Warning: Undefined array key 0 in /var/www/tgoop/function.php on line 65

Warning: Trying to access array offset on value of type null in /var/www/tgoop/function.php on line 65
- Telegram Web
Telegram Web
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
🇮🇱 የእስራኤላውያን ቋንቋ ( ዕብራይስጥ ) መማር የምትፈልጉ ብቻ

@Hebrewethio
@Hebrewethio
+ + + "እመቤታችን የያዘችው፡ የወደቀውን የአዳም ሥጋ ነው" ስለተባለው ጉዳይ፦


* * *


የቲክ ቶኩ ውዝግብ መነሻ፡ በዋናነት አክሊል የተባለ መምህር መኾኑን ሰሞኑን ተገንዝቤያለሁ። አክሊል ሳያውቅ ሊያጠፋ ይችላል። እንዲያ ከኾነ በሊቃውንት ይታረማል፤ ችግር የለውም። ችግሩ ዐውቆ እያጠፋ ከኾነ ብቻ ነው። ያ ደግሞ፡ በቅድሚያ አደጋነቱ ለራሱ ነው። እኔ ስላልተከታተልኩት ምንም ማለት አልችልም። ሊቃውንት መልስ እየሰጡበት ይመስለኛል። መልካም ውይይት ይኹንላቸው።


* * *
ይልቅ፡ በዚች አጭር ጽሑፍ ላካፍላችሁ የፈለግሁት፡ "ጥንተ አብሶ" እና "የወደቀ ሥጋ" በሚለው ዙርያ፡ በአንድ ወቅት፡ ንቡረ እድ ኤርምያስ ከበደ ወልደ ኢየሱስ፡ በኅዋ ሰሌዳቸው ላይ ለቀረበላቸው ጥያቄ የሰጡትን መልስ ስላስታወስኩ፡ እሱን ላካፍላችሁ ነው። እሳቸው በረዥሙ ነው ያብራሩት። እኔ ግን፡ በማስታውሰው መጠን፡ በአጭሩ፡ በራሴ አገላለጽ ነው መልሳቸውን የምጽፍላችሁ።


* * *
"ቅድስት ድንግል ማርያም፡ የአዳም የውርስ ኃጢአት አለባት"፣ ወይም በሰሞነኛው አገላለጽ "ሞት የተፈረደበትን የወደቀውን የአዳም ሥጋ ይዛለች" የሚለው አባባል "ትክክል ነው ወይ?" ተብለው ተጠይቀው፡ ሲመልሱ፡ እንዲህ አሉ፦


"እመቤታችን፡ እንደሌላው የአዳም ዘር ኹሉ፡ እሷም 'ጥንተ አብሶ፥ ወይም አንዳች ከኃጢአት ጋር የተያያዘ እንከን አለባት' የምንል ከኾነ፥ አልያም 'መጀመሪያ ኖሮባት ከዚያ፡ አምላክ፡ እንዳይኖርባት አድርጎ ቀደሳትና፡ አደረባት' የምንል ከኾነ፡ አንድ ከባድ ጥያቄ መመለስ ይኖርብናል። እሱም፦ 'ከቅድስት ድንግል ማርያም በፊት ብዙ የተባረኩና ምሳሌዋም የኾኑ ቅዱሳን ሴቶች፡ ለምሳሌ፦ ሣራ፣ ርብቃ፣ ልያ፣ ወዘተ እንደነበሩ ይታወቃል። እነርሱም እንዲሁ፡ የአዳምና ሔዋን ሥጋን የያዙና የውርስ ኃጢአት ያለባቸው ባለ እንከኖች ስለኾኑ፡ ከነርሱ መካከል አንዲቱን አንጽቶና በድንግልና አጽንቶ ሊያድርባት እየቻለ፡ ለምን፡ ድንግል ማርያም እስክትወለድ ድረስ፡ አዳምንና ልጆቹን በሲዖል 5,500 ዘመን ሙሉ ማስጠበቅ አስፈለገው?' የሚለው ጥያቄ ነው። ለዚህ መልሱ፡ ቅድስት ድንግል ማርያም፡ በሕይወት ዘመኗ ኹሉ፡ ፍጹም ፈጣሪዋን ብቻ ምርጫዋ አድርጋ በመኖሯ፡ ለአምላክ እናትነት በቅታ የተገኘች፡ ምንም የውርስ ኃጢአት የሌለባት ንጽሕት እሷ ብቻ ስለኾነች፡ እርሷ እስክትወለድ መጠበቅ ስለአስፈለገው ነው" የሚል ሃሳብ ነበረው፡ መልሳቸው።


