ORTODOXTEWADOCHANNAL Telegram 4199
ንስጥሮሳውያን ማናቸው

ንስጥሮሳውያንን ለመረዳት በመጀመሪያ ስለ ንስጥሮስ እንመልከት። ንስጥሮስ በ5ኛው ክፍለ ዘመን የነበረ ሲሆን በአንጾኪያ ቤተክርስቲያን የተማረና ከ 428 እስከ 431 የቁስጥንጥንያ ሊቀ ጳጳስ የነበረ ነው። ነገር ግን በ431 ዓ.ም በተካሄደው ሶስተኛው የቤተክርስቲያን ጉባኤ ተወግዞ ከጵጵስናው የተሻረ ነው።

ንስጥሮስ የተወዘገው በኤፌሶን ጉባኤ በ431 ሲሆን ይህም የሆነው የቤተ ክርሰቲያን መከፋፈል ሳይመጣ ነው። ማለትም ኦሪየንታል ኦርቶዶክስ፣ ምስራቅ ኦርቶዶክስ እና ካቶሊክ የሚባሉት መከፋፈሎች ሳይመጡ በፊት፣ የቀድሞዋ ቤተ ክርስቲያን (early church) በሚባለው ዘመን ነው።

የንስጥሮስ አስተምህሮ በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እና እመቤታችን ድንግል ማርያም ጋር የተያያዘ ሲሆን፣ እመቤታችን ድንግል ማርያም የአምላክ እናት አይደለችም የሚል ነበር። እንዲሁም ደግሞ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሁለት ባሕርይ ነው የሚል ነበር።


ይህም ማለት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሲወለድ አምላክ ሆኖ አልተወለደም የሚልን ሀሳብ የሚፈጥር ነው። ጌታችን አምላክነቱ እና ሰውነቱ አንድ ሳይሆኑ የተነጣጠሉ ናቸው የሚል ነው። ይህም ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በምድር ላይ ለሰው ልጆች የከፈለውን ዋጋ የሚያሳንስ (እሱ ስላለ ጌታችን የከፈለልን ዋጋ አይቀንስም)፣ እመቤታችን ድንግል ማርያምንም ክብሯን የሚቀንስ ነው (እሱ ስለተናገረ ክብሯ አይቀንስም)።

በዚህም ምክንያት በፈረንጆች አቆጣጠር በ431 ዓ.ም በኤፌሶን ከተማ ሶስተኛው የቤተ ክርስቲያን ጉባኤ ተደረገ። ከ200 በላይ አባቶች ጳጳሳት፣ ከሮም፣ ከእስክንድርያ፣ ከአንጾኪያ ከሁሉም ቦታ የመጡ አባቶች በተኙበት ጉባኤ ንስጥሮስ ተወገዘ። የጵጵስና ማዕረጉም ተሻረ። የሱን አስተምህሮ የሚከተሉ ሁሉም ተወገዙ።

በዚህም ንስጥሮስና ተከታዮቹ ጠፉ። ነገር ግን አስተምህሮው አልጠፋም ነበር። በ451 በተካሄደ ጉባኤ የግሪክና የላቲን ቤተ ክርስቲያናት የሱን አስተምህሮ በተዘዋዋሪ ተቀበሉ። በአፋቸው ንስጥሮስ የተወገዘ ነው ቢሉም ግን የተቀበሉትን በተዘዋዋሪ የንስጥሮስን ሁለት ባህርይ አስተምህሮ ነው። ይህን የተቃወሙትም የኦሪየንታል ቤተክርስቲያናት ከነሱ ተለዩ።


ሌሎችም የንስጥሮስ ተከታዮች ነበሩ። ይህም በምዕራብ ሶርያና ምስራቅ ኢራቅ አከባቢ የምትገኘው የ"ምስራቅ" ቤተክርስቲያን ተከታዮች ነበሩ። ይህ ቤተክርስቲያን ከዛን ጊዜ ጀምሮ እስከ ዛሬም የቆየ ሲሆን የንስጥሮስን አስተምህሮ በቀጥታ የሚቀበሉ እና ንስጥሮስንም እንደ ቅዱስ የሚቆጥሩ ናቸው።


ታዲያ ይህ ከላይ ያየነው አባት የዚህ ቤተክርስቲያን አባል ነው። ከልደቱም ጀምሮ በዚህች ንስጥሮሳዊት ቤተክርስቲያን ውስጥ የነበረ ሲሆን በዚያም ዲቁና እና ክህነት ያገኘ ነበር። በኋላ ላይ ግን ከዚያም በመለየት የራሱን ቸርች የከፈተ ሰው ነው።

እንደ ቻናሌ የዚህን ሰው የኋላ ታሪክ ሳልመረምር መልክቱን በመልቀቄ ይቅርታ እጠይቃለሁ።
@ortodoxtewadochannal
@ortodoxtewadochannal



tgoop.com/ortodoxtewadochannal/4199
Create:
Last Update:

ንስጥሮሳውያን ማናቸው

ንስጥሮሳውያንን ለመረዳት በመጀመሪያ ስለ ንስጥሮስ እንመልከት። ንስጥሮስ በ5ኛው ክፍለ ዘመን የነበረ ሲሆን በአንጾኪያ ቤተክርስቲያን የተማረና ከ 428 እስከ 431 የቁስጥንጥንያ ሊቀ ጳጳስ የነበረ ነው። ነገር ግን በ431 ዓ.ም በተካሄደው ሶስተኛው የቤተክርስቲያን ጉባኤ ተወግዞ ከጵጵስናው የተሻረ ነው።

ንስጥሮስ የተወዘገው በኤፌሶን ጉባኤ በ431 ሲሆን ይህም የሆነው የቤተ ክርሰቲያን መከፋፈል ሳይመጣ ነው። ማለትም ኦሪየንታል ኦርቶዶክስ፣ ምስራቅ ኦርቶዶክስ እና ካቶሊክ የሚባሉት መከፋፈሎች ሳይመጡ በፊት፣ የቀድሞዋ ቤተ ክርስቲያን (early church) በሚባለው ዘመን ነው።

የንስጥሮስ አስተምህሮ በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እና እመቤታችን ድንግል ማርያም ጋር የተያያዘ ሲሆን፣ እመቤታችን ድንግል ማርያም የአምላክ እናት አይደለችም የሚል ነበር። እንዲሁም ደግሞ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሁለት ባሕርይ ነው የሚል ነበር።


ይህም ማለት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሲወለድ አምላክ ሆኖ አልተወለደም የሚልን ሀሳብ የሚፈጥር ነው። ጌታችን አምላክነቱ እና ሰውነቱ አንድ ሳይሆኑ የተነጣጠሉ ናቸው የሚል ነው። ይህም ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በምድር ላይ ለሰው ልጆች የከፈለውን ዋጋ የሚያሳንስ (እሱ ስላለ ጌታችን የከፈለልን ዋጋ አይቀንስም)፣ እመቤታችን ድንግል ማርያምንም ክብሯን የሚቀንስ ነው (እሱ ስለተናገረ ክብሯ አይቀንስም)።

በዚህም ምክንያት በፈረንጆች አቆጣጠር በ431 ዓ.ም በኤፌሶን ከተማ ሶስተኛው የቤተ ክርስቲያን ጉባኤ ተደረገ። ከ200 በላይ አባቶች ጳጳሳት፣ ከሮም፣ ከእስክንድርያ፣ ከአንጾኪያ ከሁሉም ቦታ የመጡ አባቶች በተኙበት ጉባኤ ንስጥሮስ ተወገዘ። የጵጵስና ማዕረጉም ተሻረ። የሱን አስተምህሮ የሚከተሉ ሁሉም ተወገዙ።

በዚህም ንስጥሮስና ተከታዮቹ ጠፉ። ነገር ግን አስተምህሮው አልጠፋም ነበር። በ451 በተካሄደ ጉባኤ የግሪክና የላቲን ቤተ ክርስቲያናት የሱን አስተምህሮ በተዘዋዋሪ ተቀበሉ። በአፋቸው ንስጥሮስ የተወገዘ ነው ቢሉም ግን የተቀበሉትን በተዘዋዋሪ የንስጥሮስን ሁለት ባህርይ አስተምህሮ ነው። ይህን የተቃወሙትም የኦሪየንታል ቤተክርስቲያናት ከነሱ ተለዩ።


ሌሎችም የንስጥሮስ ተከታዮች ነበሩ። ይህም በምዕራብ ሶርያና ምስራቅ ኢራቅ አከባቢ የምትገኘው የ"ምስራቅ" ቤተክርስቲያን ተከታዮች ነበሩ። ይህ ቤተክርስቲያን ከዛን ጊዜ ጀምሮ እስከ ዛሬም የቆየ ሲሆን የንስጥሮስን አስተምህሮ በቀጥታ የሚቀበሉ እና ንስጥሮስንም እንደ ቅዱስ የሚቆጥሩ ናቸው።


ታዲያ ይህ ከላይ ያየነው አባት የዚህ ቤተክርስቲያን አባል ነው። ከልደቱም ጀምሮ በዚህች ንስጥሮሳዊት ቤተክርስቲያን ውስጥ የነበረ ሲሆን በዚያም ዲቁና እና ክህነት ያገኘ ነበር። በኋላ ላይ ግን ከዚያም በመለየት የራሱን ቸርች የከፈተ ሰው ነው።

እንደ ቻናሌ የዚህን ሰው የኋላ ታሪክ ሳልመረምር መልክቱን በመልቀቄ ይቅርታ እጠይቃለሁ።
@ortodoxtewadochannal
@ortodoxtewadochannal

BY ኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ መንፈሳዊ አገልግሎት


Share with your friend now:
tgoop.com/ortodoxtewadochannal/4199

View MORE
Open in Telegram


Telegram News

Date: |

“Hey degen, are you stressed? Just let it all out,” he wrote, along with a link to join the group. Hashtags 6How to manage your Telegram channel? Done! Now you’re the proud owner of a Telegram channel. The next step is to set up and customize your channel.
from us


Telegram ኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ መንፈሳዊ አገልግሎት
FROM American