ፍቅርን ፈራን
(ሎሬት ፀጋዬ ገ/መድህን)
ፍቅርን ፈራን መቀራረብ ፈራን
እንዳልተዛመድን እንዳልተዋለድን
ፈርተን መዋደድን ጉርብትናን ናድን
እኛነትን ትተን እኔነት ለመድን
“ፈራን”
ፍቅርን ፈራን ጥላቻን ሰራን ብቸኝነት ጠራን
በጋራ ቤታችን አጥር ድንበር ሰራን
“ናቅን”
በልዩነት ደምቀን ያልኖርን ያህል አንድም ቀን
እልህ ተናነቅን
“ናቅን”
መቻቻልን ናቅን ለፀብ አሟሟቅን
ለአመፅ ስንነሳ ለሰላም ወደቅን
አገር ስትቃጠል ከዳር ሆነን ሞቅን
“ጠላን”
መወያየት ጠላን መነጋገር ጠላን
መደማመጥ ጠፍቶ መነቋቆር በዝቶ
መናናቅ በርክቶ
መመካከርን ስንረሳ መከባበርን ስንረሳ
እጃችን በወንድማችን ላይ ዱላ አነሳ
የቃየል ምቀኝነት በልባችን ላይ ነግሳ
“ራቅን”
የተስፋ ሻማችን ተለኩሶ
ወጋገኑ መታየት ሲጀምር አድማሱን ጥሶ
እኛ ግን ራቅን ብሩህ ነገን ራቅን
ዛሬን ተጣበቅን ትላንትን ናፈቅን
@gGetem
@gGetem
(ሎሬት ፀጋዬ ገ/መድህን)
ፍቅርን ፈራን መቀራረብ ፈራን
እንዳልተዛመድን እንዳልተዋለድን
ፈርተን መዋደድን ጉርብትናን ናድን
እኛነትን ትተን እኔነት ለመድን
“ፈራን”
ፍቅርን ፈራን ጥላቻን ሰራን ብቸኝነት ጠራን
በጋራ ቤታችን አጥር ድንበር ሰራን
“ናቅን”
በልዩነት ደምቀን ያልኖርን ያህል አንድም ቀን
እልህ ተናነቅን
“ናቅን”
መቻቻልን ናቅን ለፀብ አሟሟቅን
ለአመፅ ስንነሳ ለሰላም ወደቅን
አገር ስትቃጠል ከዳር ሆነን ሞቅን
“ጠላን”
መወያየት ጠላን መነጋገር ጠላን
መደማመጥ ጠፍቶ መነቋቆር በዝቶ
መናናቅ በርክቶ
መመካከርን ስንረሳ መከባበርን ስንረሳ
እጃችን በወንድማችን ላይ ዱላ አነሳ
የቃየል ምቀኝነት በልባችን ላይ ነግሳ
“ራቅን”
የተስፋ ሻማችን ተለኩሶ
ወጋገኑ መታየት ሲጀምር አድማሱን ጥሶ
እኛ ግን ራቅን ብሩህ ነገን ራቅን
ዛሬን ተጣበቅን ትላንትን ናፈቅን
@gGetem
@gGetem
🔹🔹🔺🔹🔹🔺
ስንት ጊዜ ይፈጃል ምን ያህል አመታት
ስንት ሰዉ ይበቃል ትዝታን ለመርሳት
ምን የሚሉት ጂኒ ካንተ ጋር አሰረኝ💙
የትኛዉ መለኮት በፍቅርህ ጠፈረኝ
በየትኛዉ ጥበብ በየትኛዉ ዘዴ
በየትኛዉ ብልሀት አወከዉ የሆዴን
እንጃ................
ጊዜም መልሱ ጠፋበት መሰለኝ
ካንተ ጋር ይነጉዳል ጥያቄ እያጫረኝ
ስንት ዘመን ቀረኝ
ስንት እድሜ ይተርፈኝ
መቼ ያሳርፈኝ
ትዝታህ ጠቢቡ
ትዝታህ ብልሁ
ትዝታህ ብልጥ ወዳጅ🔻
እያሳሳቀ ነዉ አብሮ ሚያሳቅቀኝ
እያጫወተ ነዉ እድሜዬን የቀጨኝ
ወይ እሱ ይተወኝ ወይ አንተ ደግመህ ና
ትዝታህን ዉሰድ እኔን መልስና።❤️
┄┅┅┄┅✶♥️✶┅┄┅┅┄
@gGetem
@gGetem
ስንት ጊዜ ይፈጃል ምን ያህል አመታት
ስንት ሰዉ ይበቃል ትዝታን ለመርሳት
ምን የሚሉት ጂኒ ካንተ ጋር አሰረኝ💙
የትኛዉ መለኮት በፍቅርህ ጠፈረኝ
በየትኛዉ ጥበብ በየትኛዉ ዘዴ
በየትኛዉ ብልሀት አወከዉ የሆዴን
እንጃ................