* * *
ስለዚህ፡ ቅድስት ድንግል ማርያም የያዘችው ሥጋ፡ "ሞት የተፈረደበትን የአዳም ሥጋ" ሳይኾን፡ በአዳም ላይ ሞት ከመፈረዱ በፊት የነበረውን ንጹሕ ሥጋ ነው ማለት ነው። እንዲያ ባይኾን ኖሮ፡ "ቤዛዊተ ዓለም" አትባልም ነበር። አንድ ሰው፡ "ቤዛ" ለመባል፡ ቤዛ ከሚኾንላቸው ኹሉ የበለጠ ንጹሕ መኾን አለበት። አለዚያማ፡ "እሱም የሌላው ዕጣ ፈንታ ደረሰበት" ይባላል እንጂ፡ "ቤዛ ኾነ" አይባልም። ቅድስት ድንግል ማርያምም፡ በስደቷም፣ በኀዘኗም፣ በሞቷም፡ እንደልጇ፡ ለዓለም ሕዝብ "ቤዛ" ልትባል የቻለችው፡ የዓለም ሕዝብ የተካፈለው የውርስ ኃጢአት ተካፋይ ስላልኾነችና ከደረሰባት ነገር ኹሉ፡ አንዱም እንኳ ሊደርስባት የሚገባት ስላልኾነች ነው። ልክ እንደልጇ፡ ኢየሱስ ክርስቶስ።


"ፀጋን የመላብሽ ሆይ፥ ደስ ይበልሽ! ከሴቶች ኹሉ ተለይተሽ፡ አንቺ የተባረክሽ ነሽ" እንዳለው ቅዱስ ገብርኤል።

ምንጭ፡ ዶክተር መስከረም ለቺሳ በራሷ ዩቲዩብ ገጽ ላይ ካሰፈረች ጽሁፍ ሙሉ ለሙሉ የተወሰደ

https://www.tgoop.com/mez_tewahedo
የሊቀ መዘምራን ይልማ ኃይሉ መዝሙሮች pinned «+ + + "እመቤታችን የያዘችው፡ የወደቀውን የአዳም ሥጋ ነው" ስለተባለው ጉዳይ፦ * * * የቲክ ቶኩ ውዝግብ መነሻ፡ በዋናነት አክሊል የተባለ መምህር መኾኑን ሰሞኑን ተገንዝቤያለሁ። አክሊል ሳያውቅ ሊያጠፋ ይችላል። እንዲያ ከኾነ በሊቃውንት ይታረማል፤ ችግር የለውም። ችግሩ ዐውቆ እያጠፋ ከኾነ ብቻ ነው። ያ ደግሞ፡ በቅድሚያ አደጋነቱ ለራሱ ነው። እኔ ስላልተከታተልኩት ምንም ማለት አልችልም። ሊቃውንት…»
እንደ ግል መረዳት አቅሜ አኬ ያለውንም ይሄንንም ፅሁፍ እቀበላለሁ። እንዴት ብትለኝ አኬ እመቤታችን የወደቀውን የአዳምን ስጋ ስለያዘች ሞተች ማለቱ ኃጢአት አለባት ኃጢአት ስላደረገች ነው ማለቱ አይደለም ወይም የውርስ ኃጢአት ኖሮባት ነው እያለ አይደለም። የያዘችው ስጋ ግን የአዳም ስጋ ስለሆነ ክርስቶሳዊ ለመሆን በሞት መታደስ አለበት ነው ሞቷ ግን ቅጣት/punishment/ አይደለም ወይም ኃጢአት አይደለም ወይም ኃጢአት አለባትም አያስብልም። ስለዚህ የአኬን ሀሳብ አብዛኞቹ አላገኙትም።

