MEZ_TEWAHEDO Telegram 2587
+ + + "እመቤታችን የያዘችው፡ የወደቀውን የአዳም ሥጋ ነው" ስለተባለው ጉዳይ፦


* * *


የቲክ ቶኩ ውዝግብ መነሻ፡ በዋናነት አክሊል የተባለ መምህር መኾኑን ሰሞኑን ተገንዝቤያለሁ። አክሊል ሳያውቅ ሊያጠፋ ይችላል። እንዲያ ከኾነ በሊቃውንት ይታረማል፤ ችግር የለውም። ችግሩ ዐውቆ እያጠፋ ከኾነ ብቻ ነው። ያ ደግሞ፡ በቅድሚያ አደጋነቱ ለራሱ ነው። እኔ ስላልተከታተልኩት ምንም ማለት አልችልም። ሊቃውንት መልስ እየሰጡበት ይመስለኛል። መልካም ውይይት ይኹንላቸው።


* * *
ይልቅ፡ በዚች አጭር ጽሑፍ ላካፍላችሁ የፈለግሁት፡ "ጥንተ አብሶ" እና "የወደቀ ሥጋ" በሚለው ዙርያ፡ በአንድ ወቅት፡ ንቡረ እድ ኤርምያስ ከበደ ወልደ ኢየሱስ፡ በኅዋ ሰሌዳቸው ላይ ለቀረበላቸው ጥያቄ የሰጡትን መልስ ስላስታወስኩ፡ እሱን ላካፍላችሁ ነው። እሳቸው በረዥሙ ነው ያብራሩት። እኔ ግን፡ በማስታውሰው መጠን፡ በአጭሩ፡ በራሴ አገላለጽ ነው መልሳቸውን የምጽፍላችሁ።


* * *
"ቅድስት ድንግል ማርያም፡ የአዳም የውርስ ኃጢአት አለባት"፣ ወይም በሰሞነኛው አገላለጽ "ሞት የተፈረደበትን የወደቀውን የአዳም ሥጋ ይዛለች" የሚለው አባባል "ትክክል ነው ወይ?" ተብለው ተጠይቀው፡ ሲመልሱ፡ እንዲህ አሉ፦


"እመቤታችን፡ እንደሌላው የአዳም ዘር ኹሉ፡ እሷም 'ጥንተ አብሶ፥ ወይም አንዳች ከኃጢአት ጋር የተያያዘ እንከን አለባት' የምንል ከኾነ፥ አልያም 'መጀመሪያ ኖሮባት ከዚያ፡ አምላክ፡ እንዳይኖርባት አድርጎ ቀደሳትና፡ አደረባት' የምንል ከኾነ፡ አንድ ከባድ ጥያቄ መመለስ ይኖርብናል። እሱም፦ 'ከቅድስት ድንግል ማርያም በፊት ብዙ የተባረኩና ምሳሌዋም የኾኑ ቅዱሳን ሴቶች፡ ለምሳሌ፦ ሣራ፣ ርብቃ፣ ልያ፣ ወዘተ እንደነበሩ ይታወቃል። እነርሱም እንዲሁ፡ የአዳምና ሔዋን ሥጋን የያዙና የውርስ ኃጢአት ያለባቸው ባለ እንከኖች ስለኾኑ፡ ከነርሱ መካከል አንዲቱን አንጽቶና በድንግልና አጽንቶ ሊያድርባት እየቻለ፡ ለምን፡ ድንግል ማርያም እስክትወለድ ድረስ፡ አዳምንና ልጆቹን በሲዖል 5,500 ዘመን ሙሉ ማስጠበቅ አስፈለገው?' የሚለው ጥያቄ ነው። ለዚህ መልሱ፡ ቅድስት ድንግል ማርያም፡ በሕይወት ዘመኗ ኹሉ፡ ፍጹም ፈጣሪዋን ብቻ ምርጫዋ አድርጋ በመኖሯ፡ ለአምላክ እናትነት በቅታ የተገኘች፡ ምንም የውርስ ኃጢአት የሌለባት ንጽሕት እሷ ብቻ ስለኾነች፡ እርሷ እስክትወለድ መጠበቅ ስለአስፈለገው ነው" የሚል ሃሳብ ነበረው፡ መልሳቸው።


* * *
ስለዚህ፡ ቅድስት ድንግል ማርያም የያዘችው ሥጋ፡ "ሞት የተፈረደበትን የአዳም ሥጋ" ሳይኾን፡ በአዳም ላይ ሞት ከመፈረዱ በፊት የነበረውን ንጹሕ ሥጋ ነው ማለት ነው። እንዲያ ባይኾን ኖሮ፡ "ቤዛዊተ ዓለም" አትባልም ነበር። አንድ ሰው፡ "ቤዛ" ለመባል፡ ቤዛ ከሚኾንላቸው ኹሉ የበለጠ ንጹሕ መኾን አለበት። አለዚያማ፡ "እሱም የሌላው ዕጣ ፈንታ ደረሰበት" ይባላል እንጂ፡ "ቤዛ ኾነ" አይባልም። ቅድስት ድንግል ማርያምም፡ በስደቷም፣ በኀዘኗም፣ በሞቷም፡ እንደልጇ፡ ለዓለም ሕዝብ "ቤዛ" ልትባል የቻለችው፡ የዓለም ሕዝብ የተካፈለው የውርስ ኃጢአት ተካፋይ ስላልኾነችና ከደረሰባት ነገር ኹሉ፡ አንዱም እንኳ ሊደርስባት የሚገባት ስላልኾነች ነው። ልክ እንደልጇ፡ ኢየሱስ ክርስቶስ።


"ፀጋን የመላብሽ ሆይ፥ ደስ ይበልሽ! ከሴቶች ኹሉ ተለይተሽ፡ አንቺ የተባረክሽ ነሽ" እንዳለው ቅዱስ ገብርኤል።

ምንጭ፡ ዶክተር መስከረም ለቺሳ በራሷ ዩቲዩብ ገጽ ላይ ካሰፈረች ጽሁፍ ሙሉ ለሙሉ የተወሰደ

https://www.tgoop.com/mez_tewahedo



tgoop.com/mez_tewahedo/2587
Create:
Last Update:

+ + + "እመቤታችን የያዘችው፡ የወደቀውን የአዳም ሥጋ ነው" ስለተባለው ጉዳይ፦


* * *


የቲክ ቶኩ ውዝግብ መነሻ፡ በዋናነት አክሊል የተባለ መምህር መኾኑን ሰሞኑን ተገንዝቤያለሁ። አክሊል ሳያውቅ ሊያጠፋ ይችላል። እንዲያ ከኾነ በሊቃውንት ይታረማል፤ ችግር የለውም። ችግሩ ዐውቆ እያጠፋ ከኾነ ብቻ ነው። ያ ደግሞ፡ በቅድሚያ አደጋነቱ ለራሱ ነው። እኔ ስላልተከታተልኩት ምንም ማለት አልችልም። ሊቃውንት መልስ እየሰጡበት ይመስለኛል። መልካም ውይይት ይኹንላቸው።


* * *
ይልቅ፡ በዚች አጭር ጽሑፍ ላካፍላችሁ የፈለግሁት፡ "ጥንተ አብሶ" እና "የወደቀ ሥጋ" በሚለው ዙርያ፡ በአንድ ወቅት፡ ንቡረ እድ ኤርምያስ ከበደ ወልደ ኢየሱስ፡ በኅዋ ሰሌዳቸው ላይ ለቀረበላቸው ጥያቄ የሰጡትን መልስ ስላስታወስኩ፡ እሱን ላካፍላችሁ ነው። እሳቸው በረዥሙ ነው ያብራሩት። እኔ ግን፡ በማስታውሰው መጠን፡ በአጭሩ፡ በራሴ አገላለጽ ነው መልሳቸውን የምጽፍላችሁ።


* * *
"ቅድስት ድንግል ማርያም፡ የአዳም የውርስ ኃጢአት አለባት"፣ ወይም በሰሞነኛው አገላለጽ "ሞት የተፈረደበትን የወደቀውን የአዳም ሥጋ ይዛለች" የሚለው አባባል "ትክክል ነው ወይ?" ተብለው ተጠይቀው፡ ሲመልሱ፡ እንዲህ አሉ፦


"እመቤታችን፡ እንደሌላው የአዳም ዘር ኹሉ፡ እሷም 'ጥንተ አብሶ፥ ወይም አንዳች ከኃጢአት ጋር የተያያዘ እንከን አለባት' የምንል ከኾነ፥ አልያም 'መጀመሪያ ኖሮባት ከዚያ፡ አምላክ፡ እንዳይኖርባት አድርጎ ቀደሳትና፡ አደረባት' የምንል ከኾነ፡ አንድ ከባድ ጥያቄ መመለስ ይኖርብናል። እሱም፦ 'ከቅድስት ድንግል ማርያም በፊት ብዙ የተባረኩና ምሳሌዋም የኾኑ ቅዱሳን ሴቶች፡ ለምሳሌ፦ ሣራ፣ ርብቃ፣ ልያ፣ ወዘተ እንደነበሩ ይታወቃል። እነርሱም እንዲሁ፡ የአዳምና ሔዋን ሥጋን የያዙና የውርስ ኃጢአት ያለባቸው ባለ እንከኖች ስለኾኑ፡ ከነርሱ መካከል አንዲቱን አንጽቶና በድንግልና አጽንቶ ሊያድርባት እየቻለ፡ ለምን፡ ድንግል ማርያም እስክትወለድ ድረስ፡ አዳምንና ልጆቹን በሲዖል 5,500 ዘመን ሙሉ ማስጠበቅ አስፈለገው?' የሚለው ጥያቄ ነው። ለዚህ መልሱ፡ ቅድስት ድንግል ማርያም፡ በሕይወት ዘመኗ ኹሉ፡ ፍጹም ፈጣሪዋን ብቻ ምርጫዋ አድርጋ በመኖሯ፡ ለአምላክ እናትነት በቅታ የተገኘች፡ ምንም የውርስ ኃጢአት የሌለባት ንጽሕት እሷ ብቻ ስለኾነች፡ እርሷ እስክትወለድ መጠበቅ ስለአስፈለገው ነው" የሚል ሃሳብ ነበረው፡ መልሳቸው።


* * *
ስለዚህ፡ ቅድስት ድንግል ማርያም የያዘችው ሥጋ፡ "ሞት የተፈረደበትን የአዳም ሥጋ" ሳይኾን፡ በአዳም ላይ ሞት ከመፈረዱ በፊት የነበረውን ንጹሕ ሥጋ ነው ማለት ነው። እንዲያ ባይኾን ኖሮ፡ "ቤዛዊተ ዓለም" አትባልም ነበር። አንድ ሰው፡ "ቤዛ" ለመባል፡ ቤዛ ከሚኾንላቸው ኹሉ የበለጠ ንጹሕ መኾን አለበት። አለዚያማ፡ "እሱም የሌላው ዕጣ ፈንታ ደረሰበት" ይባላል እንጂ፡ "ቤዛ ኾነ" አይባልም። ቅድስት ድንግል ማርያምም፡ በስደቷም፣ በኀዘኗም፣ በሞቷም፡ እንደልጇ፡ ለዓለም ሕዝብ "ቤዛ" ልትባል የቻለችው፡ የዓለም ሕዝብ የተካፈለው የውርስ ኃጢአት ተካፋይ ስላልኾነችና ከደረሰባት ነገር ኹሉ፡ አንዱም እንኳ ሊደርስባት የሚገባት ስላልኾነች ነው። ልክ እንደልጇ፡ ኢየሱስ ክርስቶስ።


"ፀጋን የመላብሽ ሆይ፥ ደስ ይበልሽ! ከሴቶች ኹሉ ተለይተሽ፡ አንቺ የተባረክሽ ነሽ" እንዳለው ቅዱስ ገብርኤል።

ምንጭ፡ ዶክተር መስከረም ለቺሳ በራሷ ዩቲዩብ ገጽ ላይ ካሰፈረች ጽሁፍ ሙሉ ለሙሉ የተወሰደ

https://www.tgoop.com/mez_tewahedo

BY የሊቀ መዘምራን ይልማ ኃይሉ መዝሙሮች




Share with your friend now:
tgoop.com/mez_tewahedo/2587

View MORE
Open in Telegram


Telegram News

Date: |

Among the requests, the Brazilian electoral Court wanted to know if they could obtain data on the origins of malicious content posted on the platform. According to the TSE, this would enable the authorities to track false content and identify the user responsible for publishing it in the first place. Telegram Channels requirements & features Private channels are only accessible to subscribers and don’t appear in public searches. To join a private channel, you need to receive a link from the owner (administrator). A private channel is an excellent solution for companies and teams. You can also use this type of channel to write down personal notes, reflections, etc. By the way, you can make your private channel public at any moment. Telegram desktop app: In the upper left corner, click the Menu icon (the one with three lines). Select “New Channel” from the drop-down menu. fire bomb molotov November 18 Dylan Hollingsworth yau ma tei
from us


Telegram የሊቀ መዘምራን ይልማ ኃይሉ መዝሙሮች
FROM American