tgoop.com/gibi_gubae/839
Last Update:
ላክ ያመልኩኛል!
ሞት ፡- ሞታቸውን እንደ መልካም ነገር የሚናፍቁኝና የሚጠሩኝ ብዙዎች ናቸው ፤ አንተን ግን ፈልጎ የጠራህም የሚጠራህም የለም፡፡
ሰይጣን ፡- ብዙ ሰዎች በሥራቸው እንደሚጠሩኝና እጅ መንሻም እንደሚያቀርቡልኝ አላስተዋልክም እንዴ? አይ ሞት!
ሞት ፡- ስምህ እኮ የተጠላ ነው አይ ሰይጣን! ሁሉ ይረግምሃል ፤ ስምህን ልታነጻውና መጠላትህን ልትሸሽገው አትችልም፡፡
ሰይጣን ፡- ጆሮህ ሳይደፈን አይቀርም ፤ ሰዎች በአንተ ላይ ምን ያህል በምሬት እንደሚጮኹ አትሰማም እንዴ? ይልቅ ብትደበቅ ሳይሻልህ አይቀርም…››
የሞትና የሰይጣን ክርክር ረዥም ነው ፤ ክርክሩ ከሲኦልም ጋር ይቀጥላል፡፡ ቅዱስ ኤፍሬም ከሁሉ በመጨረሻ :- ‹‹አንድ ልብ ሆነው የነበሩትን ሞትና ሰይጣንን የከፋፈላቸው እርሱ የተመሰገነ ይሁን ፤ ተከፋፍለን የነበርነውን እኛንም አንድ ልብ ያደረገን እርሱ የተመሰገነ ይሁን›› ብሎ ውብ ድርሰቱን ያጠናቅቃል፡፡
‹አንበሳ ሲያረጅ የዝንብ መጫወቻ ይሆናል› እንደሚባለው ሞት በአሟሟቱና በመዋረዱ የተነሣም እኛ ክርስቲያኖች እጅግ ንቀነው ‹መውጊያህ የታለ?› እያልን መዘበት የጀመርን ሲሆን ሰማዕታቱ ደግሞ እንኳንስ ሊፈሩት የአንገታቸውን ኮሌታ ለመታረድ እየሰበሰቡ በደስታ የሚጠጡት ጽዋ ሆነላቸው፡፡ ስንቱን እንዳላስለቀሰና በጣር እንዳላስጨነቀ ዛሬ ሙቱ ሞት ተንቆ ኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያናችን ለፍትሐት ጸናጽልና ከበሮ ይዛ የምትዘምርበት ፣ በኀዘን ፈንታ ማኅሌት የምትቆምበት ፣ እየተደገሰ ከነዳያን ጋር የሚበላበት ክስተት ሆኖ አረፈው፡፡
ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ
ሚያዝያ 28 2012 ዓ ም
ሕማማት - ገጽ 500
@gibi_gubae
@gibi_gubae
@gibi_gubae
BY ✞ግቢ ጉባኤ✟
Share with your friend now:
tgoop.com/gibi_gubae/839