Warning: Undefined array key 0 in /var/www/tgoop/function.php on line 65

Warning: Trying to access array offset on value of type null in /var/www/tgoop/function.php on line 65
158 - Telegram Web
Telegram Web
ወደ አላህ ስትጠጊ ዉብ የሆኑ ነገሮች ሁሉ ወዳንቺ ይጠጋሉ!!!!!
10 ምክር ለእንስቶች .
እህቴ ጀግና ሴት ነኝ ካልሽ

1ኛ: ከሚያናግርሽ ወንድ ሁሉ ጋር አትሳቂ። አንዳንዴ መኮሳተር ጥሩ ነው። ድንበር የሌለው ፈገግታና ሳቅ ከመንገድሽ ያዘገይሻል።

2ኛ: በኢስላምሽ ጉዳይ አትደራደሪ፣ ምክንያቱም ኢስላምሽ ከህይወትሽ በላይ ውድ ነው። አንችን ከመከራ፣ ከስቃይ አውጥቶሻል። ከነ ህይወትሽ በሚቀብሩሽ ሰኣት ‘ለምን!?’ ብሎ ጠበቃ ሆኖ ለነፃነት አብቅቶሻል።

3ኛ: በእምነትሽ አትፍሪ፣ ረጋ ብለሽ ተጓዥ። ባለሽ ነገር ተብቃቂ። ኩርምት አትበይ። ከእምነትሽ ያፈነገጠ አለባበስና ፋሽን ተከታይ አትሁኚ አደራ። ኢስላምሽ ሰማያዊ እንጂ ዘመናዊ አይደለም።

4ኛ: ወደ ዝሙትና ወደ ወንጀል ከሚጋብዙ ነገሮች ሁሉ ራቂ። ‘ኢስላማዊ’ የሚለው ስም እንዳይሸውድሽ አደራ። ኢስላማዊ ፊልም፣ ኢስላማዊ ነሺዳ።

5ኛ: በቦርሳሽ ውስጥ የኮስሞቲክስ ነጋዴ ይመስል የቻይና እቃ ይዘሽ አትዙሪ። ይልቁንስ የእምነትሽን መመሪያ ቁርኣን መያዝን አትርሺ። ቦርሳሽ ውበት የሚኖራት ያኔ ነው።

6ኛ: ድንግልናሽን ጠብቂው። ለምታገቢው ብቻ አስቀምጪ። አላህ ካልፈቀደው ነገር ሁሉ ራቂ። ያኔ ደስተኛ ህይወትን ትኖሪያለሽ።

7ኛ: ሁሌም የምትሰሪውን ስራ አስተውይው። ሙስሊም እንስት የምትፈፅመውን እንጂ አትስሪ።

8ኛ: ሙስሊሟ እህቴ ሆይ! አንቺኮ ምርጥ ነሽ። ወንድ ሁሉ ይፈልግሻል። የሚያገባሽ እንዴት ታድሏል። ተፈላጊ መሆንሽን አትርሺ። ግን ለሚያገባሽ እንጂ ለሚፈልግሽ ሁሉ አትገኚ።

9ኛ: ሁሌም እምነቴ ኢስላም ነው ብለሽ ስታስቢ በሀሴት ልትረኪ ይገባል። ምክንያቱም የጀነት እጩ ተወዳዳሪ ነሽ። ውድድሩን ለማሸነፍ መዝሀበ ሰለፍን ተከተይ አደራሽን።

10ኛ: የመጨረሻው መልእክቴ - ተውሒድና ሱናን ባገኘሽው አጋጣሚ ሁሉ ለእህቶችሽ ስበኪ። ያኔ ውበትሽ ይደምቃል።

Copy

ምክሩ ለኔም ለናንተም ነዉ::አላህ ባወቅነዉ ተጠቃሚዎች ያድርገን!!አሚን!!
🌹እህቴ ሆይ የምትመኝውና የምትፈልጊው
ነገር ሁሉ አሏህ ዘንድ ናቸው🦋
ሱጁድ፣ ዱዐ፣አና፣ አስቲግፋርን
በማብዛት ወደ ነፉስያሽ አዝንቢያቸው
وَإِن مِّن شَىْءٍ إِلَّا عِندَنَا خَزَآئِنُهُۥ وَمَا نُنَزِّلُهُۥٓ إِلَّا بِقَدَرٍۢ مَّعْلُومٍۢ
መካዚኖቹም (መክፈቻቸው) እኛ ዘንድ ያልሆነ ምንም ነገር የለም፡፡ በተወሰነም ልክ እንጂ አናወርደውም፡

https://www.tgoop.com/muslimprincess2024
የሆነ ቦታ የሆነች የተረጋጋች ሴት ያለች ይመስለኛል። የሰውን ትኩረት የማትፈልግ ፤ ሰዎች እንዲወዷት የተለየ ነገር የማታደርግ የራሷን ኑሮ የምትኖር...

ህይወቷ በእውነት እንጂ በፈጠራ ድራማ ያልተሞላ ፤ ሰዎች እግረመንገድ ላይ ድንገት ዋነኛዋ ሴት የምትሆን ። የተሰማትን የፈለገችውን ደስ ያሰኛትን ሳይሆን ጌታዋ የሚወደዉን ነገር የምታደርግ::ለድክመቷ ለስህተቷ እጅ የማትሰጥ ተስፋ ማትቆርጥ 

ምድር ላይ ያለውን የህይወት ብሶቷን አልያም ችግሯን ለመደበቅ ማህበራዊ ሚዲያ ላይ ወ'ታ ከመንዘባዘብ ይልቅ ከአምላኳ ጋር የምትነጋገር። ስለራሷ እሷ እና አምላኳ ብቻ የሚያውቁ። ይህቺ ሴት ብርቱ ናት....ሰወች  ያከብሯታል  ይጠነቀቁላታል። የትኛውም ወንድ ደፍሮ ሌላዋን ሴት የሚያወራበት መልኩ ይቺን ሴት ሊያወራት አይችልም። ልባም ናት።

ይህቺ ሴት ብርቅ ናት የሷ ቅዋ ዱአዋ ብርታቷ ተወኩል ነዉ። ጌታዋን ማመስገንን ታውቃለች በተሰጣት አታማርርም ።አወ እርሷ ዉድ ነች
👉🏼ስለ ራሳችን በገለፅንላቹ ልክ እንጂ አታውቁንም!

• መች አወቅካትና እንዲህ ነች ብለህ ለመናገር ደፈርክ..?
ሳቋ እንደሆነ ስለሷ ሁሉንም ነገር አይነግርህም።
...ጨዋታ አዋቂነቷ መግባባቷ፣ ሰው አክባሪነቷ ልቧ... የተሸከመውን አያሳይህም።
እሷ እኮ.... ብሎ ለመናገር ድፍረት ከየት አመጣኸው?
...ሰው ልቡ ከውቅያኖስ ይጠልቃል....!

•አየህ ልቧ ሀገር ቢሆን ኖሮ ሁሉንም አንደላቆ አሳርፎ ገና ብዙ ማኖር...የሚችል ይሆን ነበር....
የሰው ልብ ብዙ ሸክሞች የሚዘዋወሩበት በሞት ብቻ የሚዘጋ ወደብ ነው...
ሁሉም በልቡ ችሎ የሚኖረውን.አታውቅም።
ባየሀትና፣ ባሳየችህ ልክ አትገምታት፣ አትደምድማት።
...የልቧን ስትገልጥልህ እንዳትደነግጥ...እንደው እሷ እኮ..? ብለህ አታሸሙርባት። አንቺዬ ሰላም ለልብሽ ይሁን!
.....🌺የኔ ሴት🌹

