tgoop.com/nahuseman25/618
Create:
Last Update:
Last Update:
አንድ ሽማግሌ ወደ አንድ የሞባይል ጥገና ሱቅ ሔዱና "ስልኬ ተበላሽቷል ሥራልኝ" ብለው ሰጡት።
የሞባይል ጠጋኙ ስልኩን አገላብጦ ከፈተሸው በኋላ
"አባባ ስልክዎ ምንም አልሆነም ይሠራል" አላቸው።
ሽማግሌው ዓይናቸው ዕንባ አቀረረና
"ስልኩ ካልተበላሸ ... ልጆቼ የማይደውሉልኝ ለምንድን ነው?" አሉ በደከመ ድምፅ።
★ ★ ★
ለወላጆቻችን የምናደርገው ትልቁ ሥጦታ ቢኖር ጊዜ መሥጠት ነው። የመኖራቸው ትርጉም የሚገባን ሲለዩን ነው። ዕድለኛ ሆነን ወላጆቻችን በሕይወት ካሉ አሁኑኑ እንደውል። ይህንን ለማንበብ ጊዜ ካገኘን መቼም ለነሱ ለመደወል ጊዜ አናጣም።
"በምድር ላይ ዕድሜህ እንዲረዝም መልካምም እንዲሆንልህ እናትና አባትህን አክብር" ዘዳ 5:16
👉 ዛሬን አሐዱ ብለን ከጀመርነው ቀን ጀምሮ በተለይ ከኤልክትሮኒክስ እቃዎች የምንሰጠውን ጊዜ ቀንሰን ለቤተሰቦቻችንን እንስጣቸው
ከወደዳቹት እርሷም ለወዳጆ ያድርሱ
BY ናሁ ሰማን(Nahu seman)
Share with your friend now:
tgoop.com/nahuseman25/618