦናቸው በመመለስ 'ምን ነካኝ' እያሉ በራሳቸው እንዲበሳጩና እንዲሸማቀቁ እያደረገ ከውስጥ ኃጢአተኛ እንደሆኑ እየደሰኮረ ከእግዚአብሔር እንዲርቁ መንገዶችን ያመቻቻል፡፡
+++
✞ መናፍስት እንዴት በወሲብ ፊልም በኩል ይዋረሳሉ? ✞
1) ቡዳ በመሆን
ከላይ ለመግለጽ እንደምከርኩት የወሲብ ፊልሞች የጀርባ አጥንት የሆኑት መናፍስታዊ ድርጅቶች የጥፋት መናፍስቱን ለራሳቸው የተንኮል ሥራና የአመፃ ስልት ስለሚጠቀሙባቸው፤ ከኖህ ዘመን አንስቶ የነበሩት ልቡሳነ ሥጋ መናፍስት-የኔፍሊም ሠራዊት ዳግም ከጥፋት ውኃ በኋላ በድጋሚ ወደ ሰው ልጆች ትውልድ ዘልቀው የሚገቡበትን ዕድል ስላገኙ እነዚህንና የዝሙት መናፍስት እንደ ሩሃንያ አባድ የሚባሉ የጽልመት መልአክትን በግብርና በተለያየ ጭዳ በመሳብ፤ በጥንቃቄ እንደ መደበኛ ፊልም ድርሰት አዘጋጅተው በሚለቁት የወሲብ ፊልምና ምስሎች ውስጥ መናፍስቱን አዚማዊ ቡዳ እንዲሆኑ ያደርጓቸዋል፡፡ በዓይን በመመልከት ብቻ በቀጥታ ውስጣዊ ሕይወትን እንዲቆጣጠሩም ተደርገው ስለሚላኩ፤ መናፍስቱ ቡዳ በመሆን የወሲብ ፊልሙን የሚያየውን ሰው ከውጪ ወደ ውስጡ ይመለከቱታል፡፡ እነዚህ ርኩሳን መናፍስት የሰው ልጆችን ሕይወት ለመያዝና በዝግታ ለመቆጣጠር የሚፈልጉት አንድ ፊልም አሊያም ምስል ብቻ ሊሆን ይችላል፡፡ በዚህም ምክንያት ዛሬ ላይ ብዙ ሰዎች በመጀመሪያ የወሲብ ምስሎችን ያዩበት ቀንን እስከተገኙበት ዕለተ ቀናቸው እየረገሙና እየተበሳጩ መፍትሔ ባጣ አኗኗር እየዋተቱ ታስረው ታስረው ተቀምጠዋል፡፡
2) ቀድሞ ውስጥ ባለ መንፈስ አዚም በመሆን
ከውስጥ ያደፈጠ ማንኛውም አይነት ርኩስ ኃይል ሲገኝ፤ ከውጪ በምናስገባው መረጃ መሠረት ላይ እየተመረኮዘ፤ የማጥፋትና ወደ መሰነካኪያው ጎዳና የሚመራ ዘዴንና ስልትን በጥንቃቄ እየቀየሰ፤ ግዜያቸው፣ ኑሮአቸው፣ ሕሊናቸው፣ እፎይታቸው የሚያለቅስ ሰዎችን እየጨመረ፤ ወደ ተስፋ ማጣትና የብስጭት አኗኗር ከማማረር ሕይወት ጋር እያንደረደረ ለስቃይና ለመከራ የተፈጠርን እስክንመስል ድረስ ይፈትነናል፡፡፡
አንደኛው ከውጪ ወደ ውስጥ የምናስገባው መረጃ ታዲያ፥ ፊልም፣ ሙዚቃ፣ ጽሑፍ፣ ንግግርና የመሳሰሉትን ነው፡፡ እነዚህ መረጃዎች ለኃጢአት ግብር መንስኤ መሆን የሚችሉ ከሆነ ያደፈጠው ጠላት ይጠቀምባቸዋል፡፡ ግለ ሩካቤ ሥጋንም እንድንወድቅበት የሚያደርጉት መንሸራተቻዎች እነዚሁ የወሲብ ፊልሞች፣ ሙዚቃዎች፣ ጽሑፎችና መሰል መረጃዎች ናቸው፡፡
ከሠለጠኑ አገራት በከፍተኛ ግፊትና ፍጥነት እየተንሰራፋ የመጣው የወሲብ ፊልሞችና መልእክቶች ዛሬ በአብዛኛው ወጣቶች ሥልክ ውስጥ ተስግስገው፤ እንደ አንድ የእውቀትና የመዝናኛ ክፍል በመታየት የስሜት ማብረጃ እየሆኑ ውስጣዊ ማንነታችንን እየበሉት፤ በውጪ ግን እየሳቅንና እየተጫወትን የምናስመስል ፍጥረቶች ሲያደርጉን ማስተዋል ተሳነን፡፡ የሚገርመው፥ ባለትዳሮች፣ አዛውንታንና በዕድሜ ያልደረሱ ትንንሽ ልጆችንም የሚለክፈው የወሲብ ፊልም ቁራኝነት፤ እነርሱም የእነዚህ የፈረንጅ አተላ የወሲብ ግብአቶችን እንደ ሕይወታቸው አንድ የተለመደ ክፍል ይዘውት በድብቅ ይጠቀሙበታል፡፡
አሁን እነዚህን ፊልሞችና መሰል መረጃዎች የምታይ ከሆነ፤ ከውስጥም ያለው ጠላት በምታየው ነገር ልክ የምትጠፋበትንና ቁራኛ የምትሆንበትን ችግር ይቀርጽለሃል፡፡ ኦሪት ዘዳግም 28፥
34 ላይ " ዓይኖችህም ከሚያዩት የተነሣ ዕብድ ትሆናለህ።" ይላል፡፡ ምን ከምትለው የተነሣ? ዓይኖችህ ከሚያዩት የተነሣ፡፡ በእውነትም ታዲያ ከምታየው የወሲብ ፊልሞችና ምስሎች የተነሣ፤ ከራስህ ጋር እየተጣላህ በግለኝነት ጸብ የምትማስን የውስጥ ዕብድ ሆነህ ትገኛለህ፡፡
3) የሚዘዋወሩ መናፍስት አጋጣሚውን ይጠቀማሉ
መጽሐፍ ቅዱስ በጴጥሮስ መልእክት በኩል << ዲያቢሎስ የሚውጠውን ፈልጎ እንደሚያገሣ አንበሳ በዙሪያችሁ ይዞራል >> በማለት ከባቢያችን ላይ የሚያንዣብቡ ጠላቶች እንዳሉ ቁልጭ ባለ ቃል አስቀምጦልናል፡፡ ከሩቅ ያያችኋል አይደለም የሚለው፡፡ በዙሪያችሁ ይዞራል ነው የሚለው፡፡ እነዚህ የሚያንዣብቡ መናፍስት የወሲብ ፊልሞችንና ምስሎችን በምንመለከትበት ጊዜ ወደኛ ለመምጣት በር ያገኛሉ፡፡ ምን ማለት ነው ለምሳሌ አበባ ንብን እንደሚጠራ ሁሉ ዝንብ ቆሻሻ ይስባታል፤ እንዲሁ የኃጢአት ልምምዶችና የአመፃ ድርጊቶች በአየር የሚዘዋወሩትን መናፍሰት እይታ ስለሚስብ፤ ክፉውንና የረከሰውን ምግባር በምናደርግበት ቅጽበት ውስጥ መናፍስቱ ወደ ሕይወታችን ሊገቡ የሚችሉበትን ዕድል ያገኛሉ፡፡ ወደ ባሕሪያችን ሲቀላቀሉም መጀመሪያ ሲገቡ የተጠቀሙበትን የርኩሰት ምግባር ግብር አድርገው ስለሚቆጥሩት፤ በርኩሰት ልምምድ ውስጥ እንድንቀር ግብራቸውን ከውስጥ ሆነው በግፊትና በከፍተኛ ጫና በየጊዜው በተደጋጋሚ በመጠየቅ ከእስራታቸው እንዳንወጣ በተጽዕኖ ኃይል እጅጉን ይታገላሉ፡፡
+++
በጥልቀትና ከእግዚአብሔር አምላክ የእውነት ቃል ጋር በማያያዝ በቀጣይ በሚኖሩኝ ተከታታይ ስድስት ክፍሎች የምዳስሰውን የሚከተሉት ርዕሶች ይዤ እመለሳለሁ፡፡
➊• የወሲብ ፊልምና የስነልቦና ጉዳቱ
➋• የወሲብ ፊልም የቱን ያህል በዘመኑ ፋሽን ዘልቆ ሄደ?