Kewni

https://www.tgoop.com/muslimprincess2024
አንድ ሰዉ በዱላ ሰሌኑን ቢደበድብ ሰሌኑን ለመጉዳት አይደለም ይልቁን ዉስጡ ከተከማቸዉ አቧራ ሊያነፃዉ ነዉ::የእኛም ነገር የሰሌኑን ይመስላል::ዉስጣች በአቧራ የተሞላ ነዉ::ይህ አቧራ እንዲሁ የሚለቀን አይደለም::በእያንዳንዱ በሚያገኘን ምት የህይወት ከፍታና ዝቅታ እንጅ::እናማ ትምህርት ሰጥቶ ያለፈ ስህተት አስተዋይ እንድኖን ያደረገን መከራ ፀፀት አይኖረውም!!!!!

https://www.tgoop.com/muslimprincess2024
✿ ከ ዕለታት አንድ ቀን ለ ሐሰን አል-በስሪ «የለይል ሶላት የሚሰግዱ ሰዎች ከሰወች ሁሉ ፊታቸው የሚያምረው ለምን ይሁን? ብለው ተጠየቁ። እሳቸውም «ከአል-ረሕማን ጋር ብቻቸውን ተገለሉ እሱም ከኑሩ አለበሳቸው።» ብለው መለሱ።
አምስት ነገሮች ከ5 ነገሮች በፊት‼️
▬ ▬ ▬ ▬ ▬ ▬ ▬ ▬ ▬ ▬
የአላህ መልክተኛ (ሶለሏሁ ዓለይሂ ወሰለም) አንድን ሰው ሲመክሩ እንዲህ ብለዋል: አምስት ነገሮችን ከአምስት ነገሮች በፊት ተጠቀምባቸው፦

1. ወጣትነትህን ከማርጀትህ በፊት፤
2. ጤንነትህን ከመታመምህ በፊት፤
3. ሀብትህን ከመደህየትህ በፊት፤
4. ትርፍ ጊዜህን ከመጨናነቅህ በፊት፤
5. ሕይወትህን ከመሞትህ በፊት።
[ሶሒሑል ጃሚዕ (1077)]
ሀቢብቲ ላንች የተከተበልሽን ሪዝቅ ፍጥረታት ተሰባስበው ሊነጥቁሽ ቢሞክሩ ሊነጥቁሽ አይችሉም!!ላንች ያልተፃፈን ሪዝቅ ሰማይ ከፍ ምድር ዝቅ ብትል አታገኝዉም!!ቀለሙ ደርቋል መፅሀፋም ተነስቷል !!! So calm down my sis
በፀጋወችህ ዉስጥ እየተገላበጥን አንተን ከማመስገን ግን የዘነጋን ሆነን አንግተናል!!!

🌹🌹 ለከል ሀምዱ ያረቢ🌹🌹
⬅️ወንድሜ➡️
ከማፍቀርህ በፊት ራስህን አርቅ ራስህን ጠብቅ
ከትዳር በፊት ያለ ፍቅር ታክመህ የማትድነው
በሽታ ነው

ልብህ ወደ ሴት ሲያዘነብል መልሰው
ካልተፈቀደችልህ ሴት ንግግር አታብዛ ሀያእ ይኑርህ
ሴትን ማፈር ልመድ ከሴትጋ በድፍረትና በድርቅና
ማውራት ጀግንነት አይደለም ኋላ ትወድቃለህ

እናም ወንድሜ አግብተህ አፍቅር 👍
🙁☹️😭🙁😭🙁☹️🙁
ስለ ሴት አብቶ የሚያወራ ጓደኛ ካለህም ራቀው አላማ
ይኑርህ አላማህ ደሞ ትዳር ይሁን አተራማሽ መባል ወንድነት አይደለም የውሻ ባህሪ ነው
አተራማሽ መባል አንተን አይመጥንም ወርደት ነው


☹️🙁☹️😣ትዳር😝☹️☹️😣
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
👆👆
🔶"አንዳችሁ የሌላቹን ፈተና አቅልላችሁ ላለማየት ሞክሩ..!ሁሉም በአቅሙ ልክ ነውና እየተፈተነ ያለው...!
• « አንቱ ሰው እንባዬ ደረቀ፣ፍላጎቴም ሞተ፣ መኖሬም ትርጉም አጣብኝ። ምን ላድርግ?» ብሎ ጠይቃቸው።

እሳቸውም፦ « የኔ ልጅ ልብ ተስፋ ስትቆርጥ በድን ትሆናለች። እንባ የልብ ወንዝ ነው። ምንጩ ሲደርቅ አይን አታለቅስም። ፍላጎት የልብ ማሳ ነው። ካልተኮተኮተ ይጠወልጋል። መኖር አላህን የማወቅያ አንድ ድልድይ ነው። ልብ ስትዝል ድልድዩ ይሰበራል። የኔ ልጅ ሕያው ወደ ሆነው ጌታህ ዘንድ ከመሄድ በቀር ያጣኸውን በተሻለ መንገድ አታገኘውም!»

ልጁም፦«የተጣላሁት ከጌታዬ ጋር ከሆነስ? » አላቸው።
እሳቸውም፦«ጌታህን አምፀኸው አይምረኝም ብለህ ካልክ በእርግጥም ስለ ጌታህ የምታውቀው ጥቂትን ነውና ከፍጡራን ጋር አመሳስለኸዋል። የኔ ልጅ ጌታዬ እኮ እስከ እለተ ትንሳኤ ድረስ እንደሚያምፀው አውቆ እንኳ ሸይጧንን የጠየቀውን ልመና ተቀብሎታል። ታድያ አንተ ያመፅኩህን ይቅር በለኝ ብትለው የማይምርህ ይመስልሀልን?
የኔ ልጅ የሞተ ልብህ ላይ ሕይወትን የሚዘራው ያ ሕይወትን ሰጥቶህ ያመፅከው ጌታህ እንጂ ሌላ ማንም አይደለም። ጌታዬን ከፍጡራን ጋር አመሳስለኸው ይጠየፈኛል ብለህ አታስብ። የኔ ልጅ እስከነ ነውርህም ቢሆን ወደ አላህ ሂድ
ከተላመዳቸው ኃጢያቶች በሸዕባን ወር ላይ መቆጠብ ያልቻለ ሙስሊም ረመዳን ሲገባ በአንድ ጊዜ ማቆሙ እንዴት ይቻለዋል?
ሸዕባን የቅድመ ዝግጅትና የመለማመጃ ወር መሆኑን እናስታውስ።
ያ ኡህቲ ፊላህ ረመዳን ሊገባ በጣት የሚቆጠሩ ቀናት ነዉ የቀሩት::ቀዷ ካለብሽ ዛሬ ነገ ሳትይ ቶሎ ጨርሽ::በኢባዳ ቢዚ ለመሆን ራስሽን አዘጋጅ::ከአሁኑ ነፍስያሽን አለማምጅ::ረመዳን የኢባዳ እንጅ የምግብ ወር አይደለም:: ሀም ኸምሽ ሁሉ ሱፍራ የሚሞላ ምግብ ስለማዘጋጀት አታድጊዉ::እያንዳንዷ ደቂቃሽን ባልባሌ ነገር ላለማሳለፍ ፕሮግራምድ ሁኝ::

🌹🌹ያ አላህ ረመዳንን ከሚደርሱት ደርሰዉ ከሚጠቀሙት አድርገን!!አሚን  🌹🌹
ነገ እግሮች ሁሉ ወደ ሚሊኒየም አዳራሽ ያቀናሉ!!ኢንሻአላህ!!
ኒቃብ + ትምህርት + መሸለም + መምራት ይቻላል::

ኒቃብ ፊትን እንጅ አዕምሮን አይሸፍንም!

ከአርባምንጭ ዩኒቨርሲቲ በወርቅ ሜዳሌያ የተሸለመችው ኒቃቢስቷ ዶክተር ዛኪራ ተባረክ
2025/03/03 18:41:36
Back to Top
HTML Embed Code: