.................ዮሐንስ✍️
ተይ አትከተይኝ
ላታስቆሚኝ መንገዴን አትዝጊው
ልቤ መች ፍቅር አዝሎ አሁን መተሽ ምፈልጊው
በቃ ሂጂ አልጠቅምሽም
ውስጤ ወና ድንጋይ ሆኗል የኔን ሀዘን አታብሺም
"ውዴ ሆዴ "አትበይኝ ውብ ቃላቶች አትምረጪ
ለፍቅራችን መለያ ስም አይጠቅምሽም ከቶ'አታውጪ
የልቤን ጉም ጥቁር ጭጋግ እንደ ፀሐይ መክፈት ካልቻሽ
የኔን ህመም በመታመም በኔ መዳን አንቺ ካልዳንሽ
ያንቺ ፍቅር ምን ሊጠቅመኝ ከቃል ውጪ ምን አትርፎ
እንደዚ አይነት የፍቅር ሂወት እስከዛሬስ መች ተፅፎ
አየሽ
ፍቅሬ ስትይኝ ዝም ያልኩሽ
ስትጠሪኝ ያልሰማውሽ
እንዳይመስልሽ ክፉ ሆኜ ከቶ አይደለም የጭካኔ
በኔ እምባ እንዳረጥቢነው የምገፊሽ ከጎኔ
በኔ ጥላ አንቺ ወድቀሽ በወንድ ልጅ ሳትጎጂ
ልብሽ ጠባሳ ሳያርፍበት እኔን ተይኝ አንቺ ሂጂ
@gGetem
@gGetem
💔1
አልሞትም!
(በእውቀቱ ስዩም)
ስሚ!
እኔ በዚህ ዐለም ፤ብዙ ብሰቃይም
አንድ ሀሙስ የቀረው፤ መስየ ብታይም
አምሮቴን ሳላገኝ፤ሱሴን ሳላከትም
በመሬት ከርስ ውስጥ ፤ገላየን አልከትም
አልሞትም!
ማንም ባልደፈረው፤ መንገድ ሳልገሰግስ
እንደ ንጉስ አይዙር፤ግማሽ ቀን ሳልነግስ
በጠገበው ሳልስቅ፤ ለራበው ሳልደግስ
አልሞትም!
ዝማሜን ሳላወልቅ፤ ያንድበቴን ግድብ
ዙፋን ላይ ሳልሸና፤ ጌቶቼን ሳልሰድብ
ከድሃ ሳላብር፤ ከገባር ሳልወግን
ከምድር በረከት፤ ድርሻየን ሳልዘግን
አልሞትም፤
ስሚ!
ልቤ እንደምኞቱ፤ ቢያገኝ እንደምርጫው
ያላማየ ማብቂያ፤ አንቺ ነሽ መቁዋጫው
እና
አገሬን ለቅቄ፤ ልብሽህ ላይ ሳልከትም
በውብ ከንፈርሽ ላይ፤ ከንፈሬን ሳላትም
አልሞትም!
@gGetem
@gGetem
(በእውቀቱ ስዩም)
ስሚ!
እኔ በዚህ ዐለም ፤ብዙ ብሰቃይም
አንድ ሀሙስ የቀረው፤ መስየ ብታይም
አምሮቴን ሳላገኝ፤ሱሴን ሳላከትም
በመሬት ከርስ ውስጥ ፤ገላየን አልከትም
አልሞትም!
ማንም ባልደፈረው፤ መንገድ ሳልገሰግስ
እንደ ንጉስ አይዙር፤ግማሽ ቀን ሳልነግስ
በጠገበው ሳልስቅ፤ ለራበው ሳልደግስ
አልሞትም!
ዝማሜን ሳላወልቅ፤ ያንድበቴን ግድብ
ዙፋን ላይ ሳልሸና፤ ጌቶቼን ሳልሰድብ
ከድሃ ሳላብር፤ ከገባር ሳልወግን
ከምድር በረከት፤ ድርሻየን ሳልዘግን
አልሞትም፤
ስሚ!
ልቤ እንደምኞቱ፤ ቢያገኝ እንደምርጫው
ያላማየ ማብቂያ፤ አንቺ ነሽ መቁዋጫው
እና
አገሬን ለቅቄ፤ ልብሽህ ላይ ሳልከትም
በውብ ከንፈርሽ ላይ፤ ከንፈሬን ሳላትም
አልሞትም!
@gGetem
@gGetem
ሢቃተ ሆሄ
ጬኸት....
ጬኸት
ጬኸት
የሆሄያት ሲቃ
የሙሾ ድለቃ
ቃል ለዛውን ቢያጣ
ቅኔ ወዙ ቢነጣ
ሆሄያት ታመሙ
ሢቃ ድምጽ አሰሙ
ያን ጊዜ
ገጣሚ ብእሩን ኣነሳ፤ከሆሄያት ድርድር
ከህመም ከሢቃ፤ስንኙን ሊያዋቅር
ደራሲ ኣነባ
የሆሄያት እንባ
ከወረቀቱ ላይ
ከነተበው ልቡ፤ከዘመኑ ሲሳይ
ደራሲ ኣነባ
የሆሄያት እንባ
ህይወቱን ሊገርፈው
በቅኔ ሊዘርፈው
ሆሄ ደረደረ
ቃላት ሰበጠረ
ሀረግ ኣዋቀረ
ሆሄያትም ታመሙ
ሢቃ ድምጽ ኣሰሙ
ስንኙም ቤት መታ
ግና የ ማታ ማታ
ሚስኪኑ ገጣሚ ቤት ለመታው ግጥሙ
በቆሰሉ ሆሄያት ህመም በሚያዜሙ
ፊደል ኣቀናብሮ በቃል በዘመነ
ቤት ለመታ ግጥሙ
ቤት መድፊያ እሱ ሆነ
@gGetem
@gGetem
@gGetem
ጬኸት....
ጬኸት
ጬኸት
የሆሄያት ሲቃ
የሙሾ ድለቃ
ቃል ለዛውን ቢያጣ
ቅኔ ወዙ ቢነጣ
ሆሄያት ታመሙ
ሢቃ ድምጽ አሰሙ
ያን ጊዜ
ገጣሚ ብእሩን ኣነሳ፤ከሆሄያት ድርድር
ከህመም ከሢቃ፤ስንኙን ሊያዋቅር
ደራሲ ኣነባ
የሆሄያት እንባ
ከወረቀቱ ላይ
ከነተበው ልቡ፤ከዘመኑ ሲሳይ
ደራሲ ኣነባ
የሆሄያት እንባ
ህይወቱን ሊገርፈው
በቅኔ ሊዘርፈው
ሆሄ ደረደረ
ቃላት ሰበጠረ
ሀረግ ኣዋቀረ
ሆሄያትም ታመሙ
ሢቃ ድምጽ ኣሰሙ
ስንኙም ቤት መታ
ግና የ ማታ ማታ
ሚስኪኑ ገጣሚ ቤት ለመታው ግጥሙ
በቆሰሉ ሆሄያት ህመም በሚያዜሙ
ፊደል ኣቀናብሮ በቃል በዘመነ
ቤት ለመታ ግጥሙ
ቤት መድፊያ እሱ ሆነ
@gGetem
@gGetem
@gGetem
👍2
ሰላምን ፈለጋ
🦗🦗🦗🦗🦗🦗🦗
በሰወች መካከል ትልቅ ክፍተት መጣ
ትንሽ ተወድሶ ትልቅ ክብር አጣ
አገሬ ኢትዮጵያ ሰላም ላንች ይሁን
ፈቅር ይለግሰን ቸሩ አምላካችን
መሪና ተመሪ መገዱ ጠፍቷቸው
ተመሪ አወቀና መገድ ሊነግራቸው
መሪ አልሰማም አለ መች ተቀበላቸው
አተ መሪ ሁነህ ሰላምን ካሳጣህ
በምን ቀመር ሆኖ አተን ልከትልህ
የወድማችን ደም አተን እየጠጣህ
እናት ደስታን ስትል ሀዘን አሸክመህ
በልጆቿ ሀዘን እናት ደም አልቀሳ
በየትኛው መገድ ላተ እጅ ልሳ
አዉቃለው ታውቃለህ መገዱ መች ጠፋህ
አልገባኝም እኔ...
እናት መግደሉ ነው ?
እምነት ማጥፋቱ ነው?
ወይስ አገር መሸጥ..?
ነው ያተ ስልጣንህ?
አልገባኝም እኔ በምን ልጠይቅህ
ተምሪያለው ብለህ ማዕረግ ተሰጠሀል
እመራለው ብለህ ዳኝነት ይዘሀል
ግን እዴት መረሀው እስኪ ልጠይቅህ
ደምን እያፈሰስክ
እናት እያስለቅስክ
ሰላም ስጠን ሲሉህ ጀግናን እየረሸክ
ይህ ነው ሀላፊነት በምን ልጠይቅህ
ሰላምን ፍለጋ ቢመጣ ትልቁ ወድሜ
እረሽን እሚባል ትንሹ ወድሜ
በምን መልኩ ይሆን እርቁ የሚሆነው
ታናሽና ታላቅ እያጋደልክ ነው
ይህ ነዉ ወይ መሪነት?
እስኪ ልጠይቅህ
ተመሪነህ ብለህ አትናቀኝ እባክህ
ለህዝቤ ነጻነት መገዱን ልገርህ
ነፍጠኛነው ብለህ ወድም ከማሰረሸን
አዴ አድምጠኝና ሰላም ይሰፈንልን....
@gGetem
@gGetem
🦗🦗🦗🦗🦗🦗🦗
በሰወች መካከል ትልቅ ክፍተት መጣ
ትንሽ ተወድሶ ትልቅ ክብር አጣ
አገሬ ኢትዮጵያ ሰላም ላንች ይሁን
ፈቅር ይለግሰን ቸሩ አምላካችን
መሪና ተመሪ መገዱ ጠፍቷቸው
ተመሪ አወቀና መገድ ሊነግራቸው
መሪ አልሰማም አለ መች ተቀበላቸው
አተ መሪ ሁነህ ሰላምን ካሳጣህ
በምን ቀመር ሆኖ አተን ልከትልህ
የወድማችን ደም አተን እየጠጣህ
እናት ደስታን ስትል ሀዘን አሸክመህ
በልጆቿ ሀዘን እናት ደም አልቀሳ
በየትኛው መገድ ላተ እጅ ልሳ
አዉቃለው ታውቃለህ መገዱ መች ጠፋህ
አልገባኝም እኔ...
እናት መግደሉ ነው ?
እምነት ማጥፋቱ ነው?
ወይስ አገር መሸጥ..?
ነው ያተ ስልጣንህ?
አልገባኝም እኔ በምን ልጠይቅህ
ተምሪያለው ብለህ ማዕረግ ተሰጠሀል
እመራለው ብለህ ዳኝነት ይዘሀል
ግን እዴት መረሀው እስኪ ልጠይቅህ
ደምን እያፈሰስክ
እናት እያስለቅስክ
ሰላም ስጠን ሲሉህ ጀግናን እየረሸክ
ይህ ነው ሀላፊነት በምን ልጠይቅህ
ሰላምን ፍለጋ ቢመጣ ትልቁ ወድሜ
እረሽን እሚባል ትንሹ ወድሜ
በምን መልኩ ይሆን እርቁ የሚሆነው
ታናሽና ታላቅ እያጋደልክ ነው
ይህ ነዉ ወይ መሪነት?
እስኪ ልጠይቅህ
ተመሪነህ ብለህ አትናቀኝ እባክህ
ለህዝቤ ነጻነት መገዱን ልገርህ
ነፍጠኛነው ብለህ ወድም ከማሰረሸን
አዴ አድምጠኝና ሰላም ይሰፈንልን....
@gGetem
@gGetem
<
...........................................ሴናዬ✍
ዝም ብዬ ሳስተውልሽ ...
ኤሊያስ የገጠመላት ያቺን እፁብ አስታወሺኝ
በቃል ብቻ የማውቃትን በእውን መተሽ አሳየሺኝ
ባላውቃትም ባላያትም ፍፁም በቁም ባልኖራትም
ኤሊያስ ግን ያሰባትን ሳይከትባት አልተዋትም
...........................................
ሳስተውልሽ እንዳመልሽ ስበት መልክሽ ወሰወሰኝ
ላንቺ ሲገጥም አንቺን ሲሰኝ ባይኔ መጣ አስታወሰኝ
የኖራትን ያወቃትን አጣጥሞ መቼ ቀረ
ገጠመላት አዜመላት ስሜት ምቱን በብራናው አጠቆረ
...........................................
ደሞ ደሞ..
ሳስተውልሽ ዘውድ አክሊልን ትጠሪያለሽ
ሀያል ስሜት በልብ ላይ ትጭሪያለሽ
ልክ እንደርሱ ሙቀት ውበት እስካርፕም ነሽ
የርሱን ግጥም ትመስያለሽ
.........................................
ሳስተውልሽ ....
የኬቢሻን ጥልቅ ግጥም
እንደ በላይ በቀለ ወያ የምትጥም
እንደ ጋሽ ደበበ ቀለም የሰፋች
እንደ ኤፍሬም ስዩም የረጋች
እንደ ጋሽ ፀጋዬ ፅሁፍ የጦፈች
በውበት ደምቃ ነብስ ያጠፋች
ያለማች
ሁሉም የገጠመላት ሁሉም ያነበነባት
በቃል ቅኔ ግጥም አርጎ የፈጠራት
.......................................
ኤላን የናፈቀችው
አስቱን ያሸፈተችው
ዘውድን የማረከችው
ኬቢን የታመነቺው
በላይን ያሳመመችው
ጋሽ ደቤን የናፈቀችው
ጋሽ ፀጋዬን የጠበቀችው
እርሷን ሴት ትመስያለሽ ጠቢቦች የተቀኙላት በደስታ በሂወት ፍሬ
በምኞት በእምባና ናፍቆት ሀያሎች የወደቁልሽ መሰልሺኝ ተበታኝ ጥሬ
በሀሳብ ቅዠት ነበልባል ታውረው የሚከተሉሽ
ዝም ብዬ ሳስተውልሽ ላንቺ ነው የሚገጥሙልሽ !
አንቺን ነው መሰል የፃፉሽ.....
@gGetem
@gGetem
<< ሳስ ተው ልሽ >>>
...........................................ሴናዬ✍
ዝም ብዬ ሳስተውልሽ ...
ኤሊያስ የገጠመላት ያቺን እፁብ አስታወሺኝ
በቃል ብቻ የማውቃትን በእውን መተሽ አሳየሺኝ
ባላውቃትም ባላያትም ፍፁም በቁም ባልኖራትም
ኤሊያስ ግን ያሰባትን ሳይከትባት አልተዋትም
...........................................
ሳስተውልሽ እንዳመልሽ ስበት መልክሽ ወሰወሰኝ
ላንቺ ሲገጥም አንቺን ሲሰኝ ባይኔ መጣ አስታወሰኝ
የኖራትን ያወቃትን አጣጥሞ መቼ ቀረ
ገጠመላት አዜመላት ስሜት ምቱን በብራናው አጠቆረ
...........................................
ደሞ ደሞ..
ሳስተውልሽ ዘውድ አክሊልን ትጠሪያለሽ
ሀያል ስሜት በልብ ላይ ትጭሪያለሽ
ልክ እንደርሱ ሙቀት ውበት እስካርፕም ነሽ
የርሱን ግጥም ትመስያለሽ
.........................................
ሳስተውልሽ ....
የኬቢሻን ጥልቅ ግጥም
እንደ በላይ በቀለ ወያ የምትጥም
እንደ ጋሽ ደበበ ቀለም የሰፋች
እንደ ኤፍሬም ስዩም የረጋች
እንደ ጋሽ ፀጋዬ ፅሁፍ የጦፈች
በውበት ደምቃ ነብስ ያጠፋች
ያለማች
ሁሉም የገጠመላት ሁሉም ያነበነባት
በቃል ቅኔ ግጥም አርጎ የፈጠራት
.......................................
ኤላን የናፈቀችው
አስቱን ያሸፈተችው
ዘውድን የማረከችው
ኬቢን የታመነቺው
በላይን ያሳመመችው
ጋሽ ደቤን የናፈቀችው
ጋሽ ፀጋዬን የጠበቀችው
እርሷን ሴት ትመስያለሽ ጠቢቦች የተቀኙላት በደስታ በሂወት ፍሬ
በምኞት በእምባና ናፍቆት ሀያሎች የወደቁልሽ መሰልሺኝ ተበታኝ ጥሬ
በሀሳብ ቅዠት ነበልባል ታውረው የሚከተሉሽ
ዝም ብዬ ሳስተውልሽ ላንቺ ነው የሚገጥሙልሽ !
አንቺን ነው መሰል የፃፉሽ.....
@gGetem
@gGetem
🥰1
ውሸት ነው በይኝ፡፡
እንደሰው ተወድጄ ተከበሬ የኖርኩበት ቀን ትዝ አይለኝም፡፡
ከሰው ጋር ራሴን አላወዳድርም አልልሽም፡፡
ካልተወዳርኩ ደስታዬ ሀዘኔ ከየት ይመነጫል፡፡ ከሰው አነስኩ ይሉ የለ እናቶች እንኳን፡፡ ከሰው እንዳላንስ ተመክሬ ተዘክሬ ነው ከእናቴ ቤት የተሞሸረኩት ለዓለም የተዳርኩት፡፡
፡
፡
ያለንፅፅር ወደድኩህ ስትይኝ የደነገጥኩት ለዛም ነው፡፡ በምን አቅምሽ ቻልሽው፡፡ አለማወዳደርን አለማነፃፀርን፡፡ ወይስ Ego የሚሉትን ጣጣ እንደገላሽ እጣቢ ደፋሽው?
:
:
ውሸት ነው በይኝ፡፡ እኔን እየነካሽ የሰማሽው ሙዚቃ ምንድነው?
ትዝታ?
ገና መቼ ኖሬና፡፡
አንቺሆዬ?
እኔ ሆዬ የደረጃ ምረኮኛ የፉክክር ባርያ ነኝ፡፡
አምባሰል?
መብሰልሰል መቁሰል ....በነገር መብሰል፡፡
ባቲ?
እንደሆንኩ ታውቂያለሽ መዋቲ፡፡
.
.
ታዲያ ምን ሰማሽ ታዲያ ምን ነካሽና ወድሀለሁ አልሽ፡፡
ተይ አታስክሪኝ፡፡ የኖርኩበትን የእሽቅድምድም ሕይወት ፉርሽ አታርጊብኝ፡፡
እያፎካከርሽ ውደጅኝ፡፡
እያወዳደርሽ አልምጅኝ፡፡
፡
፡
አፈቅርሻለሁ
ከሁሉም አስበልጬ
እናፍቅሻለሁ
ከሁሉም መርጬ
እጠራሻለሁ
አንቺን ብቻ ውጬ፡፡
፡
፡
ያለውድድር ያለንፅፅር መውደድም መወደድም ዓለም አይችልበትም፡፡
አንቺ እንዴት
@gGetem
@gGetem
እንደሰው ተወድጄ ተከበሬ የኖርኩበት ቀን ትዝ አይለኝም፡፡
ከሰው ጋር ራሴን አላወዳድርም አልልሽም፡፡
ካልተወዳርኩ ደስታዬ ሀዘኔ ከየት ይመነጫል፡፡ ከሰው አነስኩ ይሉ የለ እናቶች እንኳን፡፡ ከሰው እንዳላንስ ተመክሬ ተዘክሬ ነው ከእናቴ ቤት የተሞሸረኩት ለዓለም የተዳርኩት፡፡
፡
፡
ያለንፅፅር ወደድኩህ ስትይኝ የደነገጥኩት ለዛም ነው፡፡ በምን አቅምሽ ቻልሽው፡፡ አለማወዳደርን አለማነፃፀርን፡፡ ወይስ Ego የሚሉትን ጣጣ እንደገላሽ እጣቢ ደፋሽው?
:
:
ውሸት ነው በይኝ፡፡ እኔን እየነካሽ የሰማሽው ሙዚቃ ምንድነው?
ትዝታ?
ገና መቼ ኖሬና፡፡
አንቺሆዬ?
እኔ ሆዬ የደረጃ ምረኮኛ የፉክክር ባርያ ነኝ፡፡
አምባሰል?
መብሰልሰል መቁሰል ....በነገር መብሰል፡፡
ባቲ?
እንደሆንኩ ታውቂያለሽ መዋቲ፡፡
.
.
ታዲያ ምን ሰማሽ ታዲያ ምን ነካሽና ወድሀለሁ አልሽ፡፡
ተይ አታስክሪኝ፡፡ የኖርኩበትን የእሽቅድምድም ሕይወት ፉርሽ አታርጊብኝ፡፡
እያፎካከርሽ ውደጅኝ፡፡
እያወዳደርሽ አልምጅኝ፡፡
፡
፡
አፈቅርሻለሁ
ከሁሉም አስበልጬ
እናፍቅሻለሁ
ከሁሉም መርጬ
እጠራሻለሁ
አንቺን ብቻ ውጬ፡፡
፡
፡
ያለውድድር ያለንፅፅር መውደድም መወደድም ዓለም አይችልበትም፡፡
አንቺ እንዴት
@gGetem
@gGetem
👏1
..............
የተራቡ ነፍሶች፤ፍቅርን የተጠሙ
የደከሙ ጆሮ፤ልብን የሚሰሙ
የታረዙ ኣይኖች፤ከውበት የሸሹ
የጎደፈ ቆዳ፤በኑሮ የቆሸሹ
ደብዛዛ ኮከቦች፤ያደመቁት ሰማይ
ከዚህ ሁሉ መሀል፤ቆንጆ ሴት ኣማላይ
ውበት ለራበው ዓይን
ሀሴት የምትመግብ
ፍቅር ለጠማው ጆሮ
የነፍስ ጥኡም ዜማ፤የህሊና ምግብ
ለጎደፈ ገላ፤የዘላለም ኣልባስ
ብርሀን እንደ ኮከብ፤ከጨለማው እራስ
ብቻ ግን ቆንጆ ሴት
ከተመሳቀለ የህይወት ሸራ ላይ
ምንም ቢሸሽጓት፤ጎልታ የምትታይ
ብርሀን ያልሆነች፤ወይንም ጨለማ
ከሁሉም ለሁሉም፤ጋር የምትስማማ
ቆንጆ ሴት ኣማላይ
ጉድፍ ከበዛበት፤የኑሮ ሸራ ላይ
ኣልባስ ሆና ልትኖር
ከጎደፈ ገላው፤ከፈገግታው ሰማይ
.
..
ወደሱ ተጠጋች፤ወደ ግራ ጎኑ
ካለሷ ላለፈው፤ለባከነው ቀኑ
ዋስ እንኳ ባትሆን፤ለሀዘኑ ጠበቃ
ከእቅፋ እንዲደበቅ፤ኣቀፈችው ኣጥብቃ
ምን ኣይነት መክሊት ነው፤እንዴት ያለ ጸጋ
ህመሜ የሚፈወስ፤ከእቅፋ ስጠጋ
የምን ሀዘን ስቃይ
በፍቅር ልንሳፈፍ፤ከደመናው በላይ
ከኑሮ ሸራ ላይ
የምንመኘውን ስእል፤ስሎ ማየት
ከረሀብ
ከሀዘን
ከችግር መለየት
ምን ያለ ሀይል ነው፤እንጃ ግን ኣላቅም
ብቻ ግን እቅፋን፤ይዛለው ኣለቅም
ልክ እንደ ክርስቶስ
እንደ ሀዲስ ኪዳን
እንዴት መታደል ነው
በእቅፎቿ መዳን
@gGetem
@gGetem
@gGetem
የተራቡ ነፍሶች፤ፍቅርን የተጠሙ
የደከሙ ጆሮ፤ልብን የሚሰሙ
የታረዙ ኣይኖች፤ከውበት የሸሹ
የጎደፈ ቆዳ፤በኑሮ የቆሸሹ
ደብዛዛ ኮከቦች፤ያደመቁት ሰማይ
ከዚህ ሁሉ መሀል፤ቆንጆ ሴት ኣማላይ
ውበት ለራበው ዓይን
ሀሴት የምትመግብ
ፍቅር ለጠማው ጆሮ
የነፍስ ጥኡም ዜማ፤የህሊና ምግብ
ለጎደፈ ገላ፤የዘላለም ኣልባስ
ብርሀን እንደ ኮከብ፤ከጨለማው እራስ
ብቻ ግን ቆንጆ ሴት
ከተመሳቀለ የህይወት ሸራ ላይ
ምንም ቢሸሽጓት፤ጎልታ የምትታይ
ብርሀን ያልሆነች፤ወይንም ጨለማ
ከሁሉም ለሁሉም፤ጋር የምትስማማ
ቆንጆ ሴት ኣማላይ
ጉድፍ ከበዛበት፤የኑሮ ሸራ ላይ
ኣልባስ ሆና ልትኖር
ከጎደፈ ገላው፤ከፈገግታው ሰማይ
.
..
