tgoop.com/halale_merdaja_dilla/1002
Last Update:
"የልጅነት-ውጥን፤ የአፍላነት-ጥረት፤ የወጣትነት-ስኬት"
🌹 ክብር ለሚገባው ክብርን ምስጋና ለሚያሻውም ምስጋናን እንቸራለን። እኛ ከራሳችን አንዳች ነገርን ለማድረግ አቅሙም ብልሀቱም የለንም የአላህ መልካም ፍቃድ ቢታከልበት እንጂ። ይህን ድንቅ ስኬትም ላሳየን አምላክ የሚገባውን ያህል ምስጋና እናደርሳለን፥ አልሀምዱሊላሒ-ረቢል አለሚን።
🌹 በያዝነው ሳምንት በከተማችን ዲላ ብሎም በአካባቢያችን ታይቶም ሆነ ተሰምቶ የማይታወቅ ድንቅ ተግባር በጌታችን ይሁንታ ለመሳካት ችሏል። ለአመታት በሌሎች አካባቢዎች ሲከወን ተመልክተን እንከጅለው የነበረን መልካም ስራ ተራው ደርሶን እኛም የእድሉ ተካፋይ ለመሆን በቅተናል።
🌹 "ሀላል" የተሰኘው የልበ-ቀናዎች ስብስብ ልግስናና ቸርነት ከሞላቸው ግብረ-ሰናይ ድርጅቶች ጋር በፈጠረው ጠንካራ ግንኙነት ከ200 በላይ ወይፈን እና ቁጥራቸው ሰባት የሚደርሱ በጎችን ለተከበረው የአረፋ በዓል መስዋዕት በማድረግ ከሰባት ያላነሱ ከተሞችን፤ 12 ወረዳዎችን እንዲሁም በከተማችን ዲላ የሚገኙ ነዋሪዎችና ተቋማትን (ዩኒቨርሲቲ፣ ማረሚያ እና መሳጂዶችን) ጨምሮ ቁጥራቸው ከ3,000 ለሚልቁ ቤተሰቦች በዓሉን በደስታ ያሳልፉ ዘንድ የስጋ እደላ ፕሮግራም ሲያከናውን ውሎ አምሽቷል።
🌹 "ሀላል መረዳጃ ማህበር" በአስደናቂ የአመራር ብቃት፤ በቀልጣፋ አገልግሎት፤ አክብሮት በተሞላው መስተንግዶ እንዲሁም ጨዋነትን በተላበሰ አፈፃፀም የ1445ኛውን ዓመተ-ሒጅራ የአረፋ በዓል ታሪክ በሚያወሳው መልኩ በሰደቃ አድምቀውት ውለዋል፥ ይህን ሰናይ ተግባር አድንቀናል አመስግነናልም።
🌹 "ሀላል" ዛሬ ላይ ከሚፈፅማቸው ግሩም ተግባራት በተጨማሪ በቀጣይም ለመስራት ያሰባቸው በርካታ ውጥኖች አሉት። እነኚህ ታላላቅ ፕሮጀክቶች ዛሬ ላይ የማይቻሉ መስለው ቢታዩም በአላህ ፍቃድ ሁሉም እውን እንደሚሆን ባለሙሉ ተስፋ ነን፥ ኢንሻአላህ።
👉 በመጨረሻም "ሀላል" የወጣቶች ስብስብ እንደመሆኑ በርካታ እገዛዎችን ከሁሉም ባለድርሻ አካላት ይሻል። ይህን መሰል ባለራዕይ፤ ትጉህ እና ቆራጥ ስብስብ ወደ ተሻለ ደረጃ ማድረስ የሁሉም ሀላፊነት ሊሆን ይገባዋል።
🥀 ስለሆነም ማህበሩን በተለያየ መልኩ ለማገዝና ከወጣቶቹም ጎን በመሆን የቻላችሁትን አስተዋፆ ማበርከት የምትሹ አካላት በሚከተሉት አድራሻዎች ልታገኙዋቸው ትችላላችሁ።
👉 አድራሻ፦ ቢላል_መስጂድ_ህንፃ_አንደኛ_ፎቅ
ስልክ፦ 09-12-33-00-91
09-10-88-30-37
09-30-66-66-13
#ሀላል_በጎ_አድራጎት_ማህበር
#ኑ_በጋራ_ሆነን_የተሻለ_ማህበረሰብ_ለመፍጠር_እንትጋ!
https://www.tgoop.com/halale_merdaja_dilla
By:-Arefate abdulgefar
BY ሀላል በጎ አድራጎት ማህበር(ዲላ)
Share with your friend now:
tgoop.com/halale_merdaja_dilla/1002