GIBI_GUBAE Telegram 2686
±±±ክብደት ለመቀነስ እንጹም!±±±

የታላቁ እስክንድር ሠራዊት ፋርስን /ፐርሺያን/ በድል እየተቆጣጠረ ነበር፡፡ አንድ ወሳኝ ቦታ ላይ ግን ወታደሮቹ እየተዳከሙ ሊሸነፉ ሆነ፡፡እነዚህ ወታደሮች ከዚህ ውጊያ
በፊት በነበራቸው ጦርነት ላይ የዘረፉትን ተሸክመው ስለነበር እንደልብ እንዳይንቀሳቀሱ ከብዷቸው በደንብ መዋጋት አቃታቸው፡፡

እስክንድር ይኼን ጊዜ የዘረፉትን ሁሉ አንድ ቦታ ላይ እንዲከምሩ አደረገና እሳት ለቀቀበት፡፡ ሁሉም ምርር ብለው ተበሳጩ፡፡ የንጉሡን ብልህነት የተረዱት ግን በኋላ ነው፡፡አንዱ ጸሐፊ ‹በፍጥነት እየሮጡ ሲዋጉ ክንፍ የተሠጣቸው ይመስሉ ነበር ›› ብሎ ጽፎአል፡፡ ድላቸውንም አረጋገጡ፡፡

እንደ አሜሪካ ባሉ ሀብታም ሀገራት ሁልጊዜ ከሚነሡችግሮች አንዱ ከመጠን ያለፈ ውፍረት ነው፡፡ በሚልዮን የሚቆጠሩ ሰዎች በውፍረት ይቸገራሉ፡፡ ክብደታቸውንም ለመቀነስ ብዙ እንቅስቃሴዎችን ያደርጋሉ ፡፡ ለህክምናና ለአማካሪዎች ብዙ ገንዘብ ያወጣሉ፡

፡ አመጋገባቸውን ለመቀነስም ብዙ ትግል ያደርጋሉ፡፡ የስኳር ሕመም ፣ የልብ ሕመም ፣ ከፍተኛ የኮሌስትሮል መጠንና ስትሮክ ያሰጋቸዋል፡፡ የሚሰቃዩትም ሆነ አመጋገባቸውን
መቆጣጠር የሚቸገሩት ከምግብ መከልከልን ስላልለመዱ ነው፡፡

ክርስቲያኖች የክርስቶስ ወታደሮች እንደመሆናችንከመንፈሳዊ ጠላታችን ከዲያቢሎስ ጋር በምናደርገው ውጊያ ላይ እንዳንቸገር የሚከብደንን ማንኛውንም ነገር ማስወገድ አለብን፡፡ ውጊያውን በሚገባ ለመዋጋት የእግዚአብሔርን የጦር ዕቃ እንዴት መታጠቅ እንዳለብን ማወቅ ያስፈልገናል፡፡ (ኤፌ. 6፡11-17) የውጊያችን መሪ ጌታችን ኢየሱስ
ክርስቶስ በጾመና እኛንም እንድንጾም ባስተማረን ጊዜም ይህን ሃሳብ ነግሮናል፡፡ ከመጠን ያለፈ ምግብ ሆዳችንን ከሞላው ፣ ቁሳዊ ነገር ካበዛን ፣ በነፍሳችን ላይ ተጨማሪ ሸክም እንጨምራለን፡፡

በሰይጣን ወጥመድ ላይ የምናገኘውንም ድል ያስቀርብናል፡፡ ‹‹ነገር ግን እንዲህ ዓይነቱ ወገን ከጾምና ከጸሎትበቀር አይወጣም፡፡›› (ማቴ.17፡21)
መጽሐፍ ቅዱስ ክርስቲኖችን ከሯጮችም ጋርያመሳስላቸዋል፡፡ ሩጫን ለማሸነፍ
ደግሞ ወደ ኋላ የሚጎትተንን ‹ሸክምን ሁሉ ማስወገድ አለብን›› (ዕብ. 12፡1)

ይኼ ክብደት ገደብ የለሽ የሀብት ፍቅር ፣ በገንዘብ ፍቅር መማረክ ፣ ማለቂያ የሌለው እርካታን ፍለጋ ፣ ኃጢአት ለሆኑ ፍላጎቶች ባሪያ መሆን ፣ ሥጋዊ ምኞትና ስስት ሊሆንም ይችላል፡፡

