tgoop.com/memhrochachn/1786
Last Update:
"ኦርቶዶክሳዊት ቤተክርስቲያን ልጆቿን ትጣራለች፦ ሁላችሁም ስሟት በሩቁ አትሳለሟት ይልቅስ ቀርባችሁ ተማሯት ከእውቀት የጎደለች የመሰላችሁ በጥበብ ሞልታ ታይዋታላችሁና፤ ከወንጌል የሽሽች የመሰላችሁ ወንጌልን ለብሳ ታዩዋታላችሁና፤ ከክርስቶስ የራቀች የመሰላችሁ ክርስቶስን ስታነግስ ታይዋታላችሁና።
ኑ እናንተ የክርስቶስ ወዳጆች ወደ ክርስቶስ ቅረቡ ኑ ኦርቶዶክሳዊነታችሁን በስም ብቻ አታድርጉት ይልቅስ የህይወት መንገድ እንደሆነች እወቁና በዚህች መንገድ ላይ ተጓዙ፡፡
ኑና ተዋህዶን ግለጧት አንብቧት እዩዋት መርምሯት ፈትሿት፤ የክርስቶስን ምስጢረ ተዋህዶ ታሳያለች፣ የክርስቶስ የአምላክነት ክብር ታስረዳለች፣ የክርስቶስን ሞትና መከራ ታሳስባለች፣ የክርስቶስን ትንሳኤና እርገት ታሳውቃለች፣ የክርስቶስን ዳግም ምፅአት ታመላክታለች።
ተዋህዶን አንብቧት ክርስቶስን ታዩታላችሁ፤ ነገር ግን በትእቢት አይደለም በትህትና ነው እንጂ፤ ራስን ከፍ ከፍ በማድረግ አይደለም በማሳነስ ነው እንጂ፤ በአፍ አይደለም በህይወት በመኖር እንጂ፤ ኦርቶዶክሳዊት ቤተክርስቲያን ልጆቿን አሁንም ኑ ልጆቼ እያለች ትጣራለችና ቀርበን ፍቅሯን እንቅመስ፤ ማንም ይህንን ፍቅር ቀምሶ ያተረፈ እንጂ የከሰረ፣ ቀና ያለ እንጂ አንገቱን የደፋ፣ የተደሰተ እንጂ የተከፋ፣ ዘለዓለማዊ ህይወትን ያገኘ እንጂ የሞት ሞትን የሞተ የለምና፡፡"
@memhrochachn
BY የዕንቁ መምህሮቻችን ትምህርቶች🔥
Share with your friend now:
tgoop.com/memhrochachn/1786