MARKONALFIKRU Telegram 10
📜 መንፈሳዊ ግጥም📜


🛑 እውነት አለቀሰች🛑
▱▱▱▱▱▱▱▱


ልብ ያለህ አስተውል፥   ጆሮ ያለህ ስማ
እግርህ እንዳይገባ፥  ከክህደት ከተማ።
የያዝከውን አጽና ፥ ልብህ አይጨነቅ
ለጥያቄህ መልስም ፥  ሊቃውንትን  ጠይቅ።



     ለእውነት የቆመ፥ ሃይማኖቱን የሚያውቅ
    ንባብ ትርጓሜን ፥ ጠንቅቆ የሚዘልቅ
    ተናገር ዩሐንስ ፥ አንተ ልሳነ ወርቅ።
    ቄርሎስን  ጠይቀው ፥ የተዋህዶን ምስጢር
     የክርስቶስ ነገር ፥ እንዴት እንደነበር።
     ከብሉይ ከሐዲስ ፥ በማቀነባበር
     እንዳመሰጠረው ፥ በብዙ ምስክር።



ነቢዩ ኢሳያስ ፥ ብርሃነ ዓለም ጳውሎስ
መዝሙረኛው ዳዊት ፥ ሐዋርያው ሉቃስ
አባ ዝክረ ማርያም ፥ ወአባ ጴጥሮስ
የስነ ዘፍጥረት ሊቅ ፥ ኤጲፋኒዮስ
ዝም አትበል ተናገር ፥ ቅዱስ ሳዊሮስ
በሥጋው ማክበሩን ፥ አምላክ ክርስቶስ።



     ጊዮርጊስ ተናገር ፥ አንተ የጥዋት ጮራ
     ክርስቶስ መሲሕም ፥ ተብሎ እንደሚጠራ።
     ወልድ ቅብዕ በማለት፥ ክህደት አስተማሩ
     የሥግው ቃል ነገር ፥ መች ገባቸው ዳሩ
     የተዋሕዶ ምስጢር ፥ ሳይገባቸው ቅሉ
     ሃይማኖት ከምስጢር ፥ ይደባልቃሉ።



ክርስቶስ በሥጋ ፥ እንደሞተ ሲያውቁ
በሥጋስ መክበሩን፥ እንዴት አላወቁ
ሊቃውንት እያሉ ፥ ለምን አይጠይቁ
በተዋሕዶ ከበረ ፥ ብለው ሲናገሩ
ለዚህ ብሂላቸው ፥ የታል ምስክሩ።



   ግብርን በማፋለስ....
    አንድ ገጽ ካለው ፥ ከሰባልዮስ
    አንድነትን ትቶ ....
    ሁለት አካል ካለው ፥ ከእርጉም ንስጥሮስ
    መንፈስ ቅዱስ፥ ሕጸፅ ካለው ከመቅዶንዮስ
    ወልድ ፍጡር ካለው፥ ከእርጉም ከአርዮስ
    የዚህ ክህደቱ ፥ በምንም አያንስ።



ፈላጊዋ ጠፍቶ፥ እውነት አለቀሰች
ግብራቸው ተቃርኖ፥ ሀሰት ጥላት ሄደች።
ዳሩ ግን ወገኔ ፥ ይህ ክህደት ነውና
ቀኑ ሳይመሽብህ ፥ መንገድህን አቅና
እውነትን ከፈለክ ፥ ታገኛለህና
እረፍት ስላላት ፥ የህይወት ጎዳና
የያዝከውን ይዘህ ፥ በሃይማኖት ጽና።

    🙏ወስብሐት ለእግዚአብሔር🙏
      🙏 ወለወላዲቱ ድንግል 🙏
        🙏ወለመስቀሉ ክቡር🙏

ይቆየን ○○○○○○○○



tgoop.com/markonalfikru/10
Create:
Last Update:

📜 መንፈሳዊ ግጥም📜


🛑 እውነት አለቀሰች🛑
▱▱▱▱▱▱▱▱


ልብ ያለህ አስተውል፥   ጆሮ ያለህ ስማ
እግርህ እንዳይገባ፥  ከክህደት ከተማ።
የያዝከውን አጽና ፥ ልብህ አይጨነቅ
ለጥያቄህ መልስም ፥  ሊቃውንትን  ጠይቅ።



     ለእውነት የቆመ፥ ሃይማኖቱን የሚያውቅ
    ንባብ ትርጓሜን ፥ ጠንቅቆ የሚዘልቅ
    ተናገር ዩሐንስ ፥ አንተ ልሳነ ወርቅ።
    ቄርሎስን  ጠይቀው ፥ የተዋህዶን ምስጢር
     የክርስቶስ ነገር ፥ እንዴት እንደነበር።
     ከብሉይ ከሐዲስ ፥ በማቀነባበር
     እንዳመሰጠረው ፥ በብዙ ምስክር።



ነቢዩ ኢሳያስ ፥ ብርሃነ ዓለም ጳውሎስ
መዝሙረኛው ዳዊት ፥ ሐዋርያው ሉቃስ
አባ ዝክረ ማርያም ፥ ወአባ ጴጥሮስ
የስነ ዘፍጥረት ሊቅ ፥ ኤጲፋኒዮስ
ዝም አትበል ተናገር ፥ ቅዱስ ሳዊሮስ
በሥጋው ማክበሩን ፥ አምላክ ክርስቶስ።



     ጊዮርጊስ ተናገር ፥ አንተ የጥዋት ጮራ
     ክርስቶስ መሲሕም ፥ ተብሎ እንደሚጠራ።
     ወልድ ቅብዕ በማለት፥ ክህደት አስተማሩ
     የሥግው ቃል ነገር ፥ መች ገባቸው ዳሩ
     የተዋሕዶ ምስጢር ፥ ሳይገባቸው ቅሉ
     ሃይማኖት ከምስጢር ፥ ይደባልቃሉ።



ክርስቶስ በሥጋ ፥ እንደሞተ ሲያውቁ
በሥጋስ መክበሩን፥ እንዴት አላወቁ
ሊቃውንት እያሉ ፥ ለምን አይጠይቁ
በተዋሕዶ ከበረ ፥ ብለው ሲናገሩ
ለዚህ ብሂላቸው ፥ የታል ምስክሩ።



   ግብርን በማፋለስ....
    አንድ ገጽ ካለው ፥ ከሰባልዮስ
    አንድነትን ትቶ ....
    ሁለት አካል ካለው ፥ ከእርጉም ንስጥሮስ
    መንፈስ ቅዱስ፥ ሕጸፅ ካለው ከመቅዶንዮስ
    ወልድ ፍጡር ካለው፥ ከእርጉም ከአርዮስ
    የዚህ ክህደቱ ፥ በምንም አያንስ።



ፈላጊዋ ጠፍቶ፥ እውነት አለቀሰች
ግብራቸው ተቃርኖ፥ ሀሰት ጥላት ሄደች።
ዳሩ ግን ወገኔ ፥ ይህ ክህደት ነውና
ቀኑ ሳይመሽብህ ፥ መንገድህን አቅና
እውነትን ከፈለክ ፥ ታገኛለህና
እረፍት ስላላት ፥ የህይወት ጎዳና
የያዝከውን ይዘህ ፥ በሃይማኖት ጽና።

    🙏ወስብሐት ለእግዚአብሔር🙏
      🙏 ወለወላዲቱ ድንግል 🙏
        🙏ወለመስቀሉ ክቡር🙏

ይቆየን ○○○○○○○○

BY 📜መንፈሳዊ ግጥሞች📜MENFESAWI GITMOCH


Share with your friend now:
tgoop.com/markonalfikru/10

View MORE
Open in Telegram


Telegram News

Date: |

5Telegram Channel avatar size/dimensions According to media reports, the privacy watchdog was considering “blacklisting” some online platforms that have repeatedly posted doxxing information, with sources saying most messages were shared on Telegram. In 2018, Telegram’s audience reached 200 million people, with 500,000 new users joining the messenger every day. It was launched for iOS on 14 August 2013 and Android on 20 October 2013. The Standard Channel Choose quality over quantity. Remember that one high-quality post is better than five short publications of questionable value.
from us


Telegram 📜መንፈሳዊ ግጥሞች📜MENFESAWI GITMOCH
FROM American