አዎ ፤ መልካሙን የእምነት ውጊያ ልንዋጋና መንፈሳዊውን ሩጫ በጽናት ለመሮጥ የምናስብ ከሆነ መሪ ቃላችን መሆን ያለበት ‹ክብደት መቀነስ› ወይም ‹ጾም› የሚለው ነው፡፡‹‹እኛ ደግሞ ሸክምን ሁሉ ቶሎም የሚከበንን ኃጢአት አስወግደን፥ የእምነታችንንም ራስና

ፈጻሚውን ኢየሱስን ተመልክተን፥ በፊታችን ያለውን ሩጫ በትዕግሥት እንሩጥ፤ እርሱ ነውርን ንቆ በፊቱም ስላለው ደስታ በመስቀል ታግሦ በእግዚአብሔር ዙፋን ቀኝ
ተቀምጦአልና።›› ዕብ. 12፡1

‹‹እናንተ ደካሞች ሸክማችሁ የከበደ ሁሉ፥ ወደ እኔ ኑ፥ እኔም አሳርፋችኋለሁ ፤ ቀንበሬን በላያችሁ ተሸከሙ ከእኔም ተማሩ፥ እኔ የዋህ በልቤም ትሑት ነኝና፥ ለነፍሳችሁምዕረፍት
ታገኛላችሁ ፤ ቀንበሬ ልዝብ ሸክሜም ቀሊል ነውና።›› [ማቴ.11፡28]
ዲ\ን ሄኖክ ኃይሌ
@gibi_gubae
@gibi_gubae
@gibi_gubae



tgoop.com/gibi_gubae/2686
Create:
Last Update:

±±±ክብደት ለመቀነስ እንጹም!±±±

የታላቁ እስክንድር ሠራዊት ፋርስን /ፐርሺያን/ በድል እየተቆጣጠረ ነበር፡፡ አንድ ወሳኝ ቦታ ላይ ግን ወታደሮቹ እየተዳከሙ ሊሸነፉ ሆነ፡፡እነዚህ ወታደሮች ከዚህ ውጊያ
በፊት በነበራቸው ጦርነት ላይ የዘረፉትን ተሸክመው ስለነበር እንደልብ እንዳይንቀሳቀሱ ከብዷቸው በደንብ መዋጋት አቃታቸው፡፡

እስክንድር ይኼን ጊዜ የዘረፉትን ሁሉ አንድ ቦታ ላይ እንዲከምሩ አደረገና እሳት ለቀቀበት፡፡ ሁሉም ምርር ብለው ተበሳጩ፡፡ የንጉሡን ብልህነት የተረዱት ግን በኋላ ነው፡፡አንዱ ጸሐፊ ‹በፍጥነት እየሮጡ ሲዋጉ ክንፍ የተሠጣቸው ይመስሉ ነበር ›› ብሎ ጽፎአል፡፡ ድላቸውንም አረጋገጡ፡፡

እንደ አሜሪካ ባሉ ሀብታም ሀገራት ሁልጊዜ ከሚነሡችግሮች አንዱ ከመጠን ያለፈ ውፍረት ነው፡፡ በሚልዮን የሚቆጠሩ ሰዎች በውፍረት ይቸገራሉ፡፡ ክብደታቸውንም ለመቀነስ ብዙ እንቅስቃሴዎችን ያደርጋሉ ፡፡ ለህክምናና ለአማካሪዎች ብዙ ገንዘብ ያወጣሉ፡

፡ አመጋገባቸውን ለመቀነስም ብዙ ትግል ያደርጋሉ፡፡ የስኳር ሕመም ፣ የልብ ሕመም ፣ ከፍተኛ የኮሌስትሮል መጠንና ስትሮክ ያሰጋቸዋል፡፡ የሚሰቃዩትም ሆነ አመጋገባቸውን
መቆጣጠር የሚቸገሩት ከምግብ መከልከልን ስላልለመዱ ነው፡፡