በአንፃሩ ከላይ በፅሁፉ ላይ እንዳለው እመቤታችን የያዘችው ስጋ ሞት የተፈረደበትን ስጋ ሳይሆን አዳም ከመውደቁ በፊት የነበረውን ንጹህ ስጋ ነው የሚለው አገላለፅ በተመሳሳይ እመቤታችን ኃጢአትን አልሰራችም ለማለት የተጠቀሙት አገላለፅ ነው ብዬ አምናለሁ። ምክንያቱም አዳም ከመውደቁ በፊት ከኃጢአት ንጹህ ስለነበር ልክ እንዲሁ እመቤታችንም ንፁህ ናት ለማለት ብቻ የተጠቀሙት አድርጌ እተረጉመዋለው።

ሁለተኛውን ሀሳብ ሙሉ ለሙሉ እንደወረደ የምንቀበለው ከሆነ ግን እመቤታችን መሞት አልነበረባትም ወደ ሚል መደምደሚያ ይወስደናል ምክንያቱም አዳም ከመውደቁ በፊት ሞት ስለማያውቀው ማለት ነው ።

ስለዚህ እንደ እኔ አኬ አልተሳሳተም። ሁለተኛው ሀሳብ ደግሞ ንጽህናዋን ለመግለፅ የገባ አገላለፅ አድርጌ እወስደዋለው።
ምክንያቱም ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለእርሷም መድኃኒቷ ስለሆነ።በደረቁ ግን እሷ የያዘችው ስጋ አዳም ከመውደቁ በፊት የነበረውን ንጹህ ስጋ ነው ካልን ያ ስጋ መድሃኒት የሚፈልግ ስጋ አልነበረም። የሚሞትም አልነበረም። ስለዚህ መድሃኒት አያስፈልጋትም ኃይለ አርያማዊት ናት ልንል ነው ። ይህ ደግሞ ስህተት ነው ።
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
ሩካቤ የሚከለከልባቸው ቀናት ቤተክርስቲያን
🇮🇱 የእስራኤላውያን ቋንቋ ( ዕብራይስጥ ) መማር የምትፈልጉ ብቻ

@Hebrewethio
@Hebrewethio
አክሊልን እንደ አጵሎስ

ወንድማችን አክሊል የአበውን መጻሕፍት በትጋት በማንበብ ራሱን አስተምሮ አስደናቂ የዕቅብተ እምነት ሥራ እንደሠራና በዚህም ለብዙዎች ወደ ኦርቶዶክሳዊት (ርትዕት/ የቀናች) እምነት መመለስ ምክንያት እንደሆነ ይታወቃል፡፡

በቅርቡ ግን ወጣቱ Apologist አክሊል በሚያነሣቸው የነገረ መለኮት እሳቤዎች (theologoumena = ዶግማዊ ውሳኔ ያለተሰጠባቸው አመለካከቶች) ላይ ብዙዎች ጥያቄ ሲያቀርቡና አንዳንዶችም አክሊልን ሲከስሱ ታዝቤአለሁ፡፡ የዚህ ታዳጊ ወጣት አገልግሎት ያስታወሰኝ የሐዋርያት ሥራ ምዕራፍ 18 ውስጥ የምናገኘውን የእስክንድርያ ተወላጁን አጵሎስን ነው፡፡ ጸሐፊው ሉቃስ እንዲህ ከትቦታል፦

የሐዋ ሥራ 18፡ 24 “በወገኑም የእስክንድርያ ሰው የሆነ፣ ነገር አዋቂ የነበረ አጵሎስ የሚሉት አንድ አይሁዳዊ ሰው ወደ ኤፌሶን ወረደ፤ እርሱም በመጻሕፍት እውቀት የበረታ ነበር።
25 እርሱ የጌታን መንገድ የተማረ ነበር፥ የዮሐንስንም ጥምቀት ብቻ አውቆ በመንፈስ ሲቃጠል ስለ ኢየሱስ ይናገርና በትክክል ያስተምር ነበር።
26 እርሱም በምኵራብ ገልጦ ይናገር ጀመር። ጵርስቅላና አቂላም በሰሙት ጊዜ፥ ወስደው የእግዚአብሔርን መንገድ ከፊት ይልቅ በትክክል ገለጡለት።"