ወደሱ ተጠጋች፤ወደ ግራ ጎኑ
ካለሷ ላለፈው፤ለባከነው ቀኑ
ዋስ እንኳ ባትሆን፤ለሀዘኑ ጠበቃ
ከእቅፋ እንዲደበቅ፤ኣቀፈችው ኣጥብቃ
ምን ኣይነት መክሊት ነው፤እንዴት ያለ ጸጋ
ህመሜ የሚፈወስ፤ከእቅፋ ስጠጋ
የምን ሀዘን ስቃይ
በፍቅር ልንሳፈፍ፤ከደመናው በላይ
ከኑሮ ሸራ ላይ
የምንመኘውን ስእል፤ስሎ ማየት
ከረሀብ
ከሀዘን
ከችግር መለየት
ምን ያለ ሀይል ነው፤እንጃ ግን ኣላቅም
ብቻ ግን እቅፋን፤ይዛለው ኣለቅም
ልክ እንደ ክርስቶስ
እንደ ሀዲስ ኪዳን
እንዴት መታደል ነው
በእቅፎቿ መዳን
@gGetem
@gGetem
@gGetem
👍1
............
ሳሚኝ እና ልዳን፤ዳሺኝ በመዳፍሽ
ፊደል አቁስሎኛል፤አትሸንግይኝ ባፍሽ
ነካኪው ገላዬን፤ያካሌን ጉዳንጉድ
ኣፌ ቃላት ይርሳ፤እንጩህ እንደጉድ
ዳሺኝ እና ልንቃ፤በድን ነው ህይወቴ
ኣዝምማ ከብዳለች፤የወረስኳት ቤቴ
ኣላወድስሽም በሽንገላ በቃላት
ሆድሽን ላያባባው፤ነፍሴን ላይደልላት
ሀጥያት ነው ቢሉንም፤ካህንና ቄሱ
ተይ ጽድቁን ለነሱ
ይልቅ ለኔና ኣንቺ
ሳሚኝ እና ልዳን፤ዳሺው ኣካላቴን
የልቡን ኣያቅም፤ኣትስሚ ኣንድበቴን
ቃሉን እንጠየፍ፤ልናቀው ትዛዙን
በነገና ዛሬ ቀናት ፍቺ የገዙን
ሆነው እስከሚያዩት፤ደርሰው በኛ ቦታ
ሀጥያትን እንውደድ፤ሰው እንሁን ላፍታ
ልዳሰው ገላሽን፤ያካልሽን ጉዳንጉድ
ሳሚኝ እና ልዳን፤ልሳምሽ እንደጉድ
ፍቅር የጸነሰው፤ዝሙት እንደማይወልድ
ተዳሩ ቢሉ እንኳ፤መዳራት ለነሱ
በረከሰ ኣንድበት፤ስምሽን ለሚያረክሱ
ባይገባቸው እንጂ የመሳምሽ ምሱ
ጽድቁን ተይ ለነሱ
@gGetem
@gGetem
@gGetem
ሳሚኝ እና ልዳን፤ዳሺኝ በመዳፍሽ
ፊደል አቁስሎኛል፤አትሸንግይኝ ባፍሽ
ነካኪው ገላዬን፤ያካሌን ጉዳንጉድ
ኣፌ ቃላት ይርሳ፤እንጩህ እንደጉድ
ዳሺኝ እና ልንቃ፤በድን ነው ህይወቴ
ኣዝምማ ከብዳለች፤የወረስኳት ቤቴ
ኣላወድስሽም በሽንገላ በቃላት
ሆድሽን ላያባባው፤ነፍሴን ላይደልላት
ሀጥያት ነው ቢሉንም፤ካህንና ቄሱ
ተይ ጽድቁን ለነሱ
ይልቅ ለኔና ኣንቺ
ሳሚኝ እና ልዳን፤ዳሺው ኣካላቴን
የልቡን ኣያቅም፤ኣትስሚ ኣንድበቴን
ቃሉን እንጠየፍ፤ልናቀው ትዛዙን
በነገና ዛሬ ቀናት ፍቺ የገዙን
ሆነው እስከሚያዩት፤ደርሰው በኛ ቦታ
ሀጥያትን እንውደድ፤ሰው እንሁን ላፍታ
ልዳሰው ገላሽን፤ያካልሽን ጉዳንጉድ
ሳሚኝ እና ልዳን፤ልሳምሽ እንደጉድ
ፍቅር የጸነሰው፤ዝሙት እንደማይወልድ
ተዳሩ ቢሉ እንኳ፤መዳራት ለነሱ
በረከሰ ኣንድበት፤ስምሽን ለሚያረክሱ
ባይገባቸው እንጂ የመሳምሽ ምሱ
ጽድቁን ተይ ለነሱ
@gGetem
@gGetem
@gGetem
ልጠብቅሽ?!