ክርስቲያኖች የክርስቶስ ወታደሮች እንደመሆናችንከመንፈሳዊ ጠላታችን ከዲያቢሎስ ጋር በምናደርገው ውጊያ ላይ እንዳንቸገር የሚከብደንን ማንኛውንም ነገር ማስወገድ አለብን፡፡ ውጊያውን በሚገባ ለመዋጋት የእግዚአብሔርን የጦር ዕቃ እንዴት መታጠቅ እንዳለብን ማወቅ ያስፈልገናል፡፡ (ኤፌ. 6፡11-17) የውጊያችን መሪ ጌታችን ኢየሱስ
ክርስቶስ በጾመና እኛንም እንድንጾም ባስተማረን ጊዜም ይህን ሃሳብ ነግሮናል፡፡ ከመጠን ያለፈ ምግብ ሆዳችንን ከሞላው ፣ ቁሳዊ ነገር ካበዛን ፣ በነፍሳችን ላይ ተጨማሪ ሸክም እንጨምራለን፡፡

በሰይጣን ወጥመድ ላይ የምናገኘውንም ድል ያስቀርብናል፡፡ ‹‹ነገር ግን እንዲህ ዓይነቱ ወገን ከጾምና ከጸሎትበቀር አይወጣም፡፡›› (ማቴ.17፡21)
መጽሐፍ ቅዱስ ክርስቲኖችን ከሯጮችም ጋርያመሳስላቸዋል፡፡ ሩጫን ለማሸነፍ
ደግሞ ወደ ኋላ የሚጎትተንን ‹ሸክምን ሁሉ ማስወገድ አለብን›› (ዕብ. 12፡1)

ይኼ ክብደት ገደብ የለሽ የሀብት ፍቅር ፣ በገንዘብ ፍቅር መማረክ ፣ ማለቂያ የሌለው እርካታን ፍለጋ ፣ ኃጢአት ለሆኑ ፍላጎቶች ባሪያ መሆን ፣ ሥጋዊ ምኞትና ስስት ሊሆንም ይችላል፡፡

አዎ ፤ መልካሙን የእምነት ውጊያ ልንዋጋና መንፈሳዊውን ሩጫ በጽናት ለመሮጥ የምናስብ ከሆነ መሪ ቃላችን መሆን ያለበት ‹ክብደት መቀነስ› ወይም ‹ጾም› የሚለው ነው፡፡‹‹እኛ ደግሞ ሸክምን ሁሉ ቶሎም የሚከበንን ኃጢአት አስወግደን፥ የእምነታችንንም ራስና

ፈጻሚውን ኢየሱስን ተመልክተን፥ በፊታችን ያለውን ሩጫ በትዕግሥት እንሩጥ፤ እርሱ ነውርን ንቆ በፊቱም ስላለው ደስታ በመስቀል ታግሦ በእግዚአብሔር ዙፋን ቀኝ
ተቀምጦአልና።›› ዕብ. 12፡1

‹‹እናንተ ደካሞች ሸክማችሁ የከበደ ሁሉ፥ ወደ እኔ ኑ፥ እኔም አሳርፋችኋለሁ ፤ ቀንበሬን በላያችሁ ተሸከሙ ከእኔም ተማሩ፥ እኔ የዋህ በልቤም ትሑት ነኝና፥ ለነፍሳችሁምዕረፍት
ታገኛላችሁ ፤ ቀንበሬ ልዝብ ሸክሜም ቀሊል ነውና።›› [ማቴ.11፡28]
ዲ\ን ሄኖክ ኃይሌ
@gibi_gubae
@gibi_gubae
@gibi_gubae

BY ✞ግቢ ጉባኤ✟


Share with your friend now:
tgoop.com/gibi_gubae/2686

View MORE
Open in Telegram


Telegram News

Date: |

On Tuesday, some local media outlets included Sing Tao Daily cited sources as saying the Hong Kong government was considering restricting access to Telegram. Privacy Commissioner for Personal Data Ada Chung told to the Legislative Council on Monday that government officials, police and lawmakers remain the targets of “doxxing” despite a privacy law amendment last year that criminalised the malicious disclosure of personal information. Telegram Android app: Open the chats list, click the menu icon and select “New Channel.” Clear When choosing the right name for your Telegram channel, use the language of your target audience. The name must sum up the essence of your channel in 1-3 words. If you’re planning to expand your Telegram audience, it makes sense to incorporate keywords into your name. In the “Bear Market Screaming Therapy Group” on Telegram, members are only allowed to post voice notes of themselves screaming. Anything else will result in an instant ban from the group, which currently has about 75 members.
from us


Telegram ✞ግቢ ጉባኤ✟
FROM American