ሰባራ ልብ
ሰባራ ልብ የፃፈው ከንቱ ግጥም
ስሜትን ሰቅዞ ባይዝም እንኳ ባይጥም
ያፍቃሪን ሰው ህይዎት ባይለውጥም
እኔ ግን እፅፋለሁ ፊደልን አያይዤ
ከተውሽኝ ቦታ ሰባራ ልቤን ይዤ
የጨረቃ የክዋክብት ድብቅ መረብ
ሰማይ ወርዶ ከምድር ጋር ቢቀራረብ
የሌት ነፋስ
ብርድና ውርጭ ገላዬ ላይ ቢረባረብ
በዶፍ ዝናብ ምድር ቢጥለቀለቅ
እኔ እንደው ከተውሽኝ ከዛ ቦታ አለቅ
ታነሽኝ እንደው መተሽ አንሽኝ
እባክሽ ከሰው አታነሽኝ
መልኬ ቢገረጣም ባንቺ ፍቅር ደዝዤ
ብዙ መንገድን በሃሳቤ ተጉዤ
እጠብቅሽ አለሁ ሰባራ ልቤን ይዤ
@gGetem
@gGetem
@gGetem
ሰባራ ልብ የፃፈው ከንቱ ግጥም
ስሜትን ሰቅዞ ባይዝም እንኳ ባይጥም
ያፍቃሪን ሰው ህይዎት ባይለውጥም
እኔ ግን እፅፋለሁ ፊደልን አያይዤ
ከተውሽኝ ቦታ ሰባራ ልቤን ይዤ
የጨረቃ የክዋክብት ድብቅ መረብ
ሰማይ ወርዶ ከምድር ጋር ቢቀራረብ
የሌት ነፋስ
ብርድና ውርጭ ገላዬ ላይ ቢረባረብ
በዶፍ ዝናብ ምድር ቢጥለቀለቅ
እኔ እንደው ከተውሽኝ ከዛ ቦታ አለቅ
ታነሽኝ እንደው መተሽ አንሽኝ
እባክሽ ከሰው አታነሽኝ
መልኬ ቢገረጣም ባንቺ ፍቅር ደዝዤ
ብዙ መንገድን በሃሳቤ ተጉዤ
እጠብቅሽ አለሁ ሰባራ ልቤን ይዤ
@gGetem
@gGetem
@gGetem
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
....ከሚላ 2....
#ገጣሚ_ሊዮ_ማክ
ልብ አንጥፎ መሬት
※※※※※ ሼር ያድርጉ!! ※※※※※
አዘጋጅ፦ண @gGetem
ண @gGetem
═══════ ♢.✰.♢ ══════ @yosikeman
@gGetem
ዛሬም....
#ገጣሚ_ሊዮ_ማክ
ልብ አንጥፎ መሬት
※※※※※ ሼር ያድርጉ!! ※※※※※
አዘጋጅ፦ண @gGetem
ண @gGetem
═══════ ♢.✰.♢ ══════ @yosikeman
@gGetem
ዛሬም....
🥰2❤1👏1
Forwarded from የሆሄያት ህብር📝📝 (Sirake peterøs ☞Ye Yerijo)
የyohabi ደብዳቤ
😘የማይድን ናፍቆት.... 'የተረሳው ክፍል'😢
"ስትሄድ ያልከኝን መርሳት አቅቶኛል"
😘የማይድን ናፍቆት.... 'የተረሳው ክፍል'😢
"ስትሄድ ያልከኝን መርሳት አቅቶኛል"
በቀን እንደሞትኩ...
ከአፈሩ አፈሩን ጥለነው
ከሰማዩ ሰማያቱን አልፈነው
ሄድን ሄድንና...
ከፈጣሪ የፍርድ መንበሩ ጋር ደረስን፤
ተረኛ ነበርና...
ደጃፉ ላይ ወንበር ስበን ተቀመጥን።
ተረኛ እስኪጠራ ፥ እስኪገባ ፈጣሪው ጋ
ትዝ ይለኛል ፥ ባንዲት ርዕስ ስናወጋ።
ሞትኩኝ...
የሚላስ የሚቀመስ አጥቼ
ሞትኩኝ...
"ትን" ብሎኝ ብፌ አሰናድቼ
ሞትኩኝ...
አልጋ ላይ ላመታት እንዳልነበርኩ ማቅቄ
ሞትኩኝ...
ስዝናና ውዬ ስመለስ ደክሞኝ መሪ ለቅቄ
ሞትኩኝ...
በተኛኹበት ወዳጄ ባልኩት በሰው ታንቄ
ሞትኩኝ...
ሞትኩኝ ሲሉ ፥ ኹሉ ኹሉም በየተራው
በቀኑ እንደሞተ ፥ ኹሉ ሰው ሚያወራው።
እኔ ግን...
እኔ ግን...
በቅጡ መኖሬን
በቅጡ መሞቴን ስላላወኩ
በቀኔ ሳይሆን በቀን እንደ ሞትኩ
አስታውሼ ነበር ፥ የተናገርኩ!
@gGetem
@gGetem
ከአፈሩ አፈሩን ጥለነው
ከሰማዩ ሰማያቱን አልፈነው
ሄድን ሄድንና...
ከፈጣሪ የፍርድ መንበሩ ጋር ደረስን፤
ተረኛ ነበርና...
ደጃፉ ላይ ወንበር ስበን ተቀመጥን።
ተረኛ እስኪጠራ ፥ እስኪገባ ፈጣሪው ጋ
ትዝ ይለኛል ፥ ባንዲት ርዕስ ስናወጋ።
ሞትኩኝ...
የሚላስ የሚቀመስ አጥቼ
ሞትኩኝ...
"ትን" ብሎኝ ብፌ አሰናድቼ
ሞትኩኝ...
አልጋ ላይ ላመታት እንዳልነበርኩ ማቅቄ
ሞትኩኝ...
ስዝናና ውዬ ስመለስ ደክሞኝ መሪ ለቅቄ
ሞትኩኝ...
በተኛኹበት ወዳጄ ባልኩት በሰው ታንቄ
ሞትኩኝ...
ሞትኩኝ ሲሉ ፥ ኹሉ ኹሉም በየተራው
በቀኑ እንደሞተ ፥ ኹሉ ሰው ሚያወራው።
እኔ ግን...
እኔ ግን...
በቅጡ መኖሬን
በቅጡ መሞቴን ስላላወኩ
በቀኔ ሳይሆን በቀን እንደ ሞትኩ
አስታውሼ ነበር ፥ የተናገርኩ!
@gGetem
@gGetem
, ዕ ድ ል
የት ነሽ ዕድል የትስ ብዬ ልፈልግሽ
ከሁሉም በላይ ነው እና ያንቺ ማዕረግሽ
እስኪ ላግኝሽና ለእኔም ይድረሰኝ ወግሽ
ዕድል የት ነሽ ዕድል የትስ ብዬ ልፈልግሽ
ፍጥረት በዕድሉ ሊኖር የተፃፈለትን ትቶ
ከማይሆነው ሊጋባ ከሚሆነው ተፋትቶ
ከአላህ ከእግዚሔሩ ጋር ተጋጭቶ
አንዱ ካንዱ ያለዕድል ከዕድል ተፋጭቶ
ተጎናትሮ ተሟሙቶ ላይፈጥር ዕድል
ዕልህን
ታጥቆ ይዘምታል ፅናትን በቅናት ሊገድል
ዕድል ዕድል ዕድል የት ነሽ ዕድል
አንቺን ስፈልግ እኔ እራሴን እዳልገድል
ዕድል የት ነሽ ዕድል የትስ ብዬ ልፈልግሽ
ከሁሉም በላይ ነው እና ያንቺ ማዕረግሽ
እስኪ ላግኝሽና ለእኔም ይድረሰኝ ወግሽ
@gGetem
@gGetem
@gGetem
የት ነሽ ዕድል የትስ ብዬ ልፈልግሽ
ከሁሉም በላይ ነው እና ያንቺ ማዕረግሽ
