MENEFESAWINET Telegram 9871
+ ለመላእክት ስግደት አይገባም የሚሉን +

ይህችን ይዘው በተረዱበት መንገድ ስላልሆነ መረዳታችን እንዲህ ትብራራለች ።


"ነገር ግን እንዳታደርገው ተጠንቀቅ ከአንተ ጋር የኢየሱስም ምስክር ካላቸው ከወንድሞችህ ጋር አብሬ ባርያ ነኝ ፤ ለእግዚአብሔር ስገድ" (ራእይ19፥10፣ 22፥9)  በማለት መልአኩ የመለሰለትን መልስ በአግባቡ ሳይረዱ ለመላእክት መስግድ አይገባም ለሚለው የተጣመመ ትምህርታቸው ድጋፍ አድርገው የሚያነሡ ወገኖች አልታጡም። ቅዱስ ዮሐንስንም ሁለቴ ለመልአኩ መስገዱ "ካለማወቅ" ብለው በድፍረት ሲናገሩ ይደመጣሉ ። ግን ይህን ተቃውሞ ከመሠረቱ ለማፍረስ እስኪ ጥቂት ለመልአኩ ስለ ሰገደው ዮሐንስ ወንጌላዊ ማንነት ለመረዳት እንሞክር ፦

ቅዱስ ዮሐንስ በብዙ አስደናቂ ጸጋዎች የማናውቀው ታላቅ አባት ነው ። ምንም ከትሕትና የተነሣ በወንጌል የገዛ ስሙን ጠቅሶ ስለ ራሱ በዙ ነገር ባይጽፍልንም እንኳን ጌታ አብልጦ ይወደው የነበረ ሐዋርያ ፤ ከደረቱ የሚጠጋ ባለሟል እንደነበረ ግን ነግሮናል። ይህም ብቻ አይደለም ። ቅዱስ ዮሐንስ ነገረ ሃይማኖትን የመረዳት አቅሙ ጥልቅ እንደነበረ ሦስቱ ወንጌላውያን ባልተነሡበት መንገድ ወንጌሉን በረቀቀ ስብከት በመጀመሩ አውቀናል ። ቅዱስ ዮሐንስ የጻፈውን ወንጌሉን የተረጎመ ስመ ሞክሼው #ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ደግሞ ከመንፈስ ቅዱስ ያገኘውን ስለ ቅዱስ ዮሐንስ ክብር ሲናገር መላእክት የተፈጥሯቸውን ነገር ከእርሱ ሊማሩ ይፈልጉ እንደነበረ ከዚህ ቀደም ባጣቀስነው "በእንተ ኅቡዓት" በተሰኘ ድርሰቱ ላይ አስፍሮታል። ታድያ በመለኮታዊው ምሥጢር ባሕር ሲዋኝ የሚኖር ቅዱስ ዮሐንስ ወንጌላዊ ፣ በመላእክት የሚጠየቅ ታላቅ ጻድቅ "ለመላእክት ስግደት ይገባል ወይስ አይገባም?" የሚለውን ጉዳይ በእርሱ ዘንድ እንዴት አወዛጋቢ ሊሆን ይችላል ? እንኳን መላእክት ለማየት የበቃ ቅዱስ ዮሐንስ አይደለም እኛም ይህን ሳንረዳው ብንቀር ከታላቅ ትዝብት ላይ ይጥለናል!። 

ቅድም በያዝናት ርዕስ ዙርያ (ራእይ19፥10፣ 22፥9) 

ደግሞሰ ያለ እውቀት የፈጸመውና የማይገባ ከሆነ መልአኩ አንድ ጊዜ "አትስገድልኝ" ካለው በኋላ ደግሞ ሊሰግድለት ስለምን አልተቆጣውም ወይም በተግሳጽ ቃል አልተናገረውም ? ለሁለተኛ ጊዜ ደግሞ መበደል የሚብስ ቅጣት ያመጣልና (ዮሐ5፥14) ። ቅዱስ ዮሐንስ ግን የመላእክትን ክብር ስለተረዳ አትስገድልኝ እንኳን እያለው በግንባሩ መሬት ነክቶ ሰግዶለታል ። መልአኩም "አትስግድልኝ"  አለው እንጂ "ስግደት ለመላእክት አይገባም " አላለውም ። መልአኩም ለምን አትስገድልኝ አለው ?

ከቅድስና ልዩ ልዩ መገለጫዎች መካከል አንደኛው "አይገባይኝም" የሚል ልባዊ ትሐትና ነው ። ለዮሐንስ የተገለጠው መልአክ ትሑታን ከሆኑት የቅዱሳን መላእክት ማኅበር የመጣ እንደሆነ ካመንን በዚህ የከበረ የእግዚአብሔር ሰው ስለ ቀረበው ስግደት "አይገባኝም" ብሎ ትሕትና ከመናገር ውጪ ምን እንዲል ይጠበቅበት ይሆን ?


በስተመጨረሻም መልአኩ ቅዱስ ዮሐንስን በንጽሕና ከመዓረገ መላእክት ላይ በመድረሱ እኩያው መሆኑን ስላወቀ ከአንተ ጋር....አብሬ ባሪያ ነኝ" ሲለው ፤ "ዘኢተገብረ ለመላእክት ተገብረ ለካህናት"/"ለመላእክት ያልተደረገ ለካህናት ተደረገ" እንዲል መላእክት ሊነኩ የማይቻላቸውን የአምላክ ሥጋ እና ደም የሚፈትት የሐዲስ ኪዳን ካህን ነውና በዚህስ ደገኛ ሹመት ስለበለጠው ደግሞ "አትስገድልኝ" በማለት አስጠንቅቆታል ። ( "መላእክት" ዲያቆን አቤል ካሳሁን ገጽ 91፥92-93)
@menefesawinet



tgoop.com/menefesawinet/9871
Create:
Last Update:

+ ለመላእክት ስግደት አይገባም የሚሉን +

ይህችን ይዘው በተረዱበት መንገድ ስላልሆነ መረዳታችን እንዲህ ትብራራለች ።


"ነገር ግን እንዳታደርገው ተጠንቀቅ ከአንተ ጋር የኢየሱስም ምስክር ካላቸው ከወንድሞችህ ጋር አብሬ ባርያ ነኝ ፤ ለእግዚአብሔር ስገድ" (ራእይ19፥10፣ 22፥9)  በማለት መልአኩ የመለሰለትን መልስ በአግባቡ ሳይረዱ ለመላእክት መስግድ አይገባም ለሚለው የተጣመመ ትምህርታቸው ድጋፍ አድርገው የሚያነሡ ወገኖች አልታጡም። ቅዱስ ዮሐንስንም ሁለቴ ለመልአኩ መስገዱ "ካለማወቅ" ብለው በድፍረት ሲናገሩ ይደመጣሉ ። ግን ይህን ተቃውሞ ከመሠረቱ ለማፍረስ እስኪ ጥቂት ለመልአኩ ስለ ሰገደው ዮሐንስ ወንጌላዊ ማንነት ለመረዳት እንሞክር ፦

ቅዱስ ዮሐንስ በብዙ አስደናቂ ጸጋዎች የማናውቀው ታላቅ አባት ነው ። ምንም ከትሕትና የተነሣ በወንጌል የገዛ ስሙን ጠቅሶ ስለ ራሱ በዙ ነገር ባይጽፍልንም እንኳን ጌታ አብልጦ ይወደው የነበረ ሐዋርያ ፤ ከደረቱ የሚጠጋ ባለሟል እንደነበረ ግን ነግሮናል። ይህም ብቻ አይደለም ። ቅዱስ ዮሐንስ ነገረ ሃይማኖትን የመረዳት አቅሙ ጥልቅ እንደነበረ ሦስቱ ወንጌላውያን ባልተነሡበት መንገድ ወንጌሉን በረቀቀ ስብከት በመጀመሩ አውቀናል ። ቅዱስ ዮሐንስ የጻፈውን ወንጌሉን የተረጎመ ስመ ሞክሼው #ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ደግሞ ከመንፈስ ቅዱስ ያገኘውን ስለ ቅዱስ ዮሐንስ ክብር ሲናገር መላእክት የተፈጥሯቸውን ነገር ከእርሱ ሊማሩ ይፈልጉ እንደነበረ ከዚህ ቀደም ባጣቀስነው "በእንተ ኅቡዓት" በተሰኘ ድርሰቱ ላይ አስፍሮታል። ታድያ በመለኮታዊው ምሥጢር ባሕር ሲዋኝ የሚኖር ቅዱስ ዮሐንስ ወንጌላዊ ፣ በመላእክት የሚጠየቅ ታላቅ ጻድቅ "ለመላእክት ስግደት ይገባል ወይስ አይገባም?" የሚለውን ጉዳይ በእርሱ ዘንድ እንዴት አወዛጋቢ ሊሆን ይችላል ? እንኳን መላእክት ለማየት የበቃ ቅዱስ ዮሐንስ አይደለም እኛም ይህን ሳንረዳው ብንቀር ከታላቅ ትዝብት ላይ ይጥለናል!። 

ቅድም በያዝናት ርዕስ ዙርያ (ራእይ19፥10፣ 22፥9) 

ደግሞሰ ያለ እውቀት የፈጸመውና የማይገባ ከሆነ መልአኩ አንድ ጊዜ "አትስገድልኝ" ካለው በኋላ ደግሞ ሊሰግድለት ስለምን አልተቆጣውም ወይም በተግሳጽ ቃል አልተናገረውም ? ለሁለተኛ ጊዜ ደግሞ መበደል የሚብስ ቅጣት ያመጣልና (ዮሐ5፥14) ። ቅዱስ ዮሐንስ ግን የመላእክትን ክብር ስለተረዳ አትስገድልኝ እንኳን እያለው በግንባሩ መሬት ነክቶ ሰግዶለታል ። መልአኩም "አትስግድልኝ"  አለው እንጂ "ስግደት ለመላእክት አይገባም " አላለውም ። መልአኩም ለምን አትስገድልኝ አለው ?

ከቅድስና ልዩ ልዩ መገለጫዎች መካከል አንደኛው "አይገባይኝም" የሚል ልባዊ ትሐትና ነው ። ለዮሐንስ የተገለጠው መልአክ ትሑታን ከሆኑት የቅዱሳን መላእክት ማኅበር የመጣ እንደሆነ ካመንን በዚህ የከበረ የእግዚአብሔር ሰው ስለ ቀረበው ስግደት "አይገባኝም" ብሎ ትሕትና ከመናገር ውጪ ምን እንዲል ይጠበቅበት ይሆን ?


በስተመጨረሻም መልአኩ ቅዱስ ዮሐንስን በንጽሕና ከመዓረገ መላእክት ላይ በመድረሱ እኩያው መሆኑን ስላወቀ ከአንተ ጋር....አብሬ ባሪያ ነኝ" ሲለው ፤ "ዘኢተገብረ ለመላእክት ተገብረ ለካህናት"/"ለመላእክት ያልተደረገ ለካህናት ተደረገ" እንዲል መላእክት ሊነኩ የማይቻላቸውን የአምላክ ሥጋ እና ደም የሚፈትት የሐዲስ ኪዳን ካህን ነውና በዚህስ ደገኛ ሹመት ስለበለጠው ደግሞ "አትስገድልኝ" በማለት አስጠንቅቆታል ። ( "መላእክት" ዲያቆን አቤል ካሳሁን ገጽ 91፥92-93)
@menefesawinet

BY መንፈሳዊ ትምህርት ዘኦርቶዶክስ


Share with your friend now:
tgoop.com/menefesawinet/9871

View MORE
Open in Telegram


Telegram News

Date: |

Find your optimal posting schedule and stick to it. The peak posting times include 8 am, 6 pm, and 8 pm on social media. Try to publish serious stuff in the morning and leave less demanding content later in the day. How to create a business channel on Telegram? (Tutorial) fire bomb molotov November 18 Dylan Hollingsworth yau ma tei SUCK Channel Telegram In the next window, choose the type of your channel. If you want your channel to be public, you need to develop a link for it. In the screenshot below, it’s ”/catmarketing.” If your selected link is unavailable, you’ll need to suggest another option.
from us


Telegram መንፈሳዊ ትምህርት ዘኦርቶዶክስ
FROM American