➌• የወሲብ ፊልምና የመዝናኛው ኢንደስትሪ ተያያዥነት
➍• የወሲብ ፊልምና ከእምነት መሸሽ
➎• የወሲብ ፊልም ለአስገድዶ መድፈር ያለው ተጽዕኖ
➏• ከወሲብ ፊልም ጥገኝነት
.....ርኩስ መንፈሶች የሰውን ልጅ ትውልድ ሕይወት ወደ ረከሰውና በኃጢአት ወደተጨማለቀው ለመለወጥ በተለያዩ መንገዶች በሥጋዊ ድክመቱ በመዝለቅ መንፈሳዊ ሕልውናውን ለዘመናት ተፈታትነውታል፡፡ ለአዳምና ለሔዋን የተሰጣቸው የበረከትና የጸጋ ማኅተም ውስጥ የተሰጠንን ታላቅ ረድኤተ-ቡራኬ ስጦታን ቀልብሰው ሥጋን በማርከስ እግዚአብሔር የተቀደሰበትና ስሙ የተጠራበት ሰማያዊ አኗኗር ከሰውነት እና ቤታችን አርቀው ዘባተሎ ኑሮን እንድንኖር የጽልመት መልአክት ይፋለሙናል፡፡ በመሆኑም አመንዝራነትና ሴሰኝነት ብዙዎቻችን ከማይታዩ ተጽዕኖዋቸው ግን ከሚታይ ርኩሳን መናፍስት የኃጢአት ግብር አስፈጻሚነት ጋር የሚገናኝ ሳይሆን ሰዎች በሞራላዊ የሥነ-ምግባር መዛነፍና መበላሸት ወይም በዘመኑ አመጣጥ የሚላከክ የአጉል ዘመናዊነት ጊዜ የመዝቀጥ ውጤት ብቻ አድርገነው ፈዘን ተቀምጠናል፡፡
+++
በተሰወሩ የመናፍስት ወጥመድ ሥር የመግባት አንደኛው ገጽታ፤ በወሲብ ፊልሞችና ምስሎች የመለከፍ እድል ውስጥ ለመገኘት፤ በአንዳንዶች ላይ ልክ እንደተፈጥሮ አጋጣሚ የተለመደ ሁነት አስመስሎ በሕሊና ውስጥ አሊያ በሌሎች ሰዎች ግፊት እያሳመነ እንዲመለከቱት በማለማመድ እንደ ሱስ እንዲቆራኛቸው የአእምሮ ወሳኝነትን ይቆጣጠራል፡፡ አንዴ እንዲመለከቱት አጋጣሚና ሁኔታው ከተመቻቸ፤ መናፍስቱ ከውስጥም ከውጪም ሆነው በመዋረስ፤ የሰው ልጆች ከተፈጥሮና ከእምነትም ምግባር የወጣ የጋጠወጥነትና የእንስሳት ጠባይ የሚንጸባረቅበት አረማዊ ምግባር እንደሆነ በልቦና ቢረዱም፤ በፍትወት እያቃጠለ በስሜት እንዲነዱ ሕሊናን እየተጫነ እንዲለከፉበት ያስገድዳል፡፡ በዚህ ጉዞ ውስጥም ሦስት ደረጃዎችን ያሳልፋሉ፦
➊• በምናብ ውስጥ የሚያውቁትን ወይም የማያውቁትን ሰው ምስል እየሳለ የወሲብ ስሜትን ይቀሰቅስባቸዋል፡፡ ወይም ከዚህ በፊት ያዩትን የወሲብ ፊልም ደግሞ ከውስጥ ያሳያቸዋል፡፡
➋• ከሕሊና ውስጥ ሆኖ እንደግል አሳብ እያስመሰለ ልብ ላይ የሱሰኝነቱን አዚማዊ ኃይል ስለሚጽፈው፤ ውስጣዊ ውጊያውን በተፈጥሮ ስሜት ወስዋሽነት በኩል ገፋፍቶ ገፋፍቶ በመጨረሻም እንዲመለከቱ ያደርጋቸዋል፡፡
➌• ተመልክተው ራሳቸውን በማርካትም ሲጨርሱ ወደ ልቦናቸው በመመለስ 'ምን ነካኝ' እያሉ በራሳቸው እንዲበሳጩና እንዲሸማቀቁ እያደረገ ከውስጥ ኃጢአተኛ እንደሆኑ እየደሰኮረ ከእግዚአብሔር እንዲርቁ መንገዶችን ያመቻቻል፡፡
+++
✞ መናፍስት እንዴት በወሲብ ፊልም በኩል ይዋረሳሉ? ✞
1) ቡዳ በመሆን
ከላይ ለመግለጽ እንደምከርኩት የወሲብ ፊልሞች የጀርባ አጥንት የሆኑት መናፍስታዊ ድርጅቶች የጥፋት መናፍስቱን ለራሳቸው የተንኮል ሥራና የአመፃ ስልት ስለሚጠቀሙባቸው፤ ከኖህ ዘመን አንስቶ የነበሩት ልቡሳነ ሥጋ መናፍስት-የኔፍሊም ሠራዊት ዳግም ከጥፋት ውኃ በኋላ በድጋሚ ወደ ሰው ልጆች ትውልድ ዘልቀው የሚገቡበትን ዕድል ስላገኙ እነዚህንና የዝሙት መናፍስት እንደ ሩሃንያ አባድ የሚባሉ የጽልመት መልአክትን በግብርና በተለያየ ጭዳ በመሳብ፤ በጥንቃቄ እንደ መደበኛ ፊልም ድርሰት አዘጋጅተው በሚለቁት የወሲብ ፊልምና ምስሎች ውስጥ መናፍስቱን አዚማዊ ቡዳ እንዲሆኑ ያደርጓቸዋል፡፡ በዓይን በመመልከት ብቻ በቀጥታ ውስጣዊ ሕይወትን እንዲቆጣጠሩም ተደርገው ስለሚላኩ፤ መናፍስቱ ቡዳ በመሆን የወሲብ ፊልሙን የሚያየውን ሰው ከውጪ ወደ ውስጡ ይመለከቱታል፡፡ እነዚህ ርኩሳን መናፍስት የሰው ልጆችን ሕይወት ለመያዝና በዝግታ ለመቆጣጠር የሚፈልጉት አንድ ፊልም አሊያም ምስል ብቻ ሊሆን ይችላል፡፡ በዚህም ምክንያት ዛሬ ላይ ብዙ ሰዎች በመጀመሪያ የወሲብ ምስሎችን ያዩበት ቀንን እስከተገኙበት ዕለተ ቀናቸው እየረገሙና እየተበሳጩ መፍትሔ ባጣ አኗኗር እየዋተቱ ታስረው ታስረው ተቀምጠዋል፡፡
2) ቀድሞ ውስጥ ባለ መንፈስ አዚም በመሆን
ከውስጥ ያደፈጠ ማንኛውም አይነት ርኩስ ኃይል ሲገኝ፤ ከውጪ በምናስገባው መረጃ መሠረት ላይ እየተመረኮዘ፤ የማጥፋትና ወደ መሰነካኪያው ጎዳና የሚመራ ዘዴንና ስልትን በጥንቃቄ እየቀየሰ፤ ግዜያቸው፣ ኑሮአቸው፣ ሕሊናቸው፣ እፎይታቸው የሚያለቅስ ሰዎችን እየጨመረ፤ ወደ ተስፋ ማጣትና የብስጭት አኗኗር ከማማረር ሕይወት ጋር እያንደረደረ ለስቃይና ለመከራ የተፈጠርን እስክንመስል ድረስ ይፈትነናል፡፡፡
አንደኛው ከውጪ ወደ ውስጥ የምናስገባው መረጃ ታዲያ፥ ፊልም፣ ሙዚቃ፣ ጽሑፍ፣ ንግግርና የመሳሰሉትን ነው፡፡ እነዚህ መረጃዎች ለኃጢአት ግብር መንስኤ መሆን የሚችሉ ከሆነ ያደፈጠው ጠላት ይጠቀምባቸዋል፡፡ ግለ ሩካቤ ሥጋንም እንድንወድቅበት የሚያደርጉት መንሸራተቻዎች እነዚሁ የወሲብ ፊልሞች፣ ሙዚቃዎች፣ ጽሑፎችና መሰል መረጃዎች ናቸው፡፡
ከሠለጠኑ አገራት በከፍተኛ ግፊትና ፍጥነት እየተንሰራፋ የመጣው የወሲብ ፊልሞችና መልእክቶች ዛሬ በአብዛኛው ወጣቶች ሥልክ ውስጥ ተስግስገው፤ እንደ አንድ የእውቀትና የመዝናኛ ክፍል በመታየት የስሜት ማብረጃ እየሆኑ ውስጣዊ ማንነታችንን እየበሉት፤ በውጪ ግን እየሳቅንና እየተጫወትን የምናስመስል ፍጥረቶች ሲያደርጉን ማስተዋል ተሳነን፡፡ የሚገርመው፥ ባለትዳሮች፣ አዛውንታንና በዕድሜ ያልደረሱ ትንንሽ ልጆችንም የሚለክፈው የወሲብ ፊልም ቁራኝነት፤ እነርሱም የእነዚህ የፈረንጅ አተላ የወሲብ ግብአቶችን እንደ ሕይወታቸው አንድ የተለመደ ክፍል ይዘውት በድብቅ ይጠቀሙበታል፡፡
አሁን እነዚህን ፊልሞችና መሰል መረጃዎች የምታይ ከሆነ፤ ከውስጥም ያለው ጠላት በምታየው ነገር ልክ የምትጠፋበትንና ቁራኛ የምትሆንበትን ችግር ይቀርጽለሃል፡፡ ኦሪት ዘዳግም 28፥
34 ላይ " ዓይኖችህም ከሚያዩት የተነሣ ዕብድ ትሆናለህ።" ይላል፡፡ ምን ከምትለው የተነሣ? ዓይኖችህ ከሚያዩት የተነሣ፡፡ በእውነትም ታዲያ ከምታየው የወሲብ ፊልሞችና ምስሎች የተነሣ፤ ከራስህ ጋር እየተጣላህ በግለኝነት ጸብ የምትማስን የውስጥ ዕብድ ሆነህ ትገኛለህ፡፡
3) የሚዘዋወሩ መናፍስት አጋጣሚውን ይጠቀማሉ
መጽሐፍ ቅዱስ በጴጥሮስ መልእክት በኩል << ዲያቢሎስ የሚውጠውን ፈልጎ እንደሚያገሣ አንበሳ በዙሪያችሁ ይዞራል >> በማለት ከባቢያችን ላይ የሚያንዣብቡ ጠላቶች እንዳሉ ቁልጭ ባለ ቃል አስቀምጦልናል፡፡ ከሩቅ ያያችኋል አይደለም የሚለው፡፡ በዙሪያችሁ ይዞራል ነው የሚለው፡፡ እነዚህ የሚያንዣብቡ መናፍስት የወሲብ ፊልሞችንና ምስሎችን በምንመለከትበት ጊዜ ወደኛ ለመምጣት በር ያገኛሉ፡፡ ምን ማለት ነው ለምሳሌ አበባ ንብን እንደሚጠራ ሁሉ ዝንብ ቆሻሻ ይስባታል፤ እንዲሁ የኃጢአት ልምምዶችና የአመፃ ድርጊቶች በአየር የሚዘዋወሩትን መናፍሰት እይታ ስለሚስብ፤ ክፉውንና የረከሰውን ምግባር በምናደርግበት ቅጽበት ውስጥ መናፍስቱ ወደ ሕይወታችን ሊገቡ የሚችሉበትን ዕድል ያገኛሉ፡፡ ወደ ባሕሪያችን ሲቀላቀሉም መጀመሪያ ሲገቡ የተጠቀሙበትን የርኩሰት ምግባር ግብር አድርገው ስለሚቆጥሩት፤ በርኩሰት ልምምድ ውስጥ እንድንቀር ግብራቸውን ከውስጥ ሆነው በግፊትና በከፍተኛ ጫና በየጊዜው በተደጋጋሚ በመጠየቅ ከእስራታቸው እንዳንወጣ በተጽዕኖ ኃይል እጅጉን ይታገላሉ፡፡
+++
በጥልቀትና ከእግዚአብሔር አምላክ የእውነት ቃል ጋር በማያያዝ በቀጣይ በሚኖሩኝ ተከታታይ ስድስት ክፍሎች የምዳስሰውን የሚከተሉት ርዕሶች ይዤ እመለሳለሁ፡፡
➊• የወሲብ ፊልምና የስነልቦና ጉዳቱ
➋• የወሲብ ፊልም የቱን ያህል በዘመኑ ፋሽን ዘልቆ ሄደ?
➌• የወሲብ ፊልምና የመዝናኛው ኢንደስትሪ ተያያዥነት
➍• የወሲብ ፊልምና ከእምነት መሸሽ
➎• የወሲብ ፊልም ለአስገድዶ መድፈር ያለው ተጽዕኖ
➏• ከወሲብ ፊልም ጥገኝነት
✞ የወሲብ ፊልምና ጠንቆቻቸው ✞
ክፍል - 3
በስመ አብ፥ ወወልድ፥ ወመንፈስ ቅዱስ፥ አሐዱ አምላክ፥ አሜን፡፡
✞ የወሲብ ፊልም የቱን ያህል በዘመኑ ፋሽን ዘልቆ ሄደ? ✞
የዝሙት ፊልሞችና ምስሎች በዓለም አህጉራት በከፍተኛ ደረጃ የመሰራጨታቸው ሚስጢር ከጀርባው በተቀናጀ አደረጃጀትና ህቡዕ በሆነ አካሄድ ውስጥ የተሰለፉ የሚስጢር ማኅበራት ተጽዕኖ እና አቅም አማካኝነት ነው፡፡ አብዛኛው የወጣቱ ትውልድም በቀላሉ በሚያገኘው የእጅ ስልኮቹና የመገናኛ አውታሮች በኩል የሚለቀቁት እነዚህ የርኩሳን መናፍስት አዚማዊ መሣሪያ የሚሆኑ ፊልሞች፤ ወደኑሮና ልማድ የመቀላቀል ፍጥነታቸው ከፍተኛ የሆነ ሲሆን ያለ ውጣ ውረድና ተጨማሪ ጉልበት የተፈጥሮ ስሜት ላይ በመመርኮዝ የአእምሮ ክፍልን ተቆጣጥሮ በፍላጎት ስሜት አነሁልሎ በማደንዘዝ ወደ ልክፍት የሚመራ ስውር የማይነገርለት ጠፍናጊ ሱስ የመሆን ባሕሪይ ያለው የክፍለ ዘመናችን ማፍዠዣና ትውልድን ማሰሪያ ወጥመድ ነው፡፡
+++
ፊልሞቹ በጥንቃቄ ታቅደው ሲዘጋጁ ከኋላቸው እንዲያሳኳቸው የተቀመጡላቸው መናፍስታዊ ራእይና ግብ አላቸው፡፡ ከነዚያም መካከል ትውልዱ በሚከተላቸው የፋሽን፣ የአለባበስ፣ የመዝናኛ እና ሌሎች ዘርፎች በኩል ተዘዋዋሪ የሚመስል ነገር ግን በቀጥታ የተቆራኘ ዲያቢሎሳዊ ስብከቶችንና መገለጫዎችን ማስፋፋት አንደኛው ሲሆን፤ በእውነትም ታዲያ በዚህ በኩል ያለውን ግፊትና ያመጣውን ግልጽ ጫና ከትውልዳችንና ዘመኑ ጋር አሰናስለን ስንመለከተው በእጅጉ ተሳክቶላቸው በድሉም ከፍተኛ እርካታንና ድል አድራጊነት የሚያመጣላቸውን ስራ እንደፈጸሙ ማገናዘብ እንችላለን፡፡
+++
እነዚህ የዝሙት ኢንደስትሪዎች ጥፋት አድራሽነታቸውና የትውልድ ልክፍትነታቸው ገሃድ በወጣ እውነታ ያለ ማስረጃና ሰነድ አስፈላጊነት የተረጋገጠ ሲሆን፤ ነገር ግን "ተዉ" የሚላቸው ጠንካራ የመንግሥትና የግለሰቦች ተቋም እምብዛም አለመኖሩን ስናጤን፤ ከዓለም መንግሥታት ጀርባ ያሉት መናፍስታዊ መዋቅር ያላቸው ድርጅቶች ባለ ጠንካራ ሰንሰለታማ አሳሪዎቹ የሚስጢር ማኅበራት ክንድ የቱን ያህል እግዚአብሔር በረሳ ትውልድና ዘመን ላይ በርትቶ እየደቆሰ፣ እየጠመዘዘና እየገፈተረ እንዳለ መረዳት ያስችለናል፡፡ የወሲብ ፊልሞች አደገኝነት በንጽጽር ሲታይ ጥቂት የሚሆኑ ተመራማሪዎችና አጥኚዎች ጉዳቱንና ሁለ ገብ እከሉን በሰዎች ቋሚ ምስክርነት እያረጋገጡ ትምህርትና መረጃ ቢሰጡበትም፤ የወሲብ ኢንደስትሪዎቹ ከተሰራጩበት ጥልቀትና ስፋት አንፃር፤ እንዲሁ ትውልዱ ውስጥ ሥር ሰደው ካሉት የመናፍስት አገዛዝና አሠራር ምክንያት በቀላሉ ለኃጢአትና ለእርግማን አሳቦችና ድርጊቶች የመሳብ አዝማሚያው ከፍተኛ በመሆኑ፤ እዚህ ግባ የማይባል ለውጥ ሳያመጡ ቀርቶዋል፡፡
✞ የወሲብ ኢንደስትሪና የፋሽን ኢንደስትሪ ጣምራ ሂደት ✞
ከላይ በተገለጸው መልኩ እንደተቀመጠው ጉልህ የሆነና በቁጥርም የበዛ ጥናትና ምርምር ባለመካሄዱ እንጂ በዛሬው ትውልድ እውነታ ውስጥ የዝሙት ኢንደስትሪ ተቋማት የአሻራ ተጽዕኖ ያልነካካው የሕይወት ዘርፍ ፈልጎ ማግኘት የሚያዳግት ይሆናል፡፡ ከነዚህ በታላቅ ተጽዕኖ ውስጥ ውድቀው በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ የሚስጢር ማኅበራቱ ተልዕኮና እቅድ ተፈጻሚ ከሆነባቸው የትውልዱ ገጽታዎች መካከል የፋሽን ኢንደስትሪው ይጠቀሳል፡፡
+++
ዛሬ በፋሽን ኢንደስትሪው በኩል በየቀኑ እየተመረቱ የሚወጡት የልብስ ቅርጾችና ይዘቶች፣ የመዋቢያ መሳሪያዎች፣ የተለያዩ ቁሳቁሶች በአብዛኛው ራቁት ገላን የሚያበረታቱና ዝሙት ነክ እንድምታ የሚነበብባቸው ናቸው፡፡ ርጉማን መናፍስት፤ የዘመኑን ትውልድ የቀልብ አሳብ አዎንታዊ በሚመሰል ስሜት አነሁልሎ በራቁትነት ገጽታ በመሳብ፤ የፋሽንና የአለባበስ ሴሰኝነትን የሚያንጸባርቅ ፍላጎት በመፍጠር፤ በዓይን በመመልከት ብቻ የሕሊናን እምነት መስመር በማሳት፤ ውስጣዊ ዝንባሌን ከመናፍስት ትዕዛዝ በሚመነጭ ግፊት በማስቀልበስ ወሲብ ናፋቂ እንዲኮን ያደርጋሉ፡፡
ዘመናት አስቀድሞ አጭር ቀሚስና ደረት የሚገለብጥ ልብስ መልብስ በተለይ በኛ ማኅበረሰብ እሴትና እይታ መሠረት ነውር የተባለ ሲሆን፤ ዛሬ ነውሩ ረጃጅም ቀሚስ መልበስ እንደሆነ ሁሉ ከተማና ፈረንጅ ቀመስ የኑሮ ዘልማዶቻችን ውስጥ የአእምሮ መፍዘዝን በመናፍስቱ አስገዳጅነት አስቀምጠውብን ራቁትነትን እንደ ባሕል ለውጥ አጸደቅነው፤ 'እሴትን' የዘመን ያለፈ ታሪክ 'ነውርን' የዘመን ነባራዊ እውነት ለማድረግ ተገድደናል፡፡ በዚህ ጊዜ የሚመረቱትም ልብሶች በብዛት ሆነ ብለው ሙታንታ ላለመሆን ሩብ የቀራቸው ቀሚሶችና አልባሳት ላይ በጣም ያተኮሩ ስለሆኑ፤ ይህንን እንቃወማለን አሊያም አንለብስም የሚሉ ሴቶች እስኪቸገሩ ድረስ ዘመኑ እንደጠቅላላ አጋድሎ ራሱ አስገዳጅ ራሱ ፈራጅ የሆነ ትውልድን ሲያፈራ ከጀርባ ያሉት የመናፍስት ማኅበራት በእጅጉ ረክተውና በግባቸው መሳካትም ተደስተው፤ ዝሙት ዝሙት የሚሸት ኑሮን ከተለያየ አቅጣጫ ለጊዜው ሲያሠለጥኑ እኛ ቢቸገር ነንና ተራ በተራ እስከምንጨነቅ ድረስ፤ ተራ በተራ እስከምንሰቃይ ድረስ ቶሎ አይገባንም፡፡ ቢገባንም ዘመኑንና ትውልዱ እንደሆነው ለመሆን እንጂ የእምነትንና የማኅበረሰብን የእውነት ኃይል ለማስጠበቅ ሰብረን የምናልፍበት እውነቱም፣ ድፍረቱም፣ ፍላጎቱም የለንም፡፡
+++
በመናፍስታዊ ቁራኝነት ተለውሰው የሚለቀቁት የዝሙት ፊልሞችና ምስሎች በብዛት ሴቶችን እንደ ፍትወት ስሜት ማስታገሻ የቆጠሩና ተፈጥሮ ሁነታቸውንም ያከበሩ ስላይደሉ፤ ይህንኑ የመርዝ ዲያቢሎሳዊ ፕሮፖ-ጋንዳ በአልባስና በጌጣጌጥ በኩል እየለወሱት ለትውልዱ ልቦና መጋሸብና መጥፋት መንስኤ ሆነው፤ ሴት ልጆች በአጭር ቀሚስና ቁምጣ፣ ደረት በሚገለብጥ ልብስና ተክለ ሰውነትን በጉልህ በሚያሳይ ፋሽን እንዲያጌጡ የማስገደድ ያህል በስውር እየተጫኑ፤ በዚህኛው በኩል ደግሞ ይመጡና የውበት መለኪያና ደረጃ ራሳቸው ሆነው፤ ያልተራቆተች፣ ዘመኑን ያልመሰለችና ያልተጋጌጠች እንስት ከውበት መለኪያው በታች እንደሆነች፣ በተቃራኒ ጾታ ተመራጭነት ደረጃ ውስጥ ያልተካተተች፣ ኋላ ቀር እንደሆነች፣ ዘመኑን መዋጀት የተሣናትና የኢኮኖሚ ጥገኛ የሆነች እንደሆነች አድርገው በሙዚቃው፣ በፊልሙ፣ በመጽሐፍቱና በመዝናኛ ሚዲያው በኩል ይደሰኩራሉ፡፡
ገንዘብንና የሚዲያ አውታሮችን በመቆጣጠሩ ረገድ ከፍተኛ ሚና እና ኃይል ያላቸው እነዚህ የዲያቢሎስ እጆች የሆኑት ህቡዕ ድርጅቶች፤ የተራቆተ ልብስና ዘመኑን የሚመስል ልብስ ለመልበስ የሚፈልጉ ቆነጃጅት እንስቶችን እየመረጡ በየፊልምና መዙቃው ኢንደስትሪው የፊት ገጽነትን ሽፋን እየሰጡ፤ የዜናዎችንና የመገናኛ ሚዲያ አትኩሮት አቅጣጫዎችን ቀድመው እየቀየሱ፤ በኢኮኖሚና የዝና ደረጃ እየደገፉ ወደላይ ወደ አርአያነት ደረጃ እንዲወጡ ከተደረገ በኋላ፤ ትውልዱን በነዚህ አርቲስቶችና የሚዲያ ሰዎች በኩል ስቦ መምራት ብዙም የማይቸግር ሆኖላቸዋል፡፡ ካለፉት መቶ ዓመታት ወዲህ በሚያስደነግጥ በከፍተኛ ፍጥነትና ተደራሽነት ወደ ዓለም የተሰራጩት የወሲብ ፊልሞችም የዓለሙን ዘመናዊ ትውልድ የሰብዓዊነት ቅርጽ ከነሥነ ምግባር ገጽታው ከውስጥ በመናፍስት ዳፍንታዊ አገዛዝ ስልት በኩል ስለተቆጣጠሩ፤ በእውነት ያለበሱትን የሚለብስ ትውልድ መገኘቱ ምንም የሚያስገርም አይሆንም፡፡
" ሴቲቱም በቀይና በሐምራዊ ልብስ ተጐናጽፋ በወርቅና በከበሩ ድንጋዮች በዕንቈችም ተሸልማ ነበር፥ በእጅዋም የሚያስጸይፍ ነገር የዝሙትዋም ርኵሰት የሞላባትን የወርቅ ጽዋ ያዘች፤"
(የዮሐንስ ራእይ 17፥4)... ይቀጥላል
ክፍል - 3
በስመ አብ፥ ወወልድ፥ ወመንፈስ ቅዱስ፥ አሐዱ አምላክ፥ አሜን፡፡
✞ የወሲብ ፊልም የቱን ያህል በዘመኑ ፋሽን ዘልቆ ሄደ? ✞
የዝሙት ፊልሞችና ምስሎች በዓለም አህጉራት በከፍተኛ ደረጃ የመሰራጨታቸው ሚስጢር ከጀርባው በተቀናጀ አደረጃጀትና ህቡዕ በሆነ አካሄድ ውስጥ የተሰለፉ የሚስጢር ማኅበራት ተጽዕኖ እና አቅም አማካኝነት ነው፡፡ አብዛኛው የወጣቱ ትውልድም በቀላሉ በሚያገኘው የእጅ ስልኮቹና የመገናኛ አውታሮች በኩል የሚለቀቁት እነዚህ የርኩሳን መናፍስት አዚማዊ መሣሪያ የሚሆኑ ፊልሞች፤ ወደኑሮና ልማድ የመቀላቀል ፍጥነታቸው ከፍተኛ የሆነ ሲሆን ያለ ውጣ ውረድና ተጨማሪ ጉልበት የተፈጥሮ ስሜት ላይ በመመርኮዝ የአእምሮ ክፍልን ተቆጣጥሮ በፍላጎት ስሜት አነሁልሎ በማደንዘዝ ወደ ልክፍት የሚመራ ስውር የማይነገርለት ጠፍናጊ ሱስ የመሆን ባሕሪይ ያለው የክፍለ ዘመናችን ማፍዠዣና ትውልድን ማሰሪያ ወጥመድ ነው፡፡
+++
ፊልሞቹ በጥንቃቄ ታቅደው ሲዘጋጁ ከኋላቸው እንዲያሳኳቸው የተቀመጡላቸው መናፍስታዊ ራእይና ግብ አላቸው፡፡ ከነዚያም መካከል ትውልዱ በሚከተላቸው የፋሽን፣ የአለባበስ፣ የመዝናኛ እና ሌሎች ዘርፎች በኩል ተዘዋዋሪ የሚመስል ነገር ግን በቀጥታ የተቆራኘ ዲያቢሎሳዊ ስብከቶችንና መገለጫዎችን ማስፋፋት አንደኛው ሲሆን፤ በእውነትም ታዲያ በዚህ በኩል ያለውን ግፊትና ያመጣውን ግልጽ ጫና ከትውልዳችንና ዘመኑ ጋር አሰናስለን ስንመለከተው በእጅጉ ተሳክቶላቸው በድሉም ከፍተኛ እርካታንና ድል አድራጊነት የሚያመጣላቸውን ስራ እንደፈጸሙ ማገናዘብ እንችላለን፡፡
+++
እነዚህ የዝሙት ኢንደስትሪዎች ጥፋት አድራሽነታቸውና የትውልድ ልክፍትነታቸው ገሃድ በወጣ እውነታ ያለ ማስረጃና ሰነድ አስፈላጊነት የተረጋገጠ ሲሆን፤ ነገር ግን "ተዉ" የሚላቸው ጠንካራ የመንግሥትና የግለሰቦች ተቋም እምብዛም አለመኖሩን ስናጤን፤ ከዓለም መንግሥታት ጀርባ ያሉት መናፍስታዊ መዋቅር ያላቸው ድርጅቶች ባለ ጠንካራ ሰንሰለታማ አሳሪዎቹ የሚስጢር ማኅበራት ክንድ የቱን ያህል እግዚአብሔር በረሳ ትውልድና ዘመን ላይ በርትቶ እየደቆሰ፣ እየጠመዘዘና እየገፈተረ እንዳለ መረዳት ያስችለናል፡፡ የወሲብ ፊልሞች አደገኝነት በንጽጽር ሲታይ ጥቂት የሚሆኑ ተመራማሪዎችና አጥኚዎች ጉዳቱንና ሁለ ገብ እከሉን በሰዎች ቋሚ ምስክርነት እያረጋገጡ ትምህርትና መረጃ ቢሰጡበትም፤ የወሲብ ኢንደስትሪዎቹ ከተሰራጩበት ጥልቀትና ስፋት አንፃር፤ እንዲሁ ትውልዱ ውስጥ ሥር ሰደው ካሉት የመናፍስት አገዛዝና አሠራር ምክንያት በቀላሉ ለኃጢአትና ለእርግማን አሳቦችና ድርጊቶች የመሳብ አዝማሚያው ከፍተኛ በመሆኑ፤ እዚህ ግባ የማይባል ለውጥ ሳያመጡ ቀርቶዋል፡፡
✞ የወሲብ ኢንደስትሪና የፋሽን ኢንደስትሪ ጣምራ ሂደት ✞
ከላይ በተገለጸው መልኩ እንደተቀመጠው ጉልህ የሆነና በቁጥርም የበዛ ጥናትና ምርምር ባለመካሄዱ እንጂ በዛሬው ትውልድ እውነታ ውስጥ የዝሙት ኢንደስትሪ ተቋማት የአሻራ ተጽዕኖ ያልነካካው የሕይወት ዘርፍ ፈልጎ ማግኘት የሚያዳግት ይሆናል፡፡ ከነዚህ በታላቅ ተጽዕኖ ውስጥ ውድቀው በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ የሚስጢር ማኅበራቱ ተልዕኮና እቅድ ተፈጻሚ ከሆነባቸው የትውልዱ ገጽታዎች መካከል የፋሽን ኢንደስትሪው ይጠቀሳል፡፡
+++
ዛሬ በፋሽን ኢንደስትሪው በኩል በየቀኑ እየተመረቱ የሚወጡት የልብስ ቅርጾችና ይዘቶች፣ የመዋቢያ መሳሪያዎች፣ የተለያዩ ቁሳቁሶች በአብዛኛው ራቁት ገላን የሚያበረታቱና ዝሙት ነክ እንድምታ የሚነበብባቸው ናቸው፡፡ ርጉማን መናፍስት፤ የዘመኑን ትውልድ የቀልብ አሳብ አዎንታዊ በሚመሰል ስሜት አነሁልሎ በራቁትነት ገጽታ በመሳብ፤ የፋሽንና የአለባበስ ሴሰኝነትን የሚያንጸባርቅ ፍላጎት በመፍጠር፤ በዓይን በመመልከት ብቻ የሕሊናን እምነት መስመር በማሳት፤ ውስጣዊ ዝንባሌን ከመናፍስት ትዕዛዝ በሚመነጭ ግፊት በማስቀልበስ ወሲብ ናፋቂ እንዲኮን ያደርጋሉ፡፡
ዘመናት አስቀድሞ አጭር ቀሚስና ደረት የሚገለብጥ ልብስ መልብስ በተለይ በኛ ማኅበረሰብ እሴትና እይታ መሠረት ነውር የተባለ ሲሆን፤ ዛሬ ነውሩ ረጃጅም ቀሚስ መልበስ እንደሆነ ሁሉ ከተማና ፈረንጅ ቀመስ የኑሮ ዘልማዶቻችን ውስጥ የአእምሮ መፍዘዝን በመናፍስቱ አስገዳጅነት አስቀምጠውብን ራቁትነትን እንደ ባሕል ለውጥ አጸደቅነው፤ 'እሴትን' የዘመን ያለፈ ታሪክ 'ነውርን' የዘመን ነባራዊ እውነት ለማድረግ ተገድደናል፡፡ በዚህ ጊዜ የሚመረቱትም ልብሶች በብዛት ሆነ ብለው ሙታንታ ላለመሆን ሩብ የቀራቸው ቀሚሶችና አልባሳት ላይ በጣም ያተኮሩ ስለሆኑ፤ ይህንን እንቃወማለን አሊያም አንለብስም የሚሉ ሴቶች እስኪቸገሩ ድረስ ዘመኑ እንደጠቅላላ አጋድሎ ራሱ አስገዳጅ ራሱ ፈራጅ የሆነ ትውልድን ሲያፈራ ከጀርባ ያሉት የመናፍስት ማኅበራት በእጅጉ ረክተውና በግባቸው መሳካትም ተደስተው፤ ዝሙት ዝሙት የሚሸት ኑሮን ከተለያየ አቅጣጫ ለጊዜው ሲያሠለጥኑ እኛ ቢቸገር ነንና ተራ በተራ እስከምንጨነቅ ድረስ፤ ተራ በተራ እስከምንሰቃይ ድረስ ቶሎ አይገባንም፡፡ ቢገባንም ዘመኑንና ትውልዱ እንደሆነው ለመሆን እንጂ የእምነትንና የማኅበረሰብን የእውነት ኃይል ለማስጠበቅ ሰብረን የምናልፍበት እውነቱም፣ ድፍረቱም፣ ፍላጎቱም የለንም፡፡
+++
በመናፍስታዊ ቁራኝነት ተለውሰው የሚለቀቁት የዝሙት ፊልሞችና ምስሎች በብዛት ሴቶችን እንደ ፍትወት ስሜት ማስታገሻ የቆጠሩና ተፈጥሮ ሁነታቸውንም ያከበሩ ስላይደሉ፤ ይህንኑ የመርዝ ዲያቢሎሳዊ ፕሮፖ-ጋንዳ በአልባስና በጌጣጌጥ በኩል እየለወሱት ለትውልዱ ልቦና መጋሸብና መጥፋት መንስኤ ሆነው፤ ሴት ልጆች በአጭር ቀሚስና ቁምጣ፣ ደረት በሚገለብጥ ልብስና ተክለ ሰውነትን በጉልህ በሚያሳይ ፋሽን እንዲያጌጡ የማስገደድ ያህል በስውር እየተጫኑ፤ በዚህኛው በኩል ደግሞ ይመጡና የውበት መለኪያና ደረጃ ራሳቸው ሆነው፤ ያልተራቆተች፣ ዘመኑን ያልመሰለችና ያልተጋጌጠች እንስት ከውበት መለኪያው በታች እንደሆነች፣ በተቃራኒ ጾታ ተመራጭነት ደረጃ ውስጥ ያልተካተተች፣ ኋላ ቀር እንደሆነች፣ ዘመኑን መዋጀት የተሣናትና የኢኮኖሚ ጥገኛ የሆነች እንደሆነች አድርገው በሙዚቃው፣ በፊልሙ፣ በመጽሐፍቱና በመዝናኛ ሚዲያው በኩል ይደሰኩራሉ፡፡
ገንዘብንና የሚዲያ አውታሮችን በመቆጣጠሩ ረገድ ከፍተኛ ሚና እና ኃይል ያላቸው እነዚህ የዲያቢሎስ እጆች የሆኑት ህቡዕ ድርጅቶች፤ የተራቆተ ልብስና ዘመኑን የሚመስል ልብስ ለመልበስ የሚፈልጉ ቆነጃጅት እንስቶችን እየመረጡ በየፊልምና መዙቃው ኢንደስትሪው የፊት ገጽነትን ሽፋን እየሰጡ፤ የዜናዎችንና የመገናኛ ሚዲያ አትኩሮት አቅጣጫዎችን ቀድመው እየቀየሱ፤ በኢኮኖሚና የዝና ደረጃ እየደገፉ ወደላይ ወደ አርአያነት ደረጃ እንዲወጡ ከተደረገ በኋላ፤ ትውልዱን በነዚህ አርቲስቶችና የሚዲያ ሰዎች በኩል ስቦ መምራት ብዙም የማይቸግር ሆኖላቸዋል፡፡ ካለፉት መቶ ዓመታት ወዲህ በሚያስደነግጥ በከፍተኛ ፍጥነትና ተደራሽነት ወደ ዓለም የተሰራጩት የወሲብ ፊልሞችም የዓለሙን ዘመናዊ ትውልድ የሰብዓዊነት ቅርጽ ከነሥነ ምግባር ገጽታው ከውስጥ በመናፍስት ዳፍንታዊ አገዛዝ ስልት በኩል ስለተቆጣጠሩ፤ በእውነት ያለበሱትን የሚለብስ ትውልድ መገኘቱ ምንም የሚያስገርም አይሆንም፡፡
" ሴቲቱም በቀይና በሐምራዊ ልብስ ተጐናጽፋ በወርቅና በከበሩ ድንጋዮች በዕንቈችም ተሸልማ ነበር፥ በእጅዋም የሚያስጸይፍ ነገር የዝሙትዋም ርኵሰት የሞላባትን የወርቅ ጽዋ ያዘች፤"
(የዮሐንስ ራእይ 17፥4)... ይቀጥላል
✞ የወሲብ ፊልምና ጠንቆቻቸው ✞
ክፍል - 4
በስመ አብ፥ ወወልድ፥ ወመንፈስ ቅዱስ፥ አሐዱ አምላክ፥ አሜን፡፡
✞ የወሲብ ፊልምና የመዝናኛው ኢንደስትሪ ተያያዥነት ✞
በክፍል ሦስት ትምህርታችን ለማንሣት እንደተሞከረው "የወሲብ ፊልሞችና የፋሽን ኢንደስትሪ በጣምራ እንዲጓዙ" የአያያዥነቱን ሚና መሣሪያ ሆኖ የተጫወተው የመዝናኛው ኢንደስትሪው ነው፡፡ አሁን እንዴት ማለት ነው፥ አንድ በሦስት ፈረሶች የሚጎተት ጋሪ ላይ ተቀምጦ የሚንቀሳቀሰን ሰው አስቡ፡ ግለሰቡ ፈረሶቹን ወደሚፈልግበት አቅጣጫ መንገድ በማስያዝ መሪ እየሆነ ወዳሻው ቦታ ይጓዛል፡፡ እንዲሁ ደግሞ ሦስቱን ኢንደስትሪዎች ማለትም የወሲብ ፊልሞችን ኢንደስትሪ፣ የፋሽን ኢንደስትሪ እና የመዝናኛ ኢንደስትሪን በጋራ አያይዞ በመጠቀም የመናፍስት ማኅበራቱ ትውልዱን ወደሚፈልጉበት አኗኗር፣ ሁኔታና የዘመን ገጽታ ለመምራት ችለውበታል፡፡ በዚህ አካሄድ ላይ ዲያቢሎሳዊ ቅኝቶችን እንደ ዓለም ትውልድ በሚገባ አስርጾ ለማስፈን እና የሚፈልጉት የዘመን ትውልድና የሕይወት ዘይቤ እንዲከሰት የሚከተሉትን ስልቶች ተጠቅመዋል፡፡
☞ የሥልጣኔ ዘውጎችን ጤናማ የውስጥ ትርጉማቸውን በማፋለስ፤ የሰው ልጅ ከተፈጠረበት መነሻ ዓላማ ኪሎ ሜትሮችን ርቆ አፍታ ቆም ብሎ ሳያገናዝብ እንዲጎዝ የዓለም ሩጫዎችን መድረሻ ግብ የሥጋ መሠረታዊ ፍላጎቶችን ማሟላት እንደሆነ ብቻ ስለማሳመን ሲሉ፥ በዘርፈ ብዙ ማኅበራዊ፣ ፖለቲካዊ፣ ታሪካዊና ነባራዊ ስዕሎች ውስጥ የሚፈልጉትን አድምቀው በተደጋጋሚ እያሳዩ በመሳብ፤ ተረጋግቶ የዓለም ነገራትን የመፈተሻ ጊዜን እያሳጡ የነፍስ ጥያቄዎችና የሃይማኖት እንድምታዎች የሚጨፈለቁበት ስርዓት መዘርጋት
☞ የሰው ልጆች ሰብአዊ ማንነታቸውን እስኪዘነጉ ድረስ ሌት ተቀን ለሥጋዊ ፍቃዶች ብቻ እንዲሮጡ ዓለምን እንደ ውድድር መድረክ አድርጎ በመቅረጽ፤ መሠረታዊ የእምነት መደንግጎች የሆኑት ፍቅርን፣ እምነትንና ተስፋን በተለያየ ዘዴ በመጉዳት፤ በምትኩ ጉልበት፣ ውበት፣ ገንዘብ፣ ዝና እና ሥልጣን የመኖር መጀመሪያም መጨረሻም ማረፊያ ተልዕኮዎች እንደሆኑ አስመስሎ የሕይወትን ቅርጽ በሥጋዊ አተረጓጎም ውስጥ ብቻ ለክቶ፤ የእምነትንና የባሕልን እሴቶች በየዘመኑ መድምሰስ
☞ የሕሊና፣ የልቦና እና የነፍስ ሰማያዊ ፍቃዶች በተፈጥሮም በሥጋ ስሜቶች የተከለሉ በመሆናቸው፤ እነዚህ መንፈሳዊ ፍቃዶች ወደ ውጪ እንዳይገለጡና ሥጋን እንዳይገዙ ለመቆጣጠር፤ የሥጋ ምቾቶችን የሚያገዝፉ እንዲሁም የሚያስጠብቁ የተብለጨለጩ ስብከቶችን እና ሽልማቶችን ከፊት እያስቀደሙ በማስቀመጥ፤ ፍላጎቶች ሁሉ ተመሳሳይ የሥጋ ዝንባሌ እንዲንጸባረቅባቸው መናፍስታዊ አዚሞችን በመጠቀም የትውልድን የጊዜ መስመር ከመነሻው፣ ከመካከሉ እና ከመድረሻውም ላይ እየሆኑ መቆጣጠር
☞ የሃይማኖትን ኃይልና መንገድ እንደ ጭቆና ቆጥሮ በማስቆጠር፤ የእምነት አካሄዶች የነጻነት ብዝበዛ ተጽዕኖ አሳዳሪዎች እንደሆኑ በተለያዩ ቀጥተኛና ተዘዋዋሪ ገለጻዎች ለዓለም በማድረስ፤ ለታሪካዊ ብሎም ለነባራዊ የሕብረተሰብ ችግሮች መንስኤ ናቸው በማለት ተጠያቂነትን ከፈጠሩ በኋላ፤ የሃይማኖት ፋይዳዎችና ጉዞዎችን ማቃለል፣ ማሳደድና ማጥፋት
☞ የፋሽን አልባሳትንና የአካል ተክለ ቁመና ውበትን በፉክክር መልኩ በማቅረብ፤ መገላለጥና መራቆት እንዲሁም የተዛነፈ አለባበስንና ገጽታን መጠቀም እንደ ልዩ የዘመናዊነት መታያ አድርጎ፤ እርቃንን እንደ ትልቅ ጀብዱና ዝና በመቁጠር፤ ለኃጢአት ማደግና ለመቅሰፍት መብዛት ምክንያት መሆኑን ሰው እንዳይረዳ አድርጎ ትውልዱን የፋሽን ምርኮኛ ማድረግ
☞ የማኅበራዊ ድረገጾችን፣ የመገናኛ አውታሮችን፣ የፊልም እና የሙዚቃ ኢንደስትሪዎችን ከሥር ከመሠረቱ በመቆጣጠር፤ በሰዎች ውስጥ ያሉትን መናፍስት ለክፋት አንድነት እንዲተባበሩ የማቀናጂያ ትስስሮሾችን በማመቻቸት፤ ርኩሰት እንዲያይል፣ አመፃ እንዲስፋፋ፣ እርግማን እንዲጸና፣ ሐሰት እንዲበራከት፣ እምነት እንዲሰናከል የማዳከሚያ ዕድሎችን በመጨመር ዘመኑን ከነፍስ ወከፍ አንስቶ በሰይጣናዊ አገዛዝ ሥር መጣል
☞ የሰው ልጆች በአእምሮ አመዛዛኝነትና በሕሊና ፍረደኛነት ነገሮችን እንዳያስተውሉ ስሜታዊነትን እንደ ደስታ መሸመቻ እንዲሁም ማንጸባረቂያነት በማድረግ፤ አስፈላጊ የኑሮ ግንኙነቶችንና ግንባታዎችን በአጥፊ መናፍስት መሪነት ሥር የወደቁ አጋጣሚ የሚመስሉ ሁነቶች ላይ እንዲጀምራቸው የተለያዩ የፌዝ፣ የቲዎሪና የፍልስፍና ጽንሰ ሐሳቦችን በመዝናኛ ማዕከላት በኩል በገፍ በማሰራጨት፤ አጢኖ የማስተዋልንና የሚመጣውን አሻግሮ የመመርመርን መንፈሳዊ ኃይል በማድከም፤ ስለቅርብ ቅርቡ ክስተቶች ብቻ እንዲኖሩ በውጪያዊ ግፊት ውስጥን ማጨለም
+++
ዓለምን በአንድ ማዕከላዊነት ለመጠቅለል ከሚያገለግሉ ታላላቅ መሣሪያዎች መካከል አንደኛው የሆነው የመዝናኛው ኢንደስትሪ፥ በተለይም ዛሬ ዛሬ ተጽዕኖው እጅግ ሥር የሰደደና የአጥፊዎቹን የርኩሰት ኃይሎች ለጥፋት የሚውልን ድካም ያቀለለ፤ በአያያዥ ሰፊ አድማስነቱ በኩልም ብዙ የኃጢአት ሥራዎችን እንዲያከናውኑ መንገድ የሆነ ተቋም መሆንን ችሏል፡፡
በዛሬይቱ ዘመን ላይ ደግሞ የመዝናኛ ኢንደስትሪዎች ጫናና ስርጭት በብዙ የአኗኗር አቅጣጫዎች ላይ ተገኝቶ የአሁኑን ትውልድ ጉዞ መሪ መሆን የቻለ፤ በአቋሙ ግንባታ ውስጥም ሰርጎ ገብቶ ወደ ውጪያዊ ገጽታ ሊያውም እንደሚያኮራ ሆኖ እየተገለጠ ያለ፤ በቋንቋና ማንነት ላይም የራሱን አሻራ ያለ ብዙ አድካሚ ውጣ ውረድ ማኖር የቻለ በመሆኑ፤ ይህንን ተከትሎ የዘመኑ ወጣቶች ኑሮና ሕይወት ምን መልክ ያዘ ስንል የሚከተሉትን እናገኛለን፡፡
❖ በሚታየው የመዝናኛ ኢንደስትሪ ውስጥ ባሉት የፊት ገጽ አርቲስቶችና ፊት አውራሪዎች አማካኝነት የሚሰጠውን የንግግር፣ የአለባበስና የአኗኗር ልማዶችን ሳይጨምር ሳይቀንስ ወደራሱ ማንነት ያንጸባረቀ ሲሆን ታዲያ፤ አሁን አርቲስቶቹ ሲንጨባረሩ ትውልዳችንም ይንጨባረራል፣ ጠምዛዦቹ ሲራቁቱ ትውልዳችንም ይራቆታል፣ ፊት አውራሪዎቹ ሰላምታቸው ስድብ አዘል ሲሆን እዚህም እኛም ጋር ጸያፍ ቃላት "ደህና አደርክ?"ን ተክተዋል፡፡
❖ አብዛኛዎቹ በመዝናኛው ማዕከላት የሚንጸባረቁት የታይታ ገጽታዎች ሥጋዊ ምቾቶችን የሚያሳዩና ነጻነት መሰል መረን የለቀቁ አንዳንዴም ግልጽ እብደቶችን የሚወክሉ ናቸውና፤ ትውልዳችንም ይህንን የሥጋ ምቾት ለመቀዳጀትና በእንጀራ ብቻ የተመሠረተ ኑሮን ለመገንባት ሲል እርስ በእርሱ በዘመናዊነት ልኬት የሚወዳደር፣ በኢኮኖሚ ደረጃዎች ለመበላለጥ የሚውተረተር፣ ከፊት ፊት ቀድሞ ለመታየት በሚደረገው ጥረት ውስጥ እርስ በእርሱ ከውስጥ የተገፋፋ፤ አንድነትና መተባበር የራቀው ዜጋ ሆነና ቁጭ አለ፡፡
❖ በተጨማሪ ሃይማኖታዊ እውነታዎችን፣ አገረሰባዊ ባሕሎችንና ቤተሰባዊ መስተጋብሮችን የሚንቅ፤ በሥልጡንነት ጓዳና ላይ ለመጓዝ የእምነት ጫናዎችን እንደ ጎታች ተጽዕኖ የሚቆጥር፤ ወደፊት መሄድ ማለት የኋላውን መናድና በእርሱ ቦታ አዲሱን ተክቶ መራመድ የሚመስለው፤ ነገራትን ሁሉ ከሥጋ ፍቃድና ዓይን ብቻ የሚለካ፥ ግራ ግብት ያለው፥ መንፈሳዊ ሞገሱን የማያውቅ፣ ጸጋና ራእዩን ያጣ፣ የአባቶቹን የታሪክ ፈለግ ማግኘት የተሣነው፣ ለውሳኔ የሚቸገርና ሁልጊዜ የድካም ስሜት ያልተለየው ትውልድ ሆነን፤ እንዳደረጉን የምንሆን መሞከሪያ አሻንጉሊቶች በመሆን ሰማያዊ ኃይል ርቆን እንባትታለን፡፡ ይቀጥላል....
ክፍል - 4
በስመ አብ፥ ወወልድ፥ ወመንፈስ ቅዱስ፥ አሐዱ አምላክ፥ አሜን፡፡
✞ የወሲብ ፊልምና የመዝናኛው ኢንደስትሪ ተያያዥነት ✞
በክፍል ሦስት ትምህርታችን ለማንሣት እንደተሞከረው "የወሲብ ፊልሞችና የፋሽን ኢንደስትሪ በጣምራ እንዲጓዙ" የአያያዥነቱን ሚና መሣሪያ ሆኖ የተጫወተው የመዝናኛው ኢንደስትሪው ነው፡፡ አሁን እንዴት ማለት ነው፥ አንድ በሦስት ፈረሶች የሚጎተት ጋሪ ላይ ተቀምጦ የሚንቀሳቀሰን ሰው አስቡ፡ ግለሰቡ ፈረሶቹን ወደሚፈልግበት አቅጣጫ መንገድ በማስያዝ መሪ እየሆነ ወዳሻው ቦታ ይጓዛል፡፡ እንዲሁ ደግሞ ሦስቱን ኢንደስትሪዎች ማለትም የወሲብ ፊልሞችን ኢንደስትሪ፣ የፋሽን ኢንደስትሪ እና የመዝናኛ ኢንደስትሪን በጋራ አያይዞ በመጠቀም የመናፍስት ማኅበራቱ ትውልዱን ወደሚፈልጉበት አኗኗር፣ ሁኔታና የዘመን ገጽታ ለመምራት ችለውበታል፡፡ በዚህ አካሄድ ላይ ዲያቢሎሳዊ ቅኝቶችን እንደ ዓለም ትውልድ በሚገባ አስርጾ ለማስፈን እና የሚፈልጉት የዘመን ትውልድና የሕይወት ዘይቤ እንዲከሰት የሚከተሉትን ስልቶች ተጠቅመዋል፡፡
☞ የሥልጣኔ ዘውጎችን ጤናማ የውስጥ ትርጉማቸውን በማፋለስ፤ የሰው ልጅ ከተፈጠረበት መነሻ ዓላማ ኪሎ ሜትሮችን ርቆ አፍታ ቆም ብሎ ሳያገናዝብ እንዲጎዝ የዓለም ሩጫዎችን መድረሻ ግብ የሥጋ መሠረታዊ ፍላጎቶችን ማሟላት እንደሆነ ብቻ ስለማሳመን ሲሉ፥ በዘርፈ ብዙ ማኅበራዊ፣ ፖለቲካዊ፣ ታሪካዊና ነባራዊ ስዕሎች ውስጥ የሚፈልጉትን አድምቀው በተደጋጋሚ እያሳዩ በመሳብ፤ ተረጋግቶ የዓለም ነገራትን የመፈተሻ ጊዜን እያሳጡ የነፍስ ጥያቄዎችና የሃይማኖት እንድምታዎች የሚጨፈለቁበት ስርዓት መዘርጋት
☞ የሰው ልጆች ሰብአዊ ማንነታቸውን እስኪዘነጉ ድረስ ሌት ተቀን ለሥጋዊ ፍቃዶች ብቻ እንዲሮጡ ዓለምን እንደ ውድድር መድረክ አድርጎ በመቅረጽ፤ መሠረታዊ የእምነት መደንግጎች የሆኑት ፍቅርን፣ እምነትንና ተስፋን በተለያየ ዘዴ በመጉዳት፤ በምትኩ ጉልበት፣ ውበት፣ ገንዘብ፣ ዝና እና ሥልጣን የመኖር መጀመሪያም መጨረሻም ማረፊያ ተልዕኮዎች እንደሆኑ አስመስሎ የሕይወትን ቅርጽ በሥጋዊ አተረጓጎም ውስጥ ብቻ ለክቶ፤ የእምነትንና የባሕልን እሴቶች በየዘመኑ መድምሰስ
☞ የሕሊና፣ የልቦና እና የነፍስ ሰማያዊ ፍቃዶች በተፈጥሮም በሥጋ ስሜቶች የተከለሉ በመሆናቸው፤ እነዚህ መንፈሳዊ ፍቃዶች ወደ ውጪ እንዳይገለጡና ሥጋን እንዳይገዙ ለመቆጣጠር፤ የሥጋ ምቾቶችን የሚያገዝፉ እንዲሁም የሚያስጠብቁ የተብለጨለጩ ስብከቶችን እና ሽልማቶችን ከፊት እያስቀደሙ በማስቀመጥ፤ ፍላጎቶች ሁሉ ተመሳሳይ የሥጋ ዝንባሌ እንዲንጸባረቅባቸው መናፍስታዊ አዚሞችን በመጠቀም የትውልድን የጊዜ መስመር ከመነሻው፣ ከመካከሉ እና ከመድረሻውም ላይ እየሆኑ መቆጣጠር
☞ የሃይማኖትን ኃይልና መንገድ እንደ ጭቆና ቆጥሮ በማስቆጠር፤ የእምነት አካሄዶች የነጻነት ብዝበዛ ተጽዕኖ አሳዳሪዎች እንደሆኑ በተለያዩ ቀጥተኛና ተዘዋዋሪ ገለጻዎች ለዓለም በማድረስ፤ ለታሪካዊ ብሎም ለነባራዊ የሕብረተሰብ ችግሮች መንስኤ ናቸው በማለት ተጠያቂነትን ከፈጠሩ በኋላ፤ የሃይማኖት ፋይዳዎችና ጉዞዎችን ማቃለል፣ ማሳደድና ማጥፋት
☞ የፋሽን አልባሳትንና የአካል ተክለ ቁመና ውበትን በፉክክር መልኩ በማቅረብ፤ መገላለጥና መራቆት እንዲሁም የተዛነፈ አለባበስንና ገጽታን መጠቀም እንደ ልዩ የዘመናዊነት መታያ አድርጎ፤ እርቃንን እንደ ትልቅ ጀብዱና ዝና በመቁጠር፤ ለኃጢአት ማደግና ለመቅሰፍት መብዛት ምክንያት መሆኑን ሰው እንዳይረዳ አድርጎ ትውልዱን የፋሽን ምርኮኛ ማድረግ
☞ የማኅበራዊ ድረገጾችን፣ የመገናኛ አውታሮችን፣ የፊልም እና የሙዚቃ ኢንደስትሪዎችን ከሥር ከመሠረቱ በመቆጣጠር፤ በሰዎች ውስጥ ያሉትን መናፍስት ለክፋት አንድነት እንዲተባበሩ የማቀናጂያ ትስስሮሾችን በማመቻቸት፤ ርኩሰት እንዲያይል፣ አመፃ እንዲስፋፋ፣ እርግማን እንዲጸና፣ ሐሰት እንዲበራከት፣ እምነት እንዲሰናከል የማዳከሚያ ዕድሎችን በመጨመር ዘመኑን ከነፍስ ወከፍ አንስቶ በሰይጣናዊ አገዛዝ ሥር መጣል
☞ የሰው ልጆች በአእምሮ አመዛዛኝነትና በሕሊና ፍረደኛነት ነገሮችን እንዳያስተውሉ ስሜታዊነትን እንደ ደስታ መሸመቻ እንዲሁም ማንጸባረቂያነት በማድረግ፤ አስፈላጊ የኑሮ ግንኙነቶችንና ግንባታዎችን በአጥፊ መናፍስት መሪነት ሥር የወደቁ አጋጣሚ የሚመስሉ ሁነቶች ላይ እንዲጀምራቸው የተለያዩ የፌዝ፣ የቲዎሪና የፍልስፍና ጽንሰ ሐሳቦችን በመዝናኛ ማዕከላት በኩል በገፍ በማሰራጨት፤ አጢኖ የማስተዋልንና የሚመጣውን አሻግሮ የመመርመርን መንፈሳዊ ኃይል በማድከም፤ ስለቅርብ ቅርቡ ክስተቶች ብቻ እንዲኖሩ በውጪያዊ ግፊት ውስጥን ማጨለም
+++
ዓለምን በአንድ ማዕከላዊነት ለመጠቅለል ከሚያገለግሉ ታላላቅ መሣሪያዎች መካከል አንደኛው የሆነው የመዝናኛው ኢንደስትሪ፥ በተለይም ዛሬ ዛሬ ተጽዕኖው እጅግ ሥር የሰደደና የአጥፊዎቹን የርኩሰት ኃይሎች ለጥፋት የሚውልን ድካም ያቀለለ፤ በአያያዥ ሰፊ አድማስነቱ በኩልም ብዙ የኃጢአት ሥራዎችን እንዲያከናውኑ መንገድ የሆነ ተቋም መሆንን ችሏል፡፡
በዛሬይቱ ዘመን ላይ ደግሞ የመዝናኛ ኢንደስትሪዎች ጫናና ስርጭት በብዙ የአኗኗር አቅጣጫዎች ላይ ተገኝቶ የአሁኑን ትውልድ ጉዞ መሪ መሆን የቻለ፤ በአቋሙ ግንባታ ውስጥም ሰርጎ ገብቶ ወደ ውጪያዊ ገጽታ ሊያውም እንደሚያኮራ ሆኖ እየተገለጠ ያለ፤ በቋንቋና ማንነት ላይም የራሱን አሻራ ያለ ብዙ አድካሚ ውጣ ውረድ ማኖር የቻለ በመሆኑ፤ ይህንን ተከትሎ የዘመኑ ወጣቶች ኑሮና ሕይወት ምን መልክ ያዘ ስንል የሚከተሉትን እናገኛለን፡፡
❖ በሚታየው የመዝናኛ ኢንደስትሪ ውስጥ ባሉት የፊት ገጽ አርቲስቶችና ፊት አውራሪዎች አማካኝነት የሚሰጠውን የንግግር፣ የአለባበስና የአኗኗር ልማዶችን ሳይጨምር ሳይቀንስ ወደራሱ ማንነት ያንጸባረቀ ሲሆን ታዲያ፤ አሁን አርቲስቶቹ ሲንጨባረሩ ትውልዳችንም ይንጨባረራል፣ ጠምዛዦቹ ሲራቁቱ ትውልዳችንም ይራቆታል፣ ፊት አውራሪዎቹ ሰላምታቸው ስድብ አዘል ሲሆን እዚህም እኛም ጋር ጸያፍ ቃላት "ደህና አደርክ?"ን ተክተዋል፡፡
❖ አብዛኛዎቹ በመዝናኛው ማዕከላት የሚንጸባረቁት የታይታ ገጽታዎች ሥጋዊ ምቾቶችን የሚያሳዩና ነጻነት መሰል መረን የለቀቁ አንዳንዴም ግልጽ እብደቶችን የሚወክሉ ናቸውና፤ ትውልዳችንም ይህንን የሥጋ ምቾት ለመቀዳጀትና በእንጀራ ብቻ የተመሠረተ ኑሮን ለመገንባት ሲል እርስ በእርሱ በዘመናዊነት ልኬት የሚወዳደር፣ በኢኮኖሚ ደረጃዎች ለመበላለጥ የሚውተረተር፣ ከፊት ፊት ቀድሞ ለመታየት በሚደረገው ጥረት ውስጥ እርስ በእርሱ ከውስጥ የተገፋፋ፤ አንድነትና መተባበር የራቀው ዜጋ ሆነና ቁጭ አለ፡፡
❖ በተጨማሪ ሃይማኖታዊ እውነታዎችን፣ አገረሰባዊ ባሕሎችንና ቤተሰባዊ መስተጋብሮችን የሚንቅ፤ በሥልጡንነት ጓዳና ላይ ለመጓዝ የእምነት ጫናዎችን እንደ ጎታች ተጽዕኖ የሚቆጥር፤ ወደፊት መሄድ ማለት የኋላውን መናድና በእርሱ ቦታ አዲሱን ተክቶ መራመድ የሚመስለው፤ ነገራትን ሁሉ ከሥጋ ፍቃድና ዓይን ብቻ የሚለካ፥ ግራ ግብት ያለው፥ መንፈሳዊ ሞገሱን የማያውቅ፣ ጸጋና ራእዩን ያጣ፣ የአባቶቹን የታሪክ ፈለግ ማግኘት የተሣነው፣ ለውሳኔ የሚቸገርና ሁልጊዜ የድካም ስሜት ያልተለየው ትውልድ ሆነን፤ እንዳደረጉን የምንሆን መሞከሪያ አሻንጉሊቶች በመሆን ሰማያዊ ኃይል ርቆን እንባትታለን፡፡ ይቀጥላል....
ማኅሌተ ጽጌ ትርጓሜ
2/ ሰላምኪ ማርያም አብቆለት ዕፀ ትእምርት
ወአውጽአት ጽጌ እም አፈ ምውት
ማርያም ሰላምታሽ የታምር እንጨትን አበቀለች
ከሞተ ሰው አፍ አበባን አወጣች
🌻🌹🌷💐☘🍀ስቅለት ከሞተ ሰው መቃብር ላይ የበቀለች የእንጨቷ ስምና ታሪክ🌼🌸🌺🍀💐🌹🌻
አንድ ድሀ የዕለት ምግቡን እየሰረቀ የሚበላ ነበር ነገር ግን እመቤታችን ድንግል ማርያምን ይወዳትና ብዙ ግዜ ሰላምታዋን ያቀርብላት ነበር።
ከዕለታት አንድ ቀን የዚያች አገር ሰዎች በግፍ ሰቀሉት ተሰቅሎ እያለ ነፍሱ እስከወጣች(ከስጋው እስከተለየች) ድረስ የእመቤታችንን ሰላምታ አላቋረጠም።
በዚያች አገር ላለው ኤጲስቆጶስ አስቀድማ እመቤታችን እንደ ነገረችው በክርስቲያኖች መቃብር መካከል አስቀበረው ከ4 ቀን በኋላም ስሟ ፈርከሊሳ የምትባል ትንሽ እንጨት ከመቃብሩ ላይ በቀለች ቁመቷ አንድ ክንድ ያህል ነበር።
መልኳም ያማረ ቅጠሏም ለምለም ሲሆን አበቦቿም እንደ ብር ነጭ ነበሩ።
በቅጠሎቿም ውስጥ ወርቅ በመሰለ ቀለም የእመቤታችን የድንግል ማርያም ሰላምታ ተጽፎ ይታይ ነበር ሁሎችም አደነቁ ለኤጲስቆጶሱም ያዩትን ታምር ሁሉ ነገሩት መቃብሩንም ይቆፍሩ ዘንድ ያች እንጨትም ከየት እንደመጣችና ሥሯን ያዩ ዘንድ አዘዛቸው እንደአዘዛቸውም መቃብሩን በቆፈሩ ግዜ ከመቃብሩ ወደላይ ወጥታ ያች ዕንጨት አበባን አብባ ተገኘች ስለዚህ እግዚአብሔርንና እመቤታችንን ፈጽመው አመስግነዋልና። ይቀጥላል ....
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
2/ ሰላምኪ ማርያም አብቆለት ዕፀ ትእምርት
ወአውጽአት ጽጌ እም አፈ ምውት
ማርያም ሰላምታሽ የታምር እንጨትን አበቀለች
ከሞተ ሰው አፍ አበባን አወጣች
🌻🌹🌷💐☘🍀ስቅለት ከሞተ ሰው መቃብር ላይ የበቀለች የእንጨቷ ስምና ታሪክ🌼🌸🌺🍀💐🌹🌻
አንድ ድሀ የዕለት ምግቡን እየሰረቀ የሚበላ ነበር ነገር ግን እመቤታችን ድንግል ማርያምን ይወዳትና ብዙ ግዜ ሰላምታዋን ያቀርብላት ነበር።
ከዕለታት አንድ ቀን የዚያች አገር ሰዎች በግፍ ሰቀሉት ተሰቅሎ እያለ ነፍሱ እስከወጣች(ከስጋው እስከተለየች) ድረስ የእመቤታችንን ሰላምታ አላቋረጠም።
በዚያች አገር ላለው ኤጲስቆጶስ አስቀድማ እመቤታችን እንደ ነገረችው በክርስቲያኖች መቃብር መካከል አስቀበረው ከ4 ቀን በኋላም ስሟ ፈርከሊሳ የምትባል ትንሽ እንጨት ከመቃብሩ ላይ በቀለች ቁመቷ አንድ ክንድ ያህል ነበር።
መልኳም ያማረ ቅጠሏም ለምለም ሲሆን አበቦቿም እንደ ብር ነጭ ነበሩ።
በቅጠሎቿም ውስጥ ወርቅ በመሰለ ቀለም የእመቤታችን የድንግል ማርያም ሰላምታ ተጽፎ ይታይ ነበር ሁሎችም አደነቁ ለኤጲስቆጶሱም ያዩትን ታምር ሁሉ ነገሩት መቃብሩንም ይቆፍሩ ዘንድ ያች እንጨትም ከየት እንደመጣችና ሥሯን ያዩ ዘንድ አዘዛቸው እንደአዘዛቸውም መቃብሩን በቆፈሩ ግዜ ከመቃብሩ ወደላይ ወጥታ ያች ዕንጨት አበባን አብባ ተገኘች ስለዚህ እግዚአብሔርንና እመቤታችንን ፈጽመው አመስግነዋልና። ይቀጥላል ....
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
Forwarded from እግዚኦ መሐረነ ክርስቶስ (Welldegerima G/Christos)
መሳሳት አይደለም ................
ደስታን የሚፈጥሩ ፣የሚያበራታቱ ፣የሚገስጹ ድንቅ እና አስተማሪ የአማርኛ ጥቅሶች ለማግኘት ይፈልጋሉ ?
👇👇ለፕሮፋይል የሚሆኑ ጥቅሶች👇
🖤 @amharic_Quetes 🖤
🖤 @amharic_Quetes 🖤
ደስታን የሚፈጥሩ ፣የሚያበራታቱ ፣የሚገስጹ ድንቅ እና አስተማሪ የአማርኛ ጥቅሶች ለማግኘት ይፈልጋሉ ?
👇👇ለፕሮፋይል የሚሆኑ ጥቅሶች👇
🖤 @amharic_Quetes 🖤
🖤 @amharic_Quetes 🖤
አንዲት በትዳሯ በባሏ ሐይለኛነት ሞገደኛነት ትእግስት አልባነት የተጨነቀችና የተማረረች
ሴት ወደ ንስሐ አባቷ ሔዳ እያለቀሰች "አባቴ ምን ማድረግ እንዳለብኝ ባላውቅም አሁንስ
በቃኝ ከዚህ ሰውጋር መኖር አልችልም "ስትል ትናገራቸዋለች።
ንስሐ አባቷም እንዲህ ሲሉ ይመክሯታል ። "ልጄ በአንድ አፍ ውስጥ የሚኖሩትን ጥርስንና
ምላስን አስታውሺ። እነዚህ አካላት ተፈጥሮአቸው የተለያየ ነው። ጥርስ ነጭ ነው ምላስ
ቀይ ናት። ጥርስ ጠንካራ ስለታም ነው ምላስ በጣም ለስላሳ ናት። አፍ ሲከፈትላት ምላስ
ትወጣለች። ሲከደን በገዛ ጎረቤቷ ላለመጎዳት ትሸሻለች። ጥርስ ያደማውን እጅ ምላስ
ትልስለታለች። ጥርስ ሲያኝክ ምላስ ታርስለታለች። የፊት ጥርስ ማኘክ ሲከብደው ወደ መንጋጋው እህሉን በመውሰድ ትረዳዋለች።
ግን አንድ ቤት ይኖራሉ። እናንተም መልካችሁ
አቅማችሁ ጸባያችሁ የተለያየ አንዳችሁ ስለታም አንዳችሁ ለስላሳ ብትሆኑም አብራችሁ
እንደ ምላስና ጥርስ ተረዳድታችሁ ተቻችላችሁ መኖር ይገባችኋል። ሐይለኛና ትሁት ሰው
አንድ ቤት አይኖርም ያለው ማነው? ሥጋችንና ነፍሳችን እኮ ጦርነት ላይ ናቸው ሥጋ ልብላ
ልጠጣ ልጨፍር ሲል ነፍስ ደግሞ ልጹም ልስገድ ልዘምር ይላል። እንደውም ሐዋሪያው
ቅዱስ ጳውሎስ ነፍሴ በሥጋዬ ላይ ሥጋዬም በነፍሴ ላይ ይቀዋወማሉ። ይላል
በዚህ ምድር ላይ አንዳቸው አንዳቸውን እየተቀዋወሙ አንዳቸው ያለ አንዳቸው መኖር
አይችሉምና አብረው ይዘልቃሉ። ባልና ሚስትም አንድ አምሳል አንድ አካል ናቸው እስከተባሉ ድረስ ስጋ ያለ ነፍስ ነፍስ ያለ ስጋ እንደማይኖሩና እንደማይለያዪ ሊለያዪ አይገባቸውም።
ሞት የሚባለውም የነፍስ ከስጋ መለየት ነው።ባልና ሚስትም አንዳቸው ካንዳቸው የተለያዩ እለት ሁለቱም እንደ ሞቱ ነው የሚቆጠሩት
ልቦና ግዥ ልጄ ስጋችንና ነፍሳችን ሁልጊዜ ጦርነት ላይ ቢሆኑም እስከ እለተ ሞታችን
እንደማይለያዩት ሁሉ እኛም መቀዋወማችንን ለመለያየት አናድርገው።
መለያየት ጥል ክርክር የሰይጣን ነው። ገላትያ 5:7 ባይሆን መልካም የሆነው እንዲያሸንፍ እድል
እንስጠው።" በማለት መክረው ሸኟት።
ያስተማረን የገሰጸን እግዚአብሔር የተመሰገነ ይሁን። እናንተስ ምን ተማራችሁ?
ሴት ወደ ንስሐ አባቷ ሔዳ እያለቀሰች "አባቴ ምን ማድረግ እንዳለብኝ ባላውቅም አሁንስ
በቃኝ ከዚህ ሰውጋር መኖር አልችልም "ስትል ትናገራቸዋለች።
ንስሐ አባቷም እንዲህ ሲሉ ይመክሯታል ። "ልጄ በአንድ አፍ ውስጥ የሚኖሩትን ጥርስንና
ምላስን አስታውሺ። እነዚህ አካላት ተፈጥሮአቸው የተለያየ ነው። ጥርስ ነጭ ነው ምላስ
ቀይ ናት። ጥርስ ጠንካራ ስለታም ነው ምላስ በጣም ለስላሳ ናት። አፍ ሲከፈትላት ምላስ
ትወጣለች። ሲከደን በገዛ ጎረቤቷ ላለመጎዳት ትሸሻለች። ጥርስ ያደማውን እጅ ምላስ
ትልስለታለች። ጥርስ ሲያኝክ ምላስ ታርስለታለች። የፊት ጥርስ ማኘክ ሲከብደው ወደ መንጋጋው እህሉን በመውሰድ ትረዳዋለች።
ግን አንድ ቤት ይኖራሉ። እናንተም መልካችሁ
አቅማችሁ ጸባያችሁ የተለያየ አንዳችሁ ስለታም አንዳችሁ ለስላሳ ብትሆኑም አብራችሁ
እንደ ምላስና ጥርስ ተረዳድታችሁ ተቻችላችሁ መኖር ይገባችኋል። ሐይለኛና ትሁት ሰው
አንድ ቤት አይኖርም ያለው ማነው? ሥጋችንና ነፍሳችን እኮ ጦርነት ላይ ናቸው ሥጋ ልብላ
ልጠጣ ልጨፍር ሲል ነፍስ ደግሞ ልጹም ልስገድ ልዘምር ይላል። እንደውም ሐዋሪያው
ቅዱስ ጳውሎስ ነፍሴ በሥጋዬ ላይ ሥጋዬም በነፍሴ ላይ ይቀዋወማሉ። ይላል
በዚህ ምድር ላይ አንዳቸው አንዳቸውን እየተቀዋወሙ አንዳቸው ያለ አንዳቸው መኖር
አይችሉምና አብረው ይዘልቃሉ። ባልና ሚስትም አንድ አምሳል አንድ አካል ናቸው እስከተባሉ ድረስ ስጋ ያለ ነፍስ ነፍስ ያለ ስጋ እንደማይኖሩና እንደማይለያዪ ሊለያዪ አይገባቸውም።
ሞት የሚባለውም የነፍስ ከስጋ መለየት ነው።ባልና ሚስትም አንዳቸው ካንዳቸው የተለያዩ እለት ሁለቱም እንደ ሞቱ ነው የሚቆጠሩት
ልቦና ግዥ ልጄ ስጋችንና ነፍሳችን ሁልጊዜ ጦርነት ላይ ቢሆኑም እስከ እለተ ሞታችን
እንደማይለያዩት ሁሉ እኛም መቀዋወማችንን ለመለያየት አናድርገው።
መለያየት ጥል ክርክር የሰይጣን ነው። ገላትያ 5:7 ባይሆን መልካም የሆነው እንዲያሸንፍ እድል
እንስጠው።" በማለት መክረው ሸኟት።
ያስተማረን የገሰጸን እግዚአብሔር የተመሰገነ ይሁን። እናንተስ ምን ተማራችሁ?
"በሌላ ሀገር ትንሽ ወንዝ ካለች መዝናኛ አድርገው ይዝናኑባታል፡፡ እኛ ሀገር ትንሽ ወንዝ ካለች የመለያያ ድንበር አድርገን እንጋጭባታለን፡፡"
🎤መጋቤ ሐዲስ እሸቱ
ታላቁ ሊቅ ዮሐንስ አፈወርቅ እንዲህ ይላል …
‹ሰው እግዚአብሔር ሲለየው፤ ጠባዩ እንደ አራዊት፤ አመጋገቡ እንደ እንስሳ፣ ሆኖ መልኩ ብቻ የእግዚአብሔር ሆኖ ይቀራል›። በጣም ቀለል ባለ አገላለጽ ሲም ካርዱ የወጣ ሞባይል ማለት ነው። ጥሪ የማይቀበል….
...እኔ በዕውነቱ ከተማው ፈርሶ እየተሰራ ነው እየተባለ ዐይናማዎቹ ሲያወሩም ሲያስወሩም እሰማለው። ፈርሶ መሰራት ያለበት ግን የሰዉ አስተሳሰብ ነው።...
የሰዉ አስተሳሰብ ፈርሶ ካልተሰራ፤ የተሰራ ከተማ ይፈርሳል።
ጃፓንና ቻይና ሀገራቸውን ያለሙት መጀመሪያ አስተሳሰባቸውን አልምተው ነው። ቤታችሁ ገብታችሁ እንድታጤኑት ነው።
… እንደምታዩኝ እኔ ዐይነ ስውር ነኝ። ቀላል አይደለም.... እንክዋን ዘውትር ዓይን አጥቶ አንድ ቀን መብራት ሲሄድ ስንት እንደምታማርሩ ታውቅታላችሁ።
እኔ ግን ዓይኔ ባለማየቱ አንድ ቀን እንኳን አልቅሼ አላውቅም። ከሞት ወዲያ መብራት አለ። ከመቃብር በላይ መብራት አለ። ... ወደ መቃብር ሲወርድ ማንም ዓይነ ስውር ነው። ማንም ዐይኑ እያየ የተቀበረ የለም።
ተስፋችን ግን ምንድን ነው? ከሞት ወዲያ ሕይወት አለ። ከሞት ወዲያ ብርሃን አለ...
አንድ አንድ ጊዜ እመኛለሁ። የማይረባ ነገር ስናይ (ዓይናችንን) የሚያጠፋ ቆጣሪ ቢኖር... መልካም ነገር እስክናይ ድረስ ለጊዜው የሚያጠፋ ቆጣሪ ቢኖር።
…አሁን እንደው ጆሮ በካርድ የሚሰራ ቢሆን ሐሜት እንሰማ ነበር? የምንፈልገውን (ብቻ) አውርተን ስዊች ኦፍ እናደርገው ነበር።
ችግሩ ብዙ ነው፡፡ ስንት ዞማ ጸጉር ይዞ አስተሳሰቡ የከረደደ አለ።
... እባካችሁ ሰው እንሁን… የንጉሠ ነገሥቱ የክርስቶስ አልጋ ወራሾች ነን... የደስታችሁ ልኬት የደስታችሁ ሚዛን ምግብና መጠጥ አይሁን፤ መኪናና ቤት ዝናንም አታርጉ።
እኛ መለኪያችን ጽድቅ ነው። መከኪያችን መንግሥተ ሰማያት ነው። ያ የምንገባበት ቤት ደግም የተዋበ፣ የደመቀ፣ መብራት ውሀ የማይሄድበት፤ 24 ሰዓት ክርስቶስ የሚያበራበት፤ 24 ሰዓት የሕይወት ውሀ የሚጠጣበት፤ ሀብታም፤ ደሀ፣ ተራ ሰው የማይባልበት፣ እገሌ ግባ እገሌ ውጣ የማይባልበት
ቦታ ነው.....።
🙏 ወስብሐት ለእግዚአብሔር 🙏
🎤መጋቤ ሐዲስ እሸቱ
ታላቁ ሊቅ ዮሐንስ አፈወርቅ እንዲህ ይላል …
‹ሰው እግዚአብሔር ሲለየው፤ ጠባዩ እንደ አራዊት፤ አመጋገቡ እንደ እንስሳ፣ ሆኖ መልኩ ብቻ የእግዚአብሔር ሆኖ ይቀራል›። በጣም ቀለል ባለ አገላለጽ ሲም ካርዱ የወጣ ሞባይል ማለት ነው። ጥሪ የማይቀበል….
...እኔ በዕውነቱ ከተማው ፈርሶ እየተሰራ ነው እየተባለ ዐይናማዎቹ ሲያወሩም ሲያስወሩም እሰማለው። ፈርሶ መሰራት ያለበት ግን የሰዉ አስተሳሰብ ነው።...
የሰዉ አስተሳሰብ ፈርሶ ካልተሰራ፤ የተሰራ ከተማ ይፈርሳል።
ጃፓንና ቻይና ሀገራቸውን ያለሙት መጀመሪያ አስተሳሰባቸውን አልምተው ነው። ቤታችሁ ገብታችሁ እንድታጤኑት ነው።
… እንደምታዩኝ እኔ ዐይነ ስውር ነኝ። ቀላል አይደለም.... እንክዋን ዘውትር ዓይን አጥቶ አንድ ቀን መብራት ሲሄድ ስንት እንደምታማርሩ ታውቅታላችሁ።
እኔ ግን ዓይኔ ባለማየቱ አንድ ቀን እንኳን አልቅሼ አላውቅም። ከሞት ወዲያ መብራት አለ። ከመቃብር በላይ መብራት አለ። ... ወደ መቃብር ሲወርድ ማንም ዓይነ ስውር ነው። ማንም ዐይኑ እያየ የተቀበረ የለም።
ተስፋችን ግን ምንድን ነው? ከሞት ወዲያ ሕይወት አለ። ከሞት ወዲያ ብርሃን አለ...
አንድ አንድ ጊዜ እመኛለሁ። የማይረባ ነገር ስናይ (ዓይናችንን) የሚያጠፋ ቆጣሪ ቢኖር... መልካም ነገር እስክናይ ድረስ ለጊዜው የሚያጠፋ ቆጣሪ ቢኖር።
…አሁን እንደው ጆሮ በካርድ የሚሰራ ቢሆን ሐሜት እንሰማ ነበር? የምንፈልገውን (ብቻ) አውርተን ስዊች ኦፍ እናደርገው ነበር።
ችግሩ ብዙ ነው፡፡ ስንት ዞማ ጸጉር ይዞ አስተሳሰቡ የከረደደ አለ።
... እባካችሁ ሰው እንሁን… የንጉሠ ነገሥቱ የክርስቶስ አልጋ ወራሾች ነን... የደስታችሁ ልኬት የደስታችሁ ሚዛን ምግብና መጠጥ አይሁን፤ መኪናና ቤት ዝናንም አታርጉ።
እኛ መለኪያችን ጽድቅ ነው። መከኪያችን መንግሥተ ሰማያት ነው። ያ የምንገባበት ቤት ደግም የተዋበ፣ የደመቀ፣ መብራት ውሀ የማይሄድበት፤ 24 ሰዓት ክርስቶስ የሚያበራበት፤ 24 ሰዓት የሕይወት ውሀ የሚጠጣበት፤ ሀብታም፤ ደሀ፣ ተራ ሰው የማይባልበት፣ እገሌ ግባ እገሌ ውጣ የማይባልበት
ቦታ ነው.....።
🙏 ወስብሐት ለእግዚአብሔር 🙏