እስኪ ላግኝሽና ለእኔም ይድረሰኝ ወግሽ
ዕድል የት ነሽ ዕድል የትስ ብዬ ልፈልግሽ
ፍጥረት በዕድሉ ሊኖር የተፃፈለትን ትቶ
ከማይሆነው ሊጋባ ከሚሆነው ተፋትቶ
ከአላህ ከእግዚሔሩ ጋር ተጋጭቶ
አንዱ ካንዱ ያለዕድል ከዕድል ተፋጭቶ
ተጎናትሮ ተሟሙቶ ላይፈጥር ዕድል
ዕልህን
ታጥቆ ይዘምታል ፅናትን በቅናት ሊገድል
ዕድል ዕድል ዕድል የት ነሽ ዕድል
አንቺን ስፈልግ እኔ እራሴን እዳልገድል
ዕድል የት ነሽ ዕድል የትስ ብዬ ልፈልግሽ
ከሁሉም በላይ ነው እና ያንቺ ማዕረግሽ
እስኪ ላግኝሽና ለእኔም ይድረሰኝ ወግሽ
@gGetem
@gGetem
@gGetem
❤1
ባዶ እስኪሆን ድረስ
እንባውን ይሰፍራል ፣ ኑሮ ያሻመደው
ጥርሶቹን ይገልጣል ፣ ምቾት የታደለው።
ሰፍረን እናውቃለን ፣ እንባን በኩባያ
ሀጫ ጥርስ ዘግነናል ፣ ስጥ ሆኖ ገበያ ።
ይሄን እናውቃለን ፣ ጥንትም ነበር ድሮ
የሷ ግን ገረመን ፣ ውል ሳትን ዘንድሮ ።
ትስቅ ነበር እኮ ፣ ሆዷን በእጇ ይዛ
ከጨዋታ መኃል ፣ አንዱን ሰበዝ መ’ዛ
አንድም አልሰማንም ፣ ሀዘን እንጉርጉሮ
አንገት አልደፋንም ፣ ቀኖቿ ተቆጥሮ
እንዲህ በሳቅ ውሀ ፣ ገፅዋ ተሸርሽሮ…
እስክናጣት ድረስ ፣ ያቺን መልካም እንስት
ከቶም አላየንም ፣ ቁዝሚያ ና ምልክት
ሳቅ እንዴት ይሆናል ?
የመታመም ቅኔ
………………. ዝግ ያለ ስንብት?
@gGetem
@gGetem
@gGetem
እንባውን ይሰፍራል ፣ ኑሮ ያሻመደው
ጥርሶቹን ይገልጣል ፣ ምቾት የታደለው።
ሰፍረን እናውቃለን ፣ እንባን በኩባያ
ሀጫ ጥርስ ዘግነናል ፣ ስጥ ሆኖ ገበያ ።
ይሄን እናውቃለን ፣ ጥንትም ነበር ድሮ
የሷ ግን ገረመን ፣ ውል ሳትን ዘንድሮ ።
ትስቅ ነበር እኮ ፣ ሆዷን በእጇ ይዛ
ከጨዋታ መኃል ፣ አንዱን ሰበዝ መ’ዛ
አንድም አልሰማንም ፣ ሀዘን እንጉርጉሮ
አንገት አልደፋንም ፣ ቀኖቿ ተቆጥሮ
እንዲህ በሳቅ ውሀ ፣ ገፅዋ ተሸርሽሮ…
እስክናጣት ድረስ ፣ ያቺን መልካም እንስት
ከቶም አላየንም ፣ ቁዝሚያ ና ምልክት
ሳቅ እንዴት ይሆናል ?
የመታመም ቅኔ
………………. ዝግ ያለ ስንብት?
@gGetem
@gGetem
@gGetem
🥰2
እንቅልፌን ላውስሽ
እስከ ጠዋት ተኝ
ለችግርሽ እንደው
እኔ ልብከንከን ፣
ከቀን ባላድንሽ
የሌት ህልሜ ከሆን
ባንቺ ይታለም ፣
ከንፈርሽ ስር ያለች ነጥብ
ማሪያም ስማሽ ከሆነ ግን ፣
እንዴት አየህ አትበይ
ከእግሬ ስር ተኝተሽ
በሌሊት ወጋግን፣
(ነውና ያየሁሽ )
ካይንሽ ስር ላይ ገደል አለ
ግፋኝ ልውደቅ እያነባሽ ፣
እኔ ከታች ልውደቅ ቆይ
የዱር እሾህ እንዳይወጋሽ ፣
ደረቴ ጋር ጥብቅ በይ
ይጠፍሩኝ በልጥ ዛፍ ፣
ጡቶችሽ ጋር ካሳደረኝ
ከተራራው ጎጆ አፍ ፣
ከሰው መንጋ ተገንጥለን
ከጫጩት ድምፅ ተነጥለን ፣
በባዶ እግር ጫካ አልፈን
ተራራው ጫፍ ጎጆ ሰርተን
በጫካ ዛፍ ተከልለን ፣
ከሰሜን ንፋስ ሲ ነ ፍ ስ
ደመናው ሰማይ ሲ ወ ር ስ
በምስራቅ ጎን
የድንቢጥ ድምፅ
በምዕራብ ታች
የአንበሳም...፣
በቀስታ ተቃቅፈን
በዝምታ ስንሳሳም ፣
በጣቶቼ ወገብሽን
ክንዴ ሞልቶት ዞሮ ሲደርስ ፣
ከሰማዬ ነጫጭ ውሃ
ዝናብ ሚሉት ከእኛ ሲፈስ ፣
ተቃቅፈን ከአልጋችን
ዶፉ ሲወርድ ከጎጆ ውጭ ፣
በሳቅሽ እየታጀብኩ
በብልጭታው እያየሁሽ
በነጎድጓድ ስትደነግጭ ፣
በጣቶችሽ ጣቴን
በጭንቀት ስትጨብጭ ፣
ድንግጥ ስትይ አንገቴ ስር
ትንፋሽሽ ላይ ሙቀት ሳገኝ ፣
በግርብታ ያልጠበቀ
በቀ..ስ..ታ..ከንፈርሽ እንደሳመኝ
ከሩቅ ላይም የአራዊት ድምፅ
ከክንዴ ላይ ያንቺ ነፍስ ፣
ከንፈርሽ ስር ባለው ሀይቅ
ዋኝተንበት እንፍሰስ ፣
ከዚህ ጩኸት እንደበቅ
ከጫጫታው እንሰወር
በጨለማው ፍቅር ወበቅ
እንደ ድር እንደወር
ህልም ማለት..?እስኪ እንወቅ...?
የእኛን ኑሮ ካልጠበቁት
ከገፉን ስር ከሚስሙት
አድበስብሰው ከሚቀብሩት
ተራራ ስር ካለው ጎጆ
ዘላለም ነጥለን
ዘላለም ተቃቅፈን
ዘላለም እንሙት
@gGetem
@gGetem
@gGetem
እስከ ጠዋት ተኝ
ለችግርሽ እንደው
እኔ ልብከንከን ፣
ከቀን ባላድንሽ
የሌት ህልሜ ከሆን
ባንቺ ይታለም ፣
ከንፈርሽ ስር ያለች ነጥብ
ማሪያም ስማሽ ከሆነ ግን ፣
እንዴት አየህ አትበይ
ከእግሬ ስር ተኝተሽ
በሌሊት ወጋግን፣
(ነውና ያየሁሽ )
ካይንሽ ስር ላይ ገደል አለ
ግፋኝ ልውደቅ እያነባሽ ፣
እኔ ከታች ልውደቅ ቆይ
የዱር እሾህ እንዳይወጋሽ ፣
ደረቴ ጋር ጥብቅ በይ
ይጠፍሩኝ በልጥ ዛፍ ፣
ጡቶችሽ ጋር ካሳደረኝ
ከተራራው ጎጆ አፍ ፣
ከሰው መንጋ ተገንጥለን
ከጫጩት ድምፅ ተነጥለን ፣
በባዶ እግር ጫካ አልፈን
ተራራው ጫፍ ጎጆ ሰርተን
በጫካ ዛፍ ተከልለን ፣
ከሰሜን ንፋስ ሲ ነ ፍ ስ
ደመናው ሰማይ ሲ ወ ር ስ
በምስራቅ ጎን
የድንቢጥ ድምፅ
በምዕራብ ታች
የአንበሳም...፣
በቀስታ ተቃቅፈን
በዝምታ ስንሳሳም ፣
በጣቶቼ ወገብሽን
ክንዴ ሞልቶት ዞሮ ሲደርስ ፣
ከሰማዬ ነጫጭ ውሃ
ዝናብ ሚሉት ከእኛ ሲፈስ ፣
ተቃቅፈን ከአልጋችን
ዶፉ ሲወርድ ከጎጆ ውጭ ፣
በሳቅሽ እየታጀብኩ
በብልጭታው እያየሁሽ
በነጎድጓድ ስትደነግጭ ፣
በጣቶችሽ ጣቴን
በጭንቀት ስትጨብጭ ፣
ድንግጥ ስትይ አንገቴ ስር
ትንፋሽሽ ላይ ሙቀት ሳገኝ ፣
በግርብታ ያልጠበቀ
በቀ..ስ..ታ..ከንፈርሽ እንደሳመኝ
ከሩቅ ላይም የአራዊት ድምፅ
ከክንዴ ላይ ያንቺ ነፍስ ፣
ከንፈርሽ ስር ባለው ሀይቅ
ዋኝተንበት እንፍሰስ ፣
ከዚህ ጩኸት እንደበቅ
ከጫጫታው እንሰወር
በጨለማው ፍቅር ወበቅ
እንደ ድር እንደወር
ህልም ማለት..?እስኪ እንወቅ...?
የእኛን ኑሮ ካልጠበቁት
ከገፉን ስር ከሚስሙት
አድበስብሰው ከሚቀብሩት
ተራራ ስር ካለው ጎጆ
ዘላለም ነጥለን
ዘላለም ተቃቅፈን
ዘላለም እንሙት
@gGetem
@gGetem
@gGetem
🔥4
👏1
#የእንቢታሽ ሱሰኛ!
(ሚካኤል አስጨናቂ)
አንቺን በማሰብ ውስጥ መደሰት ለምጄ
ፍቅርሽ ሱስ ሆኖብኝ ... ማንነቴን ክጄ
ባንቺ መወድስ ስም ክታብ አሰርቼ
ስምሽን አንግቼ …
እንደ አሞራ ዙሬሽ ፣ አንዣብቤ በላይ
አንቺን ሳይሽ ፣ ‘ዋይ ፣ ዋይ …’
አጃኢብ ነው መቼም!
ስትሄጅ ተራመድሁ... ስትቆሚ ቆሜ
ባንቺ ስፍር ልኬት.. .በጠርዝ ተመድሜ
ከዕድሜ ከዘመኔ ፣ ዓመታት ቆንጥሬ
ከእንቢታሽ ጋራ ፣ በእልህ ሰክሬ
ስንኞችን ጭሬ.. .
አንቺን በመጀንጀንጀን ፣ ልማድ ተጠፍሬ
በሚጣፍጥ ህመም ...
ብቻዬን በአርምሞ ፣ ስብሰለስል ኖሬ
ከሀሳቤ ማግስት ... በስንኜ ድርድር
ቃላት ድል ነስተውሽ ፣ በኃይላቸው በትር
እኔም በተራዬ ፣ መፈቀር ስጀምር
“ፍቅርህን ተቀበልሁ” ያልሽኝ ጊዜ ‘ለታ
ፍቅርሽ ጥሎኝ ጠፋ ፣ ትዝታሽ ተረታ።
(እንቢ በይኝ ዳግም
እልህን ላጣጥም ። )
@gGetem
@gGetem
@gGetem
(ሚካኤል አስጨናቂ)
አንቺን በማሰብ ውስጥ መደሰት ለምጄ
ፍቅርሽ ሱስ ሆኖብኝ ... ማንነቴን ክጄ
ባንቺ መወድስ ስም ክታብ አሰርቼ
ስምሽን አንግቼ …
እንደ አሞራ ዙሬሽ ፣ አንዣብቤ በላይ
አንቺን ሳይሽ ፣ ‘ዋይ ፣ ዋይ …’
አጃኢብ ነው መቼም!
ስትሄጅ ተራመድሁ... ስትቆሚ ቆሜ
ባንቺ ስፍር ልኬት.. .በጠርዝ ተመድሜ
ከዕድሜ ከዘመኔ ፣ ዓመታት ቆንጥሬ
ከእንቢታሽ ጋራ ፣ በእልህ ሰክሬ
ስንኞችን ጭሬ.. .
አንቺን በመጀንጀንጀን ፣ ልማድ ተጠፍሬ
በሚጣፍጥ ህመም ...
ብቻዬን በአርምሞ ፣ ስብሰለስል ኖሬ
ከሀሳቤ ማግስት ... በስንኜ ድርድር
ቃላት ድል ነስተውሽ ፣ በኃይላቸው በትር
እኔም በተራዬ ፣ መፈቀር ስጀምር
“ፍቅርህን ተቀበልሁ” ያልሽኝ ጊዜ ‘ለታ
ፍቅርሽ ጥሎኝ ጠፋ ፣ ትዝታሽ ተረታ።
(እንቢ በይኝ ዳግም
እልህን ላጣጥም ። )
@gGetem
@gGetem
@gGetem
👍1
እንደምትወዳት ንገራት,
(በእውቀቱ ስዩም)
ሕይወት የብድር በሬ፥መቼ ሁሌ ይጠመዳል
ለጊዜው ብቻ የመጣ፥ ጊዜው ሲደርስ ይሄዳል
የተሰጠህ ጸጋ ሁሉ፥ ደሞ ካንተ ይወሰዳል::
ቀለበት፥ አምባር አይደሉም
እጅህ ላይ ሁልጊዜ የሉም
-ቀናት ሳምንታት ወራት
ዛሬውኑ ፥አሁኑኑ፥ እንደምትወዳት ንገራት::
አበቦች ሁሉ ሳይረግፉ
ምኡዝ ሽታዎች ሳይጠፉ
ያጸድ በሮች ሳይቆለፉ
በንቦች ጎዳና ላይ፥ተርቦች ሳይሰለፉ
በንፋስ ክንፍ ሳይመታ
ሕይወት የላምባ መብራት
አሁንኑ ዛሬውኑ ፥እንደምትወዳት ንገራት፤
ርቃ ሳትገሰግስ
ገና ስንቋን ስትደግስ
እንዲሁ እንዳማረባት
ቀልብህ እንደቀረባት
መቃብር በመዳፉ
እንደጠጠር ሳይቀልባት
አፈሩን ሳትዛመድ
ወደማትቀባው አመድ
ወደማትስበው አየር
ሳትቀየር
አንትም አንደበት ሳለህ፥ እሷም ጆሮ ሳያጥራት
ዛሬውኑ! አሁኑኑ! እንደምትወዳት ንገራት።
@gGetem
@gGetem
(በእውቀቱ ስዩም)
ሕይወት የብድር በሬ፥መቼ ሁሌ ይጠመዳል
ለጊዜው ብቻ የመጣ፥ ጊዜው ሲደርስ ይሄዳል
የተሰጠህ ጸጋ ሁሉ፥ ደሞ ካንተ ይወሰዳል::
ቀለበት፥ አምባር አይደሉም
እጅህ ላይ ሁልጊዜ የሉም
-ቀናት ሳምንታት ወራት
ዛሬውኑ ፥አሁኑኑ፥ እንደምትወዳት ንገራት::
አበቦች ሁሉ ሳይረግፉ
ምኡዝ ሽታዎች ሳይጠፉ
ያጸድ በሮች ሳይቆለፉ
በንቦች ጎዳና ላይ፥ተርቦች ሳይሰለፉ
በንፋስ ክንፍ ሳይመታ
ሕይወት የላምባ መብራት
አሁንኑ ዛሬውኑ ፥እንደምትወዳት ንገራት፤
ርቃ ሳትገሰግስ
ገና ስንቋን ስትደግስ
እንዲሁ እንዳማረባት
ቀልብህ እንደቀረባት
መቃብር በመዳፉ
እንደጠጠር ሳይቀልባት
አፈሩን ሳትዛመድ
ወደማትቀባው አመድ
ወደማትስበው አየር
ሳትቀየር
አንትም አንደበት ሳለህ፥ እሷም ጆሮ ሳያጥራት
ዛሬውኑ! አሁኑኑ! እንደምትወዳት ንገራት።
@gGetem
@gGetem
👌1
መናፈቅ ማለት …
ከወትሮው በድንገት
ከከተማ ግፊያ
ከሰፊው ገበያ
ከሰው ትርምስ
ከህይወት ግብስብስ
አረፍ ብለው ባልጋ
ከራስ ጋር ሲወጋ
የአስቴር እና ኤፍሬም
አባባይ ሙዚቃ ...
አንጀትንን ሲገርፍ
ትዝታን ሲያነቃ
እንዲህ ይመስለኛል !
..
መናፈቅ ማለት..
በቡሄ አመሻሽ
እርግት ባለ ሰማይ
ልጅነት ሲወያይ
ሲሸት የኩበት ጭስ
የአሪቲ ቃና መንደርን ሲዳብስ
ውብ አደይ አበባ ምድሪቷን ሲያነግስ
እንዲህ ይመስለኛል !
..
መናፈቅ ማለት ..
እኔና አንቺ አፍረን
ከዓይን ተሸሽገን
ከመስቀል ዳመራ
ሸሽተን ከጓደኞች
ፈልገን ሰዋራ ...
ተቃቅፈን እየሄድን
ውሎን ስንጋራ
ስትሰጪኝ ፖፖቲን
‘’ፖስት ካርዴስ ?’’ ብለሽ
ኪሴን ስትዳብሽኝ
እንዲህ ይመስለኛል ።
..
መናፈቅ ማለት …
ትምህርት ሊዘጋ ወቅት
ድራማ ተውነን
በሰኔ ሰላሳ ለመታየት ደምቀን
በድራማው መኃል
ፈልገን ስህተት
ከልብ የሳቅን ዕለት
ከሳቅን በኋላ
ኩሪፊያ ሲከተለን ...
ድፍን ሶስት ወራትን
ያለመገናኘት ፍርሀት ሲውጠን
ስትሰናበችኝ በጥልቁ ዝምታ
ዓይንሽን እያየሁ
ዓይኖቼን እያየሽ
የቆዘምን ለታ …..
እንዲህ ይመስለኛል ።
..
መናፈቅ ማለት …
የሽፍታ ፍርሀት
ነፍስያን ሳይንጣት
በ አራት እግር ጉዞ
የመኪናን መስኮት
በራስ ተመርኩዞ
የገጠርን መስመር
አንዱን መንገድ ይዞ
ተራራውን ማየት
እሸቱን መጎምዠት
ከገበሬ ቁና
በቆሎ መሸመት
የፀሀይዋን ግባት
አሻግሮ መቃኘት
እንዲህ ይመስለኛል።
…
መናፈቅ ማለት …
(ሚካኤል አ )
@gGetem
@gGetem
@gGetem
ከወትሮው በድንገት
ከከተማ ግፊያ
ከሰፊው ገበያ
ከሰው ትርምስ
ከህይወት ግብስብስ
አረፍ ብለው ባልጋ
ከራስ ጋር ሲወጋ
የአስቴር እና ኤፍሬም
አባባይ ሙዚቃ ...
አንጀትንን ሲገርፍ
ትዝታን ሲያነቃ
እንዲህ ይመስለኛል !
..
መናፈቅ ማለት..
በቡሄ አመሻሽ
እርግት ባለ ሰማይ
ልጅነት ሲወያይ
ሲሸት የኩበት ጭስ
የአሪቲ ቃና መንደርን ሲዳብስ
ውብ አደይ አበባ ምድሪቷን ሲያነግስ
እንዲህ ይመስለኛል !
..
መናፈቅ ማለት ..
እኔና አንቺ አፍረን
ከዓይን ተሸሽገን
ከመስቀል ዳመራ
ሸሽተን ከጓደኞች
ፈልገን ሰዋራ ...
ተቃቅፈን እየሄድን
ውሎን ስንጋራ
ስትሰጪኝ ፖፖቲን
‘’ፖስት ካርዴስ ?’’ ብለሽ
ኪሴን ስትዳብሽኝ
እንዲህ ይመስለኛል ።
..
መናፈቅ ማለት …
ትምህርት ሊዘጋ ወቅት
ድራማ ተውነን
በሰኔ ሰላሳ ለመታየት ደምቀን
በድራማው መኃል
ፈልገን ስህተት
ከልብ የሳቅን ዕለት
ከሳቅን በኋላ
ኩሪፊያ ሲከተለን ...
ድፍን ሶስት ወራትን
ያለመገናኘት ፍርሀት ሲውጠን
ስትሰናበችኝ በጥልቁ ዝምታ
ዓይንሽን እያየሁ
ዓይኖቼን እያየሽ
የቆዘምን ለታ …..
እንዲህ ይመስለኛል ።
..
መናፈቅ ማለት …
የሽፍታ ፍርሀት
ነፍስያን ሳይንጣት
በ አራት እግር ጉዞ
የመኪናን መስኮት
በራስ ተመርኩዞ
የገጠርን መስመር
አንዱን መንገድ ይዞ
ተራራውን ማየት
እሸቱን መጎምዠት
ከገበሬ ቁና
በቆሎ መሸመት
የፀሀይዋን ግባት
አሻግሮ መቃኘት
እንዲህ ይመስለኛል።
…
መናፈቅ ማለት …
(ሚካኤል አ )
@gGetem
@gGetem
@gGetem