ትመጫለሽ ብይ ቆማለው ከመንገድ
በአንቺ ተስፋ ቆርጭ አልሄድ
የፍቅራችንን ትላንት እያሰብኩኝ
በትላንትናችን ነጋችንን እያለምኩኝ
ግን አንቺ ጥለሽኝ ሄድሽ
እጠብቅሻለው እያልኩኝ ትመጫለሽ
እዛው ነኝ ጥለሽኝ የሄድሽበት ቦታ
አለ ልቤ በፍቅርሽ እደተረታ
ትመጫለሽ እያልኩኝ ከዛሬ ነገ
እደምትመለሽ ልቤ ተስፍ እያደረገ
እዛው ነኝ የቆምንበት ቦታ
ልቤ አንቺንስ በማንም አይተካ
ብያደክመኝም መቆሙ ከመንገድ
ብሉኝም ሄዳለች አንተ ሄድ
እጠብቅሻለው እዛው ቦታ ላይ ሁኝ
እደምትመለሽ መንገዱን አምኝ
@gGetem
@gGetem
@gGetem
ትመጫለሽ ብይ ቆማለው ከመንገድ
በአንቺ ተስፋ ቆርጭ አልሄድ
የፍቅራችንን ትላንት እያሰብኩኝ
በትላንትናችን ነጋችንን እያለምኩኝ
ግን አንቺ ጥለሽኝ ሄድሽ
እጠብቅሻለው እያልኩኝ ትመጫለሽ
እዛው ነኝ ጥለሽኝ የሄድሽበት ቦታ
አለ ልቤ በፍቅርሽ እደተረታ
ትመጫለሽ እያልኩኝ ከዛሬ ነገ
እደምትመለሽ ልቤ ተስፍ እያደረገ
እዛው ነኝ የቆምንበት ቦታ
ልቤ አንቺንስ በማንም አይተካ
ብያደክመኝም መቆሙ ከመንገድ
ብሉኝም ሄዳለች አንተ ሄድ
እጠብቅሻለው እዛው ቦታ ላይ ሁኝ
እደምትመለሽ መንገዱን አምኝ
@gGetem
@gGetem
@gGetem
የሰው ስህተት
ተቀይርክ አሉኝ ተገርመው
አፍ በእጅ ያዙ ተደንቀው
አንተ አይደለህም ይሉኛል
አዎ አይደለውም እኔንማ ገለውኛል
መቀየሬ ገረማቸው
ገለው ክደው ሰባብረውኝ ምን ሆነሀል ጥያቄአቸው
እራሳቸው መልሴ ናቸው
አልናገር አልጋገር
ዝምም አልል እሰጣለው መልስ ነገር
አልነበርክም እንዲ አልሆንክም ለሚሉኝም
አዎ አልሆንኩም አልነበርኩም ግን አሁንም ባዶ አልሆንኩም
አዎ ነበርኩ ሳልሰበር
ለጥያቄው መልሴ ነበር
የለም ዳኛ ሀቃቢም ህግ
የኔን ስሜት ሚደነግግ
ማንም ምንም አይሰማው
ማንም ቢሆን የራሱን ነው የሚሰማው
የለም አንድም የበደልኩት
ነክሶኝ ሄዶ ያጎረስኩት
ደግሞ አማኝ እንደካድኩት
ትቶኝ ሄዶ ይናገራል እንደተውኩት
ከሰው ስህተት ከብረት ዝገት አይጠፋም ግን ይመራል!
መሳሳቱም መዛዛጉም ከአንገት በላይ ግን ያቅራል
ሁሉም ፃድቅ ሁሉ በጎ
እኔን ክፉ ሰው አድርጎ
ሁሉም አለው የራሱ ልክ
ለፈፀመው ሰበብ ምክኒያት የሚያላክክ
ላንዱ በደል ላንዱ እውነት
ልክነት ነው የሰው ስህተት
@gGetem
@gGetem
👍3🗿1
ቋጠሮሽ
ዞሮ ዞሮ ከሀገር ዞሬ ዞሬ ካንቺ
ካንቺ ሚስበኝን ቋጠሮሽን ፍቺ
ከተሰደዱበት ሀገር ቢመለሱ
እንደው ተጓዙ እንጂ ድሮስ መች ደረሱ
እንደ አፈሯ ሽታ እትብቴ ከተቀበረባት እኩል
እረቄ ከሄድኩት ትጎትተኛለች በትዝታ በኩል
ሀገርስ እናት ነች ብወድቅ ባላገግም
አልጋ ባትሰጠኝ በረንዳን አትነፍግም
ያንቺ ግን ጥላ ነው ወደ ፀሀይ ስዞር
ከኋላ ይወድቃል
ተፈጥሮው ነውና ስርቀው ይቀርባል
ስቀርበው ይርቃል
የኔ ፍላጎቴ መራቅ ብቻ ካንቺ
በቃ ልሂድበት ቋጠሮሽን ፍቺ
የታመመን ትናንት ዛሬ ባማርርም
መድረስ ከሌለበት ነገን አልገብርም
@gGetem
@gGetem
@gGetem
ዞሮ ዞሮ ከሀገር ዞሬ ዞሬ ካንቺ
ካንቺ ሚስበኝን ቋጠሮሽን ፍቺ
ከተሰደዱበት ሀገር ቢመለሱ
እንደው ተጓዙ እንጂ ድሮስ መች ደረሱ
እንደ አፈሯ ሽታ እትብቴ ከተቀበረባት እኩል
እረቄ ከሄድኩት ትጎትተኛለች በትዝታ በኩል
ሀገርስ እናት ነች ብወድቅ ባላገግም
አልጋ ባትሰጠኝ በረንዳን አትነፍግም
ያንቺ ግን ጥላ ነው ወደ ፀሀይ ስዞር
ከኋላ ይወድቃል
ተፈጥሮው ነውና ስርቀው ይቀርባል
ስቀርበው ይርቃል
የኔ ፍላጎቴ መራቅ ብቻ ካንቺ
በቃ ልሂድበት ቋጠሮሽን ፍቺ
የታመመን ትናንት ዛሬ ባማርርም
መድረስ ከሌለበት ነገን አልገብርም
@gGetem
@gGetem
@gGetem
☃1💋1
..............
ከማበዴ በፊት፤ኣንድ ቃል ልንገርሽ
ላንቺ ብዬ ኣይደለም፤ጨርቅ የምቀድልሽ
ስለተውሺኝ ብዬ
መራቅ መገፋቴን፤መቻል ስላቃተኝ
ፍቅርሽ እንደ ቅዘት፤ስለሚያቃትተኝ
ከምቀደው ልብሴ፤ከገላዬ ካለው
ትዝታሽ ብቻ ነው፤በውብ የተሳለው
ጠረንሽ ነው ያለ፤ከገላ ከጨርቄ
የሄድሽ ቀን ጣልኩት፤ሀፍረቴን ኣውልቄ
ከማበዴ በፊት
ኣንድ ቃል ለናገር፤ፍቅርዬ ባንቺ ፊት
ኡ ኡ ብዬ ብጮህ
እንዳትጠብቂ ከጬኀቴ መሀል
ከቶም ስምሽ የለም
የኔ ውድ የኔ ኣለም
ለኔ ኣይነቱ ኣፍቃሪ
እብደት ጤንነት ነው ከእስሩ መፈቻ
ኣንቺን አንቺን ብቻ
ማለቱን እረስቶ
ፍቅርን እንደጨርቅ፤ከገላው ለይቶ
ከገረባው መሀል
ተግቶ ሊፈልጋት፤የጠፋችው ፍቅሩን
ቅጠሏ ኣመርቅኖ
ግንዷ የበከለ ሰማይና ምድሩን
ቅጠሏ ፍቅር ነው፤ሙትን የሚባብል
ግንዷ ደሞ ግፍሽ፤በቁም የሚገድል
ለዚህ ይሆን ? እብድ ሁሉ
ገረባ የሚያነሳ፤ገረባ የሚጥለው
የጠፋችው ፍቅሩን፤ስለምትመስለው
እናም ፍቅርዬ
ላብድ ስለሆነ እንዳትጸጸቺ
ኣንቺን ፍለጋ ነው፤የማበዴ ፍቺ
ከሰው መሀል ባጣሽ፤ካትሮንስ ባትገኚ
ኣብጄ ፈለኩሽ፤ገረባ ስትሆኚ
@gGetem
@gGetem
@gGetem
ከማበዴ በፊት፤ኣንድ ቃል ልንገርሽ
ላንቺ ብዬ ኣይደለም፤ጨርቅ የምቀድልሽ
ስለተውሺኝ ብዬ
መራቅ መገፋቴን፤መቻል ስላቃተኝ
ፍቅርሽ እንደ ቅዘት፤ስለሚያቃትተኝ
ከምቀደው ልብሴ፤ከገላዬ ካለው
ትዝታሽ ብቻ ነው፤በውብ የተሳለው
ጠረንሽ ነው ያለ፤ከገላ ከጨርቄ
የሄድሽ ቀን ጣልኩት፤ሀፍረቴን ኣውልቄ
ከማበዴ በፊት
ኣንድ ቃል ለናገር፤ፍቅርዬ ባንቺ ፊት
ኡ ኡ ብዬ ብጮህ
እንዳትጠብቂ ከጬኀቴ መሀል
ከቶም ስምሽ የለም
የኔ ውድ የኔ ኣለም
ለኔ ኣይነቱ ኣፍቃሪ
እብደት ጤንነት ነው ከእስሩ መፈቻ
ኣንቺን አንቺን ብቻ
ማለቱን እረስቶ
ፍቅርን እንደጨርቅ፤ከገላው ለይቶ
ከገረባው መሀል
ተግቶ ሊፈልጋት፤የጠፋችው ፍቅሩን
ቅጠሏ ኣመርቅኖ
ግንዷ የበከለ ሰማይና ምድሩን
ቅጠሏ ፍቅር ነው፤ሙትን የሚባብል
ግንዷ ደሞ ግፍሽ፤በቁም የሚገድል
ለዚህ ይሆን ? እብድ ሁሉ
ገረባ የሚያነሳ፤ገረባ የሚጥለው
የጠፋችው ፍቅሩን፤ስለምትመስለው
እናም ፍቅርዬ
ላብድ ስለሆነ እንዳትጸጸቺ
ኣንቺን ፍለጋ ነው፤የማበዴ ፍቺ
ከሰው መሀል ባጣሽ፤ካትሮንስ ባትገኚ
ኣብጄ ፈለኩሽ፤ገረባ ስትሆኚ
@gGetem
@gGetem
@gGetem
🥰1