ጊዜም መልሱ ጠፋበት መሰለኝ
ካንተ ጋር ይነጉዳል ጥያቄ እያጫረኝ
ስንት ዘመን ቀረኝ
ስንት እድሜ ይተርፈኝ
መቼ ያሳርፈኝ
ትዝታህ ጠቢቡ
ትዝታህ ብልሁ
ትዝታህ ብልጥ ወዳጅ🔻
እያሳሳቀ ነዉ አብሮ ሚያሳቅቀኝ
እያጫወተ ነዉ እድሜዬን የቀጨኝ
ወይ እሱ ይተወኝ ወይ አንተ ደግመህ ና
ትዝታህን ዉሰድ እኔን መልስና።❤️
┄┅┅┄┅✶♥️✶┅┄┅┅┄
@gGetem
@gGetem
❤1👍1
#የጥምቀት_ስንብት
#ሊዮ_ማክ 💔
#የቀጠለ
#የጥምቀት_ስጦታ
"እ....አለኝ... አለኝ"ብዬ እጄን ወደ ኪሴ ስሰደው አንድ ባለ አምስት እና ባለ ሁለት ባለ ሀምሳ የብር ኖት ይዞ ወጣ:ወዲያውኑ አንዱን ሀምሳውን ብር ስሰጣት "አይ ከሌለህ ተወው አስር ብር ብቻ ነው የፈለኩት" አለችኝ፡እኔም ይህን ጥሩ አጋጣሚ ማለፍ ስላልፈለኩ ችግር የለውም አልኩኝ ከዘረጋችው እጇ ላይ እያኖርኩት:ግን በመሀል ምስጋና ይግባት እና በቀሩት አርባ ብሮች ፈንታ እንድቀላቀላቸው ስትጋብዘኝ አላመነታው ወዲያውኑ ነበር የተስማማሁት አብረንም ሔድን አታስተዋወቀችኝ ናርዶስ፣ሳባ፣ኤልሳ ከእኔ ልብ ላይ ደግሞ የቀረችው ቤዛ ነበር ስሟ እንደጨበጥኳት በዚያች ቅስፈት ሳለቃት እድሜ ልኬን እንደያዝኳት ለመኖር ለራሴ ቃል ኪዳን እየገባሁ ያለ ያክል በትኩረት ተመለከትኳት፡እርሷም ሴትነቷ ይዟት እንጂ አንዳች ነገር ውስጧ እንደተፀነሰ ታወቀኝ ከአይኖቿ ላይ....
እና በአንድ እይታ የተጀመረው ትውውቅ፡ እየዋለ ሲያድር አንዳች የጋለ ፍቅር ውስጥ ከተትን ብዙ ነገሮችም በመሀከላችን ለመፈጠር እና ለመከናወን አልፈጀብንም በሰዓቱ ለአመታት የምንተዋወቅ ጥንዶች የሆነን ያክል ተሰማን ግን ከአስራ አምስት ቀን በኃላ ፀብ በመሀከላችን ተፈጥሮ ተለያየን።በጓደኛዋ ምክንያት የተጀመረው ትውውቅ መልሶ በጓደኛዋ ተ...ለ...ያ....የ...ን....
www.tgoop.com/gGetem
እናም ዛሬ ከዚህ ሁሉ ነገር መፈጠር በኃላ እንደ ጨው ክምር ሀውልት አድርጎ ያስቀረኝ የእናቴ ንግግር እንዲህ ይል ስለነበረ ነው።
"ፍቄ አየሀት እህትህን የሟቹ የአጎቴ ኪዳን ልጅ እኮ ነች:ለበዓል የአሰላ መጥታለች ብላኝ ነበር እናቷ ና እናናግራት ብላ ልታናግራት መንገዱን ስታቋርጥ፡ እውነታውን ከሰማሁ አንስቶ የፈፀምነውን ያንን ሁሉ ነገር ሳስበው እርሷም ዘመዴ እህቴ መሆኗን ሳውቅ ወሽመጤ ቁርጥ ብሎ ባለሁበት ተተክዬ ቀረሁ ..............
(ጥቆማ👆😟)
ሀሳብ፣ቅሬታ፣ብርታት፣ነቀፌታ ካለ)👇
www.tgoop.com/gGetem
www.tgoop.com/leoyri
#ሊዮ_ማክ 💔
#የቀጠለ
#የጥምቀት_ስጦታ
"እ....አለኝ... አለኝ"ብዬ እጄን ወደ ኪሴ ስሰደው አንድ ባለ አምስት እና ባለ ሁለት ባለ ሀምሳ የብር ኖት ይዞ ወጣ:ወዲያውኑ አንዱን ሀምሳውን ብር ስሰጣት "አይ ከሌለህ ተወው አስር ብር ብቻ ነው የፈለኩት" አለችኝ፡እኔም ይህን ጥሩ አጋጣሚ ማለፍ ስላልፈለኩ ችግር የለውም አልኩኝ ከዘረጋችው እጇ ላይ እያኖርኩት:ግን በመሀል ምስጋና ይግባት እና በቀሩት አርባ ብሮች ፈንታ እንድቀላቀላቸው ስትጋብዘኝ አላመነታው ወዲያውኑ ነበር የተስማማሁት አብረንም ሔድን አታስተዋወቀችኝ ናርዶስ፣ሳባ፣ኤልሳ ከእኔ ልብ ላይ ደግሞ የቀረችው ቤዛ ነበር ስሟ እንደጨበጥኳት በዚያች ቅስፈት ሳለቃት እድሜ ልኬን እንደያዝኳት ለመኖር ለራሴ ቃል ኪዳን እየገባሁ ያለ ያክል በትኩረት ተመለከትኳት፡እርሷም ሴትነቷ ይዟት እንጂ አንዳች ነገር ውስጧ እንደተፀነሰ ታወቀኝ ከአይኖቿ ላይ....
እና በአንድ እይታ የተጀመረው ትውውቅ፡ እየዋለ ሲያድር አንዳች የጋለ ፍቅር ውስጥ ከተትን ብዙ ነገሮችም በመሀከላችን ለመፈጠር እና ለመከናወን አልፈጀብንም በሰዓቱ ለአመታት የምንተዋወቅ ጥንዶች የሆነን ያክል ተሰማን ግን ከአስራ አምስት ቀን በኃላ ፀብ በመሀከላችን ተፈጥሮ ተለያየን።በጓደኛዋ ምክንያት የተጀመረው ትውውቅ መልሶ በጓደኛዋ ተ...ለ...ያ....የ...ን....
www.tgoop.com/gGetem
እናም ዛሬ ከዚህ ሁሉ ነገር መፈጠር በኃላ እንደ ጨው ክምር ሀውልት አድርጎ ያስቀረኝ የእናቴ ንግግር እንዲህ ይል ስለነበረ ነው።
"ፍቄ አየሀት እህትህን የሟቹ የአጎቴ ኪዳን ልጅ እኮ ነች:ለበዓል የአሰላ መጥታለች ብላኝ ነበር እናቷ ና እናናግራት ብላ ልታናግራት መንገዱን ስታቋርጥ፡ እውነታውን ከሰማሁ አንስቶ የፈፀምነውን ያንን ሁሉ ነገር ሳስበው እርሷም ዘመዴ እህቴ መሆኗን ሳውቅ ወሽመጤ ቁርጥ ብሎ ባለሁበት ተተክዬ ቀረሁ ..............
(ጥቆማ👆😟)
ሀሳብ፣ቅሬታ፣ብርታት፣ነቀፌታ ካለ)👇
www.tgoop.com/gGetem
www.tgoop.com/leoyri
Telegram
የሆሄያት ህብር📝📝
ውድ የሆሄያት ህብር ቻናል ቤተሰቦች ስለተቀላቀሉን እናመሰግናለን።👍👍
ቻናላችን፦
👉በግጥም 📔📰📼📼
👉በድርሰት📚📚
👉በትረካ📀🎼
👉በስዕል🃏🃏
👉ወጎች📜📜
👉በአጫጭር ልብ ወለዶች ወደ እናንተ እንደርሳለን።
ለሀሳብ እና አስተያየት
፦ሊዮ ማክ፦ @Leoyri
፦ዮሲ ማን፦ @yosikeman
፦የሪ፦ @yerijo
ወደ ቻናላችን ለመቀላቀል 👉 @gGetem
ቻናላችን፦
👉በግጥም 📔📰📼📼
👉በድርሰት📚📚
👉በትረካ📀🎼
👉በስዕል🃏🃏
👉ወጎች📜📜
👉በአጫጭር ልብ ወለዶች ወደ እናንተ እንደርሳለን።
ለሀሳብ እና አስተያየት
፦ሊዮ ማክ፦ @Leoyri
፦ዮሲ ማን፦ @yosikeman
፦የሪ፦ @yerijo
ወደ ቻናላችን ለመቀላቀል 👉 @gGetem
Forwarded from የሆሄያት ህብር📝📝
ንፍገት
ደራሲ ጆሲ
የሚሆነው አይታወቅምና በርህን አጥብቀህ አትዝጋ ብላ አያቴ ትነግረኝ ነበር። እኔም የእርሷን ምክር አንደ ዶግማ በልቤ ፅላት ፅፌው ይሀው ዛሬ ድርስ በራፌን አልዘጋም። ምሽት ከሆነና እቤት ከሌለው ብቻ ነው በራፌ የሚዘጋው።
ታዲያ ይህ ባህሪዬ ከቤት አልፎ መስሪያ ቤትም ተከትሎኝ ከትሟል። እንደተለመደው በራፌን ገርበብ አድርጌ ስራዬን እየሰራው ሳለ በራፌ ተንኳኳ መሰረት ነበረች። ምንግዜም እርሷ በር ስታንኳኳ ለየት ያለ ስለተ ምት ነበረው። ኳኳ ኳ ኳኳኳ ኳ ታደርግና ጥቂት ትታገሳለች ከዛም ከፍት ከሆነ ትገባለች አልያም ዝግ ከሆነባት ተመልሳ ትሄዳለች ትዕግስቷ የጠብታ ያክል ናት ። እኔም ፀባዮዋን ስለማውቅ መሲ ግቢ አልኩኝ አይኔን ከኮፒተሬ ላይ ሳልነቅል። ለአፍታም የምሰራውን ገታ አድርጌ ቀና ስል መሲ ከክፍሉ ዘልቃ ኖሯል በፈገግታ እንደደመቀች ገዜ እንዴት ውልሃል አለችኝ በቆመችበት ሳለች ። ፈገግታዋ ልብ የሚሰርቅ ነው። መሰረት ከቁመቷ ዘለግ ያለች ቀይ ብርቱካን የምትመስል አጠር ያለ የስፌ ቀሚስ የምታዘወትር አላፊ አግዳሚ ሳይቀር በውበቷ የሚማረክባት ውብ ሴት ናት። መሲ እንዴት ውለሻል ደግሞ ዛሬ ውብ ሆነሻል። ... አይደል አለችና ከእግሯ አንስታ እራሷን ተመልክታ አመሰግናለሁ አለች።
በሁለት እጇቿ ደረታ ላይ ለጥፋ አንዳች መፅሔት የመሰለ የወረቀት ጥራዝ ይዛለች አትኩሬ ተመለከትኩት እውነትም መፅሔት ነበር። አረፍ በይ አልኳት በእጄ ወንበሩን አያመላከትኳት። ፈጥና ተቀመጠች በእጇቿ ይዛው የነበረውን መፅሔት ከፊት ለፊቷ ካለው ጠረፔዛ ላይ አስቀመጠችው። ጥቂት የግል ወሬያችንን ስናወጋ ቆየንና እኔ ምልህ ገዜ አለች የወሬውን አቅጣጫ ለማስቀየር ቀጠለችና ትናንት ትልቅ እንግዳ ነው ያለን አላልኩህም ነበር። ማን እንደ ሆነ ገምት አለች አይን አይኔን እያየች። እኔም ሊሆኑ ይችላሉ ብዬ ያስብኳቸውን ሰዎች ጠቀስኩ። ግን መሳሳቴን ፊቷ ይናገራል። መፅሔቱን ከስቀመጠችበት በማንሳት ተመልከት የዚህ መፅሔት አዘጋጅ የሆነችው ሴት አወካት አለችኝና መፅሔቱን ሰጠችኝ ተቀብያት ማገላበጥ ያዝኩ። እንዴት የምታሳዝን ሴት መሰለችህ በፊት የነበራት የሞራል ልዕልና ከስሞ የአዕምሮ መቃወስ ሁሉ ገጥሟት ሰራም ማቆሟን ባደረኩት ማጣራት ማወቅ ችያለሁ። ብላ ከተቀመጠችበት ተነሳችና ቀሚሷን ወደታች ወደታች እየሳበች ለመንኛውም ይሄንን ልነግርህ ብዬ ነው ብላኝ ወጣች። አፃፃፉም ሆነ የስዕልና የፎቶግራፎቹ አቀማመጥ ልጅ ሳለሁ እቤታች ያሸበርቅበት የነበረውን ጋዜጣ አስታወሰኝ። ትዝ ይለኛል ለሰዓታት የቤታችን ግድግዳ ላይ አፍጥጬ ነበር የምውለው።ፖለቲካ፣እስፖርት፣የሃራጅና የጨረታ እንዲሁም የስራ ቅጥር ማስታወቂያው መዝናኛውም ቢሆን ለንባብ የሚጋብዝ አፃፃፍ ነበራቸው የአዘጋጆቹም ብስለት ይሄ ነው የማይባል ነበር።ከሁሉም ከሁሉም መዝናኛ ላይ ያነበብኩት #ከገፅ 3የዞረ የአንድ ጫማ ሰፊ አሟሟትን የሚያትት ፅሑፍ ጉዳይ መጨረሻውን ፍለጋ ግድግዳው ሳስስ የቆየሁበትን ጊዜ አልረሳውም እስገዛሬ ድረስ በውስጤ መጨረሻው ጥያቄ ሆኖ አለ ለሁሉ ግን ክብር ይገባቸዋል!#
ለሰዓታት ከተጓዝኩቀት የሃሳብ ጎዳና ወደ ዛሬ ተመለስኩ እውነት ነው ክብር ይገባቸዋል። ስንቱን መወደስ የሌለበትን ስናወድስ ክብር ለሚገባቸው ግን ክብርን ነፍገናቸው የት እንደ ወደቁ እንኳን አለማወቃችን ያሳፍራል
ክብር ለሚገባው ክብር እንስጥ!