አጵሎስ በመጻሕፍት እውቀት የበረታ እንደነበር፣ ወንድማችን አክሊልም የአበውን መጻሕፍት በትጋት በማንበብና የሚያውቀውን በማካፈል ብርቱ ነው፡፡ አጵሎስ በመንፈስ እየተቃጠለ (እንግሊዝኛው "with burning enthusiasm" ይላል) ስለ ኢየሱስ ይናገርና በትክክል ያስተምር እንደነበር፣ አክሊልም ከኦርቶዶክሳውያን አባቶች የተማረውን በትክክል ያስተምር ነበር፡፡

ልዩነቱ ያለው አጵሎስንና አክሊልን ባረሙ (ባቀኑ) ሰዎቸ ላይ ነው፡፡ ባልና ሚስቱ ጵርስቅላና አቂላ የአጵሎስን ቅንዐት (zeal) ተመልክተው፣ አንዳንድ እርማት የሚያስፈልጋቸው ነገሮች እንዳሉ ባስተዋሉ ጊዜ ወደ ቤታቸው ወስደው "የእግዚአብሔርን መንገድ ከፊት ይልቅ በትክክል ገለጡለት" እንጂ አልከሰሱትም፤ አላወገዙትም፡፡

እኛም ለወንድማችን አክሊል ልናደርግ የሚገባው ይህንኑ ነው፡፡ በተሻለ መልኩ በጥበብ ሊቀርቡ የሚገባቸው አስተምህሮዎች ካሉ አክሊልን በፍቅር እናቅናው እንጂ፣ አናውግዘው፡፡ አንዳንድ ጽንፈኞች ስም እያጠፉ በማስደንበር ከኦርቶዶክሳዊት በረት ያስኮበለሏቸው በጎች ብዙዎች ናቸውና ያለፈው ጥፋት ይበቃል!
Forwarded from ELOHE PICTURES ♱
🌟 ELOHE PICTURE

መልአከ ሞት መጥቶ አጠገብህ ሲደርስ ያኔ ትዝ ይልሃ ያቃለልከው ያ ቄስ

👍ㅤ  ➡️ㅤ          💬 Lᶦᵏᵉ   ˢᵃᵛᵉ      ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ
ቶሎ ቶሎ እንድንለቅ ሪያክሽን እንዳይረሳ
   😍 ➪ ꌗꃅꍏꋪꍟ ꌩꂦꀎꋪ ꎇꋪꀤꍟꈤꀸ

🔻🔻ይቀላቀሉን 🔗🔗
https://www.tgoop.com/+Ci5F1FcleWtlZThk
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
Forwarded from BUTTON MAKER
🇮🇱 የእስራኤላውያን ቋንቋ የሆነውን ዕብራይስጥ ቋንቋ መማር ትፈልጋላችሁ ?

👇
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
Forwarded from BUTTON MAKER
🇮🇱 የእስራኤላውያን ቋንቋ የሆነውን ዕብራይስጥ ቋንቋ መማር ትፈልጋላችሁ ?

👇
Forwarded from ELOHE PICTURES ♱ (አይመረ)
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
Forwarded from ELOHE PICTURES ♱ (Elohe pictures) via @dooxbot
ELOHE PICTURE

እምኵሉ ዕለት ሰንበት አክበረ
ወእምኵሉን አንስት ማርያምሃ አፍቀረ


♡ ㅤ  ⎙ㅤ    ⌲        ✉️    Lᶦᵏᵉ   ˢᵃᵛᵉ    ˢʰᵃʳᵉ    ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ
ቶሎ ቶሎ እንድንለቅ ሪያክሽን እንዳይረሳ ❤️
     ➪ ꌗꃅꍏꋪꍟ ꌩꂦꀎꋪ ꎇꋪꀤꍟꈤꀸ

🔻🔻ይቀላቀሉን 🔗🔗
https://www.tgoop.com/+Ci5F1FcleWtlZThk
2025/03/04 08:42:32
Back to Top
HTML Embed Code: