tgoop.com/memhrochachn/1695
Last Update:
" አጋንትን የሚያስጮኹ ሰዎች🤔"
በዘመናችን አጋንትን እናስወጣለን የሚሉ ስዎች ግን ምን አስበው ነው የሰይጣንን ምስክርነት ከሰይጣን እየጠየቁ የሚነግሩን የሰይጣንን ምስክርነት አመነን እንድንቀበል ነውን ሰይጣንን ዝም ብለው ማስወጣት ሲገባ ሰይጣንን እየጠየቁ ማድጮኽ ምን የሚሉት ነው ለሠይጣንን ሥራውን እያገዙት ይኾን እንዴ😁😁😁
እንዴት ያዝከው የት አገኘኸው እያሉ እየጠይቁ የሰይጣንን ጩኸት እና ከአጋንት ጋር ተባባሪ ሊያደርጉን ፈልገው ነውን 🤔
ሰይጣን ምስክርነቱ ሀሰት እንደው አየታወቀ መጠየቅ ለምን አስፈለገው
ነገሩ አብረው ካልሠሩ ሠይጣኑ ወጣው ብሎ አይጮኽም መሰል በሕብረት እንደሚሠሩ እየነገሩን አይመስላችሁም😁
ለማንኛው አንድ ወንድሜ የጻፋትን ላካፍላችኹ
📖 "ኢየሱስም ዝም በል ከርሱ ውጣ ብሎ ገሰፀው::" ማር 1:25
➡️ ወንጌላዊው እንደገለጠው ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወደ ቅፍር ናሆም (የናሆም መንደር) ወረደ፡፡ በቅፍርናሆምም በክፉ መንፈስ የተያዘ ሰውን አገኘ፡፡ ከርሱም ክፉውን መንፈስ አወጣለት፡፡ "ቅፍርናሆም" የቃሉ ትርጉም "የመጽናናት ቦታ" ማለት ነው፡፡ ጌታም ወደዚያ በገባ ጊዜ ቅፍርናሆም በእውነትም የመጽናናት ቦታ ሆነች በዚያ ከክፉ መንፈስ ሰዎችን አድኖበታልና፡፡ ርኩስ መንፈስ ያለበት ሰው "ልታጠፋን መጣህን? ማን እንደሆንህ አውቄያለሁ የእግዚአብሔር ቅዱሱ ብሎ ጮኸ፡፡" ማር 1:24 በዚህን ጊዜ ክርስቶስ "ዝም ብለህ ከእርሱ ውጣ፡፡" በማለት ገስፆታል፡፡ በዚህም ሐብተ ፈውስ ተሰጥቷቸው አጋንንትን ለሚያወጡ ሰዎች ፍኖቱን ይከተሉ ዘንድ አብነት ሆኗል፡፡ በቤተ ክርስቲያንም አጋንንትን ማስለፍለፍ የሚፈቀድ አይደለም፡፡ የአጋንንትአባት ምስክርነታቸውም ተቀባይነት የለውም፡፡ ዲያብሎስ ተንኮልን የተሞላ ሐሰተኛ የሐሰት ነው፡፡ ዮሐ 8:44
ስለዚህ ጉዳይ የቤተ ክርስቲያን ቅዱሳን አባቶች አስተምረውበታል፡፡ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ እንዲህ ይላል:- "አጋንንት እንኳ የእግዚአብሔርን ስም ይጠራሉ፡፡ ነገር ግን አጋንንት ከመሆን አይለወጡም፡፡ ጌታም እነርሱን ይገስፃቸውና ያስወጣቸው ነበር፡፡ እኔም ይህን ክፉ ነገር ታስወግዱ ዘንድ እለምናችኀለሁ፡፡ ይሀውም የእግዚአብሔርን ስም በከንቱ መጥራት ነው፡፡" በማለት በከንቱ ስሙን መጥራት ከአጋንንት ጋር እንደ መተባበር መሆኑን ይገልፃል፡፡ በሌላም ክፍል ሊቁ እንዲህ ብሏል፦ "እውነት በርኩሳን መናፍስት ምስክርነት አይመካም፡፡ አጋንንትን እውነትን ቢናገሩ እንኳ ማመን አይገባም፡፡" ብሏል፡፡ ምክንያቱም ጨለማ በብርሃን ይገለጣል እንጂ ብርሃን በጨለማ አይገለጥምና፡፡ "ብርሃን ከጨለማ ጋር ምን ኅብረት አለው?" 2ኛ ቆሮ 6:14 እንዳለ ሐዋርያው፡፡ የአጋንንትን ምስክርነት ስንመለከት ተንኮል የተመላበት ሆኖ እናገኘዋለን፡፡ ጌታ በጌርጌሴኖን ተገኝቶ ሌጌዎን አጋንንት ያደረበትን ሰው ከተገናኘው በኋላ አጋንንቱ "ታወጣንስ እንደሆነ ወደ እርያ መንጋ ስደደን ብለው ለመኑት፡፡ ሂዱም አላቸው፡፡" ማቴ 8:31 ወደ እርያዎቹም ሄዱ እርያዎቹም ሞቱ፡፡ በዚህም ጊዜ ሕዝቡ ከከተማው እንዲሄድላቸው ለመኑት፡፡ በእርያዎቹ እንዲህ ካደረገ የኛን ኃጠአታችንንማ ምንኛ ቆጥሮ ይፈርድብን ይሆን ብለው ከከተማው እንዲሄድ ለመኑት፡፡ የአጋንንትን ክፉ ስራ አስተዋላችሁን? ጌታችን የአጋንንትን ተንኮል ሳያውቅ ቀርቶ አይደለም ይልቁኑ ትምህርት ሊሰጠን እንጂ፡፡ ለዚህም ነው ጌታ ከሰዎች ርኩስ መንፈስን ሲያወጣ "ዝም ብለህ ውጣ" ብሎ የተናገረው፡፡ የአጋንንት ምስክርነት ተቀባይነት የለውም፡፡
◾️ሊቁ አውግስጢኖስም እንዲህ ይላል፦ " 'የእግዚአብሔር ልጅ' ተብሎ በቅዱስ ጴጥሮስ የተጠራው (ማቴ 16:16) በአጋንንትም ተጠርቷል፡፡ ( ማቴ 8:29፤ ማር1:24) ቃላቱ ተመሳሳይ ቢሆንም ሃሳባቸው ግን ልዩ ነው፡፡ ...የክርስቲያን እምነት መሠረት ማድረግ ያለበት ፍቅር ላይ ነው፡፡ አጋንንት ግን ከፍቅር የተራቆቱ (የራቁ) ናቸው፡፡ ጴጥሮስ 'የእግዚአብሔር ልጅ' ያለው በፍቅር የሆነ እምነቱን ሲገልጥ ነው አጋንንት ግን ይጠሩት የነበረው ክርስቶስ እንዲተዋቸው ነው፡፡" ሊቁ ይቀጥልና
" 'አጋንንት ያምናሉ ይንቀጠቀጡማል' ያዕ 2:19:: እምነት ኃይል አለው ያለ ፍቅር ግን ትርጉም የለውም፡፡ አጋንንት ስለ ክርስቶስ መስክረዋል ምስክርነታቸው ግን ያለ ፍቅር በእምነት ብቻ ነው፡፡... ስለዚህ ፍቅር የሌለበት እንደ አጋንንት የሆነ እምነት ከያዝን በዚህ ልንኮራ አይገባም፡፡"
@memhrochachn
BY የዕንቁ መምህሮቻችን ትምህርቶች🔥
Share with your friend now:
tgoop.com/memhrochachn/1695