ለሃሳብ አስተያየት
ጆሲ:@yosikeman
ለመቀላቀል
@gGetem
ደራሲ ጆሲ
የሚሆነው አይታወቅምና በርህን አጥብቀህ አትዝጋ ብላ አያቴ ትነግረኝ ነበር። እኔም የእርሷን ምክር አንደ ዶግማ በልቤ ፅላት ፅፌው ይሀው ዛሬ ድርስ በራፌን አልዘጋም። ምሽት ከሆነና እቤት ከሌለው ብቻ ነው በራፌ የሚዘጋው።
ታዲያ ይህ ባህሪዬ ከቤት አልፎ መስሪያ ቤትም ተከትሎኝ ከትሟል። እንደተለመደው በራፌን ገርበብ አድርጌ ስራዬን እየሰራው ሳለ በራፌ ተንኳኳ መሰረት ነበረች። ምንግዜም እርሷ በር ስታንኳኳ ለየት ያለ ስለተ ምት ነበረው። ኳኳ ኳ ኳኳኳ ኳ ታደርግና ጥቂት ትታገሳለች ከዛም ከፍት ከሆነ ትገባለች አልያም ዝግ ከሆነባት ተመልሳ ትሄዳለች ትዕግስቷ የጠብታ ያክል ናት ። እኔም ፀባዮዋን ስለማውቅ መሲ ግቢ አልኩኝ አይኔን ከኮፒተሬ ላይ ሳልነቅል። ለአፍታም የምሰራውን ገታ አድርጌ ቀና ስል መሲ ከክፍሉ ዘልቃ ኖሯል በፈገግታ እንደደመቀች ገዜ እንዴት ውልሃል አለችኝ በቆመችበት ሳለች ። ፈገግታዋ ልብ የሚሰርቅ ነው። መሰረት ከቁመቷ ዘለግ ያለች ቀይ ብርቱካን የምትመስል አጠር ያለ የስፌ ቀሚስ የምታዘወትር አላፊ አግዳሚ ሳይቀር በውበቷ የሚማረክባት ውብ ሴት ናት። መሲ እንዴት ውለሻል ደግሞ ዛሬ ውብ ሆነሻል። ... አይደል አለችና ከእግሯ አንስታ እራሷን ተመልክታ አመሰግናለሁ አለች።
በሁለት እጇቿ ደረታ ላይ ለጥፋ አንዳች መፅሔት የመሰለ የወረቀት ጥራዝ ይዛለች አትኩሬ ተመለከትኩት እውነትም መፅሔት ነበር። አረፍ በይ አልኳት በእጄ ወንበሩን አያመላከትኳት። ፈጥና ተቀመጠች በእጇቿ ይዛው የነበረውን መፅሔት ከፊት ለፊቷ ካለው ጠረፔዛ ላይ አስቀመጠችው። ጥቂት የግል ወሬያችንን ስናወጋ ቆየንና እኔ ምልህ ገዜ አለች የወሬውን አቅጣጫ ለማስቀየር ቀጠለችና ትናንት ትልቅ እንግዳ ነው ያለን አላልኩህም ነበር። ማን እንደ ሆነ ገምት አለች አይን አይኔን እያየች። እኔም ሊሆኑ ይችላሉ ብዬ ያስብኳቸውን ሰዎች ጠቀስኩ። ግን መሳሳቴን ፊቷ ይናገራል። መፅሔቱን ከስቀመጠችበት በማንሳት ተመልከት የዚህ መፅሔት አዘጋጅ የሆነችው ሴት አወካት አለችኝና መፅሔቱን ሰጠችኝ ተቀብያት ማገላበጥ ያዝኩ። እንዴት የምታሳዝን ሴት መሰለችህ በፊት የነበራት የሞራል ልዕልና ከስሞ የአዕምሮ መቃወስ ሁሉ ገጥሟት ሰራም ማቆሟን ባደረኩት ማጣራት ማወቅ ችያለሁ። ብላ ከተቀመጠችበት ተነሳችና ቀሚሷን ወደታች ወደታች እየሳበች ለመንኛውም ይሄንን ልነግርህ ብዬ ነው ብላኝ ወጣች። አፃፃፉም ሆነ የስዕልና የፎቶግራፎቹ አቀማመጥ ልጅ ሳለሁ እቤታች ያሸበርቅበት የነበረውን ጋዜጣ አስታወሰኝ። ትዝ ይለኛል ለሰዓታት የቤታችን ግድግዳ ላይ አፍጥጬ ነበር የምውለው።ፖለቲካ፣እስፖርት፣የሃራጅና የጨረታ እንዲሁም የስራ ቅጥር ማስታወቂያው መዝናኛውም ቢሆን ለንባብ የሚጋብዝ አፃፃፍ ነበራቸው የአዘጋጆቹም ብስለት ይሄ ነው የማይባል ነበር።ከሁሉም ከሁሉም መዝናኛ ላይ ያነበብኩት #ከገፅ 3የዞረ የአንድ ጫማ ሰፊ አሟሟትን የሚያትት ፅሑፍ ጉዳይ መጨረሻውን ፍለጋ ግድግዳው ሳስስ የቆየሁበትን ጊዜ አልረሳውም እስገዛሬ ድረስ በውስጤ መጨረሻው ጥያቄ ሆኖ አለ ለሁሉ ግን ክብር ይገባቸዋል!#
ለሰዓታት ከተጓዝኩቀት የሃሳብ ጎዳና ወደ ዛሬ ተመለስኩ እውነት ነው ክብር ይገባቸዋል። ስንቱን መወደስ የሌለበትን ስናወድስ ክብር ለሚገባቸው ግን ክብርን ነፍገናቸው የት እንደ ወደቁ እንኳን አለማወቃችን ያሳፍራል
ክብር ለሚገባው ክብር እንስጥ!
ለሃሳብ አስተያየት
ጆሲ:@yosikeman
ለመቀላቀል
@gGetem
👍1
የናፈቀኝ ነገር
ያልኖርኩበት ሃገር!
ማንም ሰው ሳያውቀኝ÷ ከዜሮ መጀመር
ጠዋት የምሰማው
የማላውቃትን ወፍ፣ አዲስ አዘማመር።
የፈለግሁት ነገር
መኖሪያ መቀየር
ልብሴንም መቀየር
ለየት ቢልልኝ
የምጠጣው ውሃ÷ የምስበው አየር።
መራመድ የሚያምረኝ
በአዲስ ጎዳና ላይ ÷ በኔ እግር የነቃ
ባገኝ አዲስ ሃሳብ
አዲስ አይነት እውነት ÷ ወይም አዲስ ቋንቋ።
ማየት የምመኘው ÷ያልራቀ ወደላይ
ሰማያዊ ሳይሆን ÷አዲስ አይነት ሰማይ
በማላውቀው ቀለም ÷ አዲስ አይነት ፀሃይ።
.
.
.
የማውቀውን ሁሉ
መተካት በመሻት
ወደማይታወቅ
ህይወቴን ብሸሻት
የማልሰለቸውን ÷ አጣሁት ፈልጌው
(ስገምት ችግሩን)
አዲሱን የሚያስረጅ ÷ እኔ ነኝ አሮጌው።
በርግጥ እንኳን ማርጀት ÷ መኖር ይለመዳል?
መሰልቸትን መቻል÷ ከናፍቆት ይከብዳል?
በማውቀው አኗኗር÷ መኖር ከከበደኝ
ወደማይታወቅ ÷ ልቤ ካሰደደኝ
እኔ የሌለሁበት ÷ ማንስ በወሰደኝ?
ወላጅ ባገኘሁኝ
በሆነ አይነት ታምር÷ ዳግም በወለደኝ??
@gGetem
@gGetem
@gGetem
ያልኖርኩበት ሃገር!
ማንም ሰው ሳያውቀኝ÷ ከዜሮ መጀመር
ጠዋት የምሰማው
የማላውቃትን ወፍ፣ አዲስ አዘማመር።
የፈለግሁት ነገር
መኖሪያ መቀየር
ልብሴንም መቀየር
ለየት ቢልልኝ
የምጠጣው ውሃ÷ የምስበው አየር።
መራመድ የሚያምረኝ
በአዲስ ጎዳና ላይ ÷ በኔ እግር የነቃ
ባገኝ አዲስ ሃሳብ
አዲስ አይነት እውነት ÷ ወይም አዲስ ቋንቋ።
ማየት የምመኘው ÷ያልራቀ ወደላይ
ሰማያዊ ሳይሆን ÷አዲስ አይነት ሰማይ
በማላውቀው ቀለም ÷ አዲስ አይነት ፀሃይ።
.
.
.
የማውቀውን ሁሉ
መተካት በመሻት
ወደማይታወቅ
ህይወቴን ብሸሻት
የማልሰለቸውን ÷ አጣሁት ፈልጌው
(ስገምት ችግሩን)
አዲሱን የሚያስረጅ ÷ እኔ ነኝ አሮጌው።
በርግጥ እንኳን ማርጀት ÷ መኖር ይለመዳል?
መሰልቸትን መቻል÷ ከናፍቆት ይከብዳል?
በማውቀው አኗኗር÷ መኖር ከከበደኝ
ወደማይታወቅ ÷ ልቤ ካሰደደኝ
እኔ የሌለሁበት ÷ ማንስ በወሰደኝ?
ወላጅ ባገኘሁኝ
በሆነ አይነት ታምር÷ ዳግም በወለደኝ??
@gGetem
@gGetem
@gGetem
👍1
Audio
የሌሊት 💀ጋገን
#ደራሲ_እና_ተራኪ_ሊዮ_ማክ
የሆሄያት ህብር
#የጥበብ_ማዕድ
#በቅርብ_ቀን_ይጠብቁን
#አዲስ_ስራ
ለጥያቄና ሒስ @sirak6
ለቤተሰባዊነት www.tgoop.com/gGetem
#ደራሲ_እና_ተራኪ_ሊዮ_ማክ
የሆሄያት ህብር
#የጥበብ_ማዕድ
#በቅርብ_ቀን_ይጠብቁን
#አዲስ_ስራ
ለጥያቄና ሒስ @sirak6
ለቤተሰባዊነት www.tgoop.com/gGetem
ነይ
በሰማያዊ ሰማዩ ላይ አንሳፈፍ
በፍቅራችን ምናብ እንበል እና ከፍ
መኖር ውልክፍክፉ ሳያደናቅፈን
ነይ ሀሴት እናድርግ
በመውደድ ተቃቅፈን
ነይ አብረን እንብረር
ይህ መኖር ሳይጠልፈን
በህይወት ውበቷ የመኖርን ክርታስ
ሰብረን እንጣለው መኖርን አናስታውስ
በአብሮነታችን አለምን እንራሳ
ለኛ አይገባንም ያለም ግሳንግሷ
መኖርን እንካድ
ፍቅርን እናሳድ
እግዜር ይቀዬመን ሀጥያታችን ይብዛ
አብረን እንጥፋ እና አለምን እንግዛ
ነይ
መዓት ይውረድብን ሀጥያታችን በዝቶ
አንድ አንቺ ካለሺኝ ምን ሊጎድለኝ ከቶ
ነይ....................
@gGetem
@gGetem
@gGetem
በሰማያዊ ሰማዩ ላይ አንሳፈፍ
በፍቅራችን ምናብ እንበል እና ከፍ
መኖር ውልክፍክፉ ሳያደናቅፈን
ነይ ሀሴት እናድርግ
በመውደድ ተቃቅፈን
ነይ አብረን እንብረር
ይህ መኖር ሳይጠልፈን
በህይወት ውበቷ የመኖርን ክርታስ
ሰብረን እንጣለው መኖርን አናስታውስ
በአብሮነታችን አለምን እንራሳ
ለኛ አይገባንም ያለም ግሳንግሷ
መኖርን እንካድ
ፍቅርን እናሳድ
እግዜር ይቀዬመን ሀጥያታችን ይብዛ
አብረን እንጥፋ እና አለምን እንግዛ
ነይ
መዓት ይውረድብን ሀጥያታችን በዝቶ
አንድ አንቺ ካለሺኝ ምን ሊጎድለኝ ከቶ
ነይ....................
@gGetem
@gGetem
@gGetem
Audio
ምርጥ ግጥም
🎙🎙🎙ናትናኤል
ለሃሳብ እና አስተያየት @yosikeman
ለቤተሰብ ለመሆንና ለማጋራት @gGetem
Rip የኔ ጀግና ወንድም ስራህ በልቤ ከፍ ብሎ ይደመጣል።
🎙🎙🎙ናትናኤል
ለሃሳብ እና አስተያየት @yosikeman
ለቤተሰብ ለመሆንና ለማጋራት @gGetem
Rip የኔ ጀግና ወንድም ስራህ በልቤ ከፍ ብሎ ይደመጣል።
Audio
ምርጥ ግጥም
🎙🎙🎙ናትናኤል
ለሃሳብ እና አስተያየት @yosikeman
ለቤተሰብ ለመሆንና ለማጋራት @gGetem
Rip የኔ ጀግና ወንድም ስራህ በልቤ ከፍ ብሎ ይደመጣል።
🎙🎙🎙ናትናኤል
ለሃሳብ እና አስተያየት @yosikeman
ለቤተሰብ ለመሆንና ለማጋራት @gGetem
Rip የኔ ጀግና ወንድም ስራህ በልቤ ከፍ ብሎ ይደመጣል።
መሳቀቅ
ካልወሉበት ዉለው ባለቤቱን ማነቅ
መደንገጥ
ያለርባን አሳቦ ልብ ምት ማቋረጥ
መታመም
አሜን ለማይል ልብ ሰርክ ሁሌም መሳለም
ማርገብገብ
ለነደደ እሳት ለዕፍታ መስገብገብ
ለማትረጋ እርግብ ጎጆ እየቀለስን
በበረረች ቁጥር ስንት ጊዜ አለቀስን
እያወቅን ስራችን እንደሌለው ጥቅም
በጨዋታ መሃል ስቀን አናስቅም
ማርገብገብ ለምዶብን ለጊዜ ተቀማጭ
እንራወጣለን እስክንሆን ተለዋጭ
መሆንን ሳናውቀው ኑረን በጉድ ሀገር
ደሃ አድርጎ አስቀረን ልማድ ሚሉት ነገር
ለመሆን ሳንጥር ስንት ጊዜ ፈጀን
በማስሆን አረጀን
ለነዋሪ ጊዜ ሆነን አኗኗሪ
አደረገን ቀሪ።
@gGetem
@gGetem
@gGetem
ካልወሉበት ዉለው ባለቤቱን ማነቅ
መደንገጥ
ያለርባን አሳቦ ልብ ምት ማቋረጥ
መታመም
አሜን ለማይል ልብ ሰርክ ሁሌም መሳለም
ማርገብገብ
ለነደደ እሳት ለዕፍታ መስገብገብ
ለማትረጋ እርግብ ጎጆ እየቀለስን
በበረረች ቁጥር ስንት ጊዜ አለቀስን
እያወቅን ስራችን እንደሌለው ጥቅም
በጨዋታ መሃል ስቀን አናስቅም
ማርገብገብ ለምዶብን ለጊዜ ተቀማጭ
እንራወጣለን እስክንሆን ተለዋጭ
መሆንን ሳናውቀው ኑረን በጉድ ሀገር
ደሃ አድርጎ አስቀረን ልማድ ሚሉት ነገር
ለመሆን ሳንጥር ስንት ጊዜ ፈጀን
በማስሆን አረጀን
ለነዋሪ ጊዜ ሆነን አኗኗሪ
አደረገን ቀሪ።
@gGetem
@gGetem
@gGetem
❤1👏1
ፍቅር በቃኝ
እኔ ልበ ስንኩል ማፍቀር የተሳነኝ
የወደድኩትን ውድ ጨርሼ ማልገኝ
መውደድን ለመውደድ ኃይል ያጠረኝ
ካቅሜ አንጠፍጥፌ ልጠቀለል
ባንድ ሰው ሥር አረፍ ልል
ብጥር ብጥር
ለጨዋታ ሆኗል አሉ የፍቅር ነገር
እውነት ቀርቶ በትብብር
እንደውም
ሰዶ ማሳደዱም ደክሞኛል ሰጥቶ መቀበሉም እንዲሁ
የገባው ሰው እስኪመጣ የራሱ የፍቅር ትርጉሙ
መፅሐፉ ላይ የተፃፈው እንደዚህ ነው የተባልነው
እርሱ ሰው ተገኝቶ እስከሚያሳርፈኝ
ፍቅር በቃኝ
@gGetem
እኔ ልበ ስንኩል ማፍቀር የተሳነኝ
የወደድኩትን ውድ ጨርሼ ማልገኝ
መውደድን ለመውደድ ኃይል ያጠረኝ
ካቅሜ አንጠፍጥፌ ልጠቀለል
ባንድ ሰው ሥር አረፍ ልል
ብጥር ብጥር
ለጨዋታ ሆኗል አሉ የፍቅር ነገር
እውነት ቀርቶ በትብብር
እንደውም
ሰዶ ማሳደዱም ደክሞኛል ሰጥቶ መቀበሉም እንዲሁ
የገባው ሰው እስኪመጣ የራሱ የፍቅር ትርጉሙ
መፅሐፉ ላይ የተፃፈው እንደዚህ ነው የተባልነው
እርሱ ሰው ተገኝቶ እስከሚያሳርፈኝ
ፍቅር በቃኝ
@gGetem