SAMUELBELETE Telegram 1662
የውስጥ ቀለሞች ...
:

ቀና አለ ። ግራጫው ሰማይ ላይ የተሰመሩት ወፎች ቁልቁል : ወደ ታች : ይወርዳሉ ። ዝቅ ሲል ...ከከንፈሩ የሚያፈተልከው የሲጋራ ጢስ ፊቱ ላይ ብን : ብን : ይላል ። አእምሮው ውስጥ ቀይ - ቢጫ - ነጭ - ቀለሞች ተፈጥረዋል:: -----1

ከአዳማ ወደ ድሬ ዳዋ የሚወስድ መኪና ውስጥ ... ላብ ካቸፈቸፈበት አየር ስር አንዲት ሴት ተቀምጣለች ። ጸጉሯ ተበታትኑዋል። ፊቷ ላይ ማዲያት ጥላውን ጥሏል። ለንቦጩን የጣለው መኪና የሁሉንም ጩኸት አፍኖ ይዟል። ከሁሉም ሰዎች ይቺ ሴት ደመቅ ብላ ትታያለች ። በዛለ ክንዷ ሮዛ የሚል መጽሐፍ ይዛ : በመጽሐፉ መሃል ጠቋሚ ጣቷን ከታ መጽሐፉን ቆልፋዋለች ። ከውልደት እስከ አሁን ያለው ኅዘኗ አካሏን ሰርቷል ? ...2

ሳን ሚጉኤል የጻፈውን 'voices from silence' ን እየባከንሁበት : የልብ - መልኳን እያሰስሁበት : የሴቲቷን አይኖች ለማዬት ቀናሁ ። ታሪክ ድጋሚ ተፈጠረ ። የሰው ቀለሙ በቀን : አካሉም በፀሐይ ይሳላል ። የተናገርነው ጭምር የቃላት ቀለም ነው ። እነዚህ ናፍቆት ይሆናሉ ። አንዳንዴ ቢጫ ጥላ አያጠላም ። ተስፋ ማጣት : ተስፋ አለማዬት---ሕይወት--- ሳይወድ በግዱ ሰው ፈሳሽ ጨለማውን ተግቶ ያጋሳል ። ጥጋብ አይደለም---።

"የት ነው የምትሄደው?"

"ጨለንቆ ! አንቺስ?"

"ድሬ ዳዋ" መርጋት ተደላድሏል በድምጿ ::

"ለሥራ ነው?"

"አዎ ! አንቺስ ?''

"እኔም"

"ምን ትሰሪያለሽ ?"

ዝም .....

መኪናው በፍጥነት ይጓዛል ። መኪና ውስጥ ባሉ ሰዎች ሕመም ተደብቋል ። በወና ህዋ የተንሳፈፉ ቀለማት አርፈውባቸዋል ። በአበባና በአበባ መካከል እንዳለ ፈገግታ ፈገግ ብላ ጥርሷን ገለጠች ።በእርግጥም የስዕልን ርቃቄ ነች ።----

"ምንድነው? የምታነበው?"

"ሳን ሚጉኤልን ታውቂዋለሽ?"

" የሚወራለት ንባብ የለኝም :: አንድ ...አንድ ...ከሁለት አይበልጡም ያነበብኋቸው ። ምን ፃፈ ያንተስ ሰውዬ ?"

"ስለ አርጀንቲናዎች የጻፈው ነው።" ነገር በእንጥልጥል ...

ከንፈሮቿን በአይኔ ሰሳምኩ ...

''ሮዛ ደስ ይለኛል ። ይሄ መጽሐፍ ብዙ ጣእሞች አሉበት ። ቡዙ እጆች ፣ ብዙ ገላዎች ፣ ተነክተውበታል ። አፎች ተጣመዋል ። ድምጾች ሰልለው ፣ ጸጉሮች ጸጥ : ጭጭ : ረጭ : ብለውበታል። ብዙ ሕመሞች ...! ትራስ ላይ ተንሰቅስቀው ፣ ሲያለቅሱም ፡ ሳያለቅሱም ፡ ሳግ ፡ ሲያንቃቸው ጭምር አይበታለሁ... ። አንዳንዴኮ... አንዳንድ አካሎችም : አእምሮ ላይ እንደ በረዶ ይረጋሉ ። ደስ አይልም ? አንዳንድ አካሎች ደግሞ በሌላ ይሰንፋሉ ። ሲያስጠላ ! ይሄ ፍቅር ። የሰው ልጅ ተጫውቶ የሚሸነፍበት ካርታ ። ጦር ያለው ። የሚዋጋ ። የሚያቃጥል ...''3

"ካነበብሁት ቆዬሁ ። በለኮስሽኝ ... እስካልበርድ : እስካልረግብ : በትውስታ ምሪት እንደ አጥቢያ ኮከብ እንዳልበርቅ ፈራሁ ። ሃሃሃ ... "

'' ጥሩ ታወራለህ ። ድምፅህ መግራት አለው ።''

'' መኖርን አታስመስግኝኝ ! ''
.
.
.

ለፀሐይ እንደተተወ ውጥር ቆዳ : የሁሉም ሰው ፊት ሲቃጠል : ዜማም : ግጥምም : እንደ ሌለው ሙዚቃ ነገሮች ዝም ሲሉ : ብልቶች እንቅስቃሴ ሲያቆሙ----- ልቦች በልቦች ሲጎዱ : ቀጭን ሰይጣን ግንባሩ ላይ በለኮሳት እሳት ሲነድ----- በመጽሐፍ መልካ - መልክ ላይ ተዘበራርቆ ተደርሷል። ስለ ቀለም : ማንም... ስለሌላቸው ነፍሶች : ተወግረው እንደጎበጡ አካሎች : እንደተዘበራረቀው ተፈጥሮ : መኪናው ጥሎ እንዳለፋቸው የትላንት መንገዶች : እንዳልተከፈተ ሙዚቃ : ቅላጼ እንደሌለው ሕመም : በውስጥ እንደሚመላለስ : የሚንሴጠሰጥ ጩኸተ - ራስ : የማይያዝ : የማይጨበጥ : የማይደረስበት : የራቀ : በጣቶቼ ልጨብጠው ስል ...ሲያዳልጠኝ : በቃ! በቃ ! ይሄም ...ትንሽ ትንሽ ያማል።''---4

"የት ደረስን?"

"አዋሽ 40"

ካንቀላፉ ትላንቶች ቅዠት ...ቀለም ሲውለበለብ...! ረጋ ካለ የአዋሽ ተንሳፋፊ ሐይቅ : ሙቀት የሚያነጥባቸው ላቦች... በገላ : በገጻችን ሲሰፉ : በቃ! ----አይኗ ተስለመለመ ። ቅንድቧ ስር ላብ አቸፈ---።

"እምልሽ ለምን ሮዛን ወደድሽ ?"

"እኔ እንጃ ! ምናልባት ታሪኬን ስለሚነግረኝ ?።"

" ብዙ ኖርሽለት ለሃዘን ? ተጎናበስሽለት ለደስታ ?"

ምኑ ይነገራል ብለህ ?

እዚህ ጥያቄ ምልክት ላይ! ብዙ አዳፋ ታሪኮች አሉ ። ቢጻፉ የማይጠሩ ። ሸፋፋነታቸው በጫማ የማይሸፈን ። መንገድ የጠፋባቸው የታሪክ እግሮች : አቅጣጫ የሌላቸው : ቀለም የሌላቸው : ስሜት የሌላቸው : ብዙ ምንም የለሾች -----ያልተሞሸሩ ሕመሞች : ማንም ያልካደመላቸው : የበለዘ ወዝ : ጠረን የሌለው ሰመመን : ምጽአት የራቀው በድን : በአይን ቆብ ተጠቅልሎ ያሸለበ አይን : በጨረር የተጠቀጠቀ አይን ... ለህመሟ ስታሸልብ እያያሁዋት ...! ---- ከተከፈተው ጭኗ ጠባሳዋን ማዬት : ለአዋሽ እንደ ገባር የገባ ዕንባዋን ማለቂያውን ማዬት ፈለግሁ ። ኦ ! አንተ አላህ ። ኦ ! ያንተ ያለህ ...።

ከታሪኳ : ከነካካችው ገላዋ : ከነኳት ገላዎች : የሚነሱ ታሪኮች ታሪክ ለመሆን ሲጣጣሩ : ሲጥሩ : ሲፈጉ : ዝም ብለው ዝም አስባሏት ። የወገገ ታሪኳን ሲያርመጠምጡት : በጣታቸው ሲያጨማልቁት---- የማያውቋት : የማታቃቸው : ደሟን : ደም ግባቷን : ከደምስሯ ሰርገው ሲጠቡት : አያውቁ ይሄን መከራ---- አያውቁ ይህንን ሕይወት ---- ልስልስ ሞትና ---ከራስ መለየት ነው የሕይወት ኋላና ፊቷ ።

"እኔ እምልሽ ድሬ ዳዋ ለምን ነው ምትሄጅው!"

"ቁልቢ ነኝ"

" ኧረ ? ዘመድ ጥዬቃ ? ወይስ... ?"

" አይ ! ለንግስ... ስዕለት አለብኝ ። ዘቢብ መልኬን : ፀጋ ወዜን አደርሳለሁ ። "

" ስለ ቀደስሻት ቀኔ : ሌሊቶቼን ሰዉቼ እጎናበስልሻለሁ ። ሃሌታን እወጣልሽም ዘንድ አስብሻለሁ ። ''

'' ሃዘን ተቃመስን አይደል ? በደስታህ በኩል ተጋደምኩ ?''

'' የዕንባ መና የሕይወት ችሮታም ነው :: ''

ከተሳፈርኩበት ወረድኩ :: የሳን ሚጎኤልን መጽሐፍ ጨርሼ እጄላይ ተዝረክርኳል :: ጨረቃ ... ከርቀት ተቀበለችኝ ። ባለንጀራዬ ከሩቅ ጨረቃዋን ቀድሟት ይመጣል። የምናየው የማይታየውን ቀለም ነው ? የምናየው የኛ ቀለም ነጸብራቁ አይናችን እንዳልሆነስ ? የደም ዝውውራችን የተደበቀ ሌላ ቀይ ቀለም ይሰጣል ። የኖርነው ዛሬ : የዛሬ ቀለም ነው ። የናፍቆት ቀለሙ - መለያዬት ነው ? የተለዬኋትን ? የተነጠልኳቸውን አሰብሁ ።

ዞር ብዬ መኪናውን አየሁት ። የተጫነበት ሃሳብ እንደሚያንገዳግደው : ወደ ቀኙ : ወደ ግራው እንደሚያስዘምመው ይሆናል ::

1.The color introduced by daylight ግጥም ፓሬ
2.ግራ ገብ በሆነ ዓለም አንዳንዴ ክምችት(restኸ mass) በሐዘን ሊፈጠር ይችላል አካልም
3. እንቅልፍ አሸለብ አረጋት የሚዘንበው የኃዘን ዝናብ ቆመ
4.የመንገድ ኃሳቦቸ
6.የሚቀጥ[...]
:

ቀና አለ ። ግራጫው ሰማይ ላይ የተሰመሩት ወፎች ቁልቁል : ወደ ታች : ይወርዳሉ ። ዝቅ ሲል ...ከከንፈሩ የሚያፈተልከው የሲጋራ ጢስ ፊቱ ላይ ብን : ብን : ይላል ። አእምሮው ውስጥ ቀይ - ቢጫ - ነጭ - ቀለሞች ተፈጥረዋል:: -----1



tgoop.com/samuelbelete/1662
Create:
Last Update:

የውስጥ ቀለሞች ...
:

ቀና አለ ። ግራጫው ሰማይ ላይ የተሰመሩት ወፎች ቁልቁል : ወደ ታች : ይወርዳሉ ። ዝቅ ሲል ...ከከንፈሩ የሚያፈተልከው የሲጋራ ጢስ ፊቱ ላይ ብን : ብን : ይላል ። አእምሮው ውስጥ ቀይ - ቢጫ - ነጭ - ቀለሞች ተፈጥረዋል:: -----1

ከአዳማ ወደ ድሬ ዳዋ የሚወስድ መኪና ውስጥ ... ላብ ካቸፈቸፈበት አየር ስር አንዲት ሴት ተቀምጣለች ። ጸጉሯ ተበታትኑዋል። ፊቷ ላይ ማዲያት ጥላውን ጥሏል። ለንቦጩን የጣለው መኪና የሁሉንም ጩኸት አፍኖ ይዟል። ከሁሉም ሰዎች ይቺ ሴት ደመቅ ብላ ትታያለች ። በዛለ ክንዷ ሮዛ የሚል መጽሐፍ ይዛ : በመጽሐፉ መሃል ጠቋሚ ጣቷን ከታ መጽሐፉን ቆልፋዋለች ። ከውልደት እስከ አሁን ያለው ኅዘኗ አካሏን ሰርቷል ? ...2

ሳን ሚጉኤል የጻፈውን 'voices from silence' ን እየባከንሁበት : የልብ - መልኳን እያሰስሁበት : የሴቲቷን አይኖች ለማዬት ቀናሁ ። ታሪክ ድጋሚ ተፈጠረ ። የሰው ቀለሙ በቀን : አካሉም በፀሐይ ይሳላል ። የተናገርነው ጭምር የቃላት ቀለም ነው ። እነዚህ ናፍቆት ይሆናሉ ። አንዳንዴ ቢጫ ጥላ አያጠላም ። ተስፋ ማጣት : ተስፋ አለማዬት---ሕይወት--- ሳይወድ በግዱ ሰው ፈሳሽ ጨለማውን ተግቶ ያጋሳል ። ጥጋብ አይደለም---።

"የት ነው የምትሄደው?"

"ጨለንቆ ! አንቺስ?"

"ድሬ ዳዋ" መርጋት ተደላድሏል በድምጿ ::

"ለሥራ ነው?"

"አዎ ! አንቺስ ?''

"እኔም"

"ምን ትሰሪያለሽ ?"

ዝም .....

መኪናው በፍጥነት ይጓዛል ። መኪና ውስጥ ባሉ ሰዎች ሕመም ተደብቋል ። በወና ህዋ የተንሳፈፉ ቀለማት አርፈውባቸዋል ። በአበባና በአበባ መካከል እንዳለ ፈገግታ ፈገግ ብላ ጥርሷን ገለጠች ።በእርግጥም የስዕልን ርቃቄ ነች ።----

"ምንድነው? የምታነበው?"

"ሳን ሚጉኤልን ታውቂዋለሽ?"

" የሚወራለት ንባብ የለኝም :: አንድ ...አንድ ...ከሁለት አይበልጡም ያነበብኋቸው ። ምን ፃፈ ያንተስ ሰውዬ ?"

"ስለ አርጀንቲናዎች የጻፈው ነው።" ነገር በእንጥልጥል ...

ከንፈሮቿን በአይኔ ሰሳምኩ ...

''ሮዛ ደስ ይለኛል ። ይሄ መጽሐፍ ብዙ ጣእሞች አሉበት ። ቡዙ እጆች ፣ ብዙ ገላዎች ፣ ተነክተውበታል ። አፎች ተጣመዋል ። ድምጾች ሰልለው ፣ ጸጉሮች ጸጥ : ጭጭ : ረጭ : ብለውበታል። ብዙ ሕመሞች ...! ትራስ ላይ ተንሰቅስቀው ፣ ሲያለቅሱም ፡ ሳያለቅሱም ፡ ሳግ ፡ ሲያንቃቸው ጭምር አይበታለሁ... ። አንዳንዴኮ... አንዳንድ አካሎችም : አእምሮ ላይ እንደ በረዶ ይረጋሉ ። ደስ አይልም ? አንዳንድ አካሎች ደግሞ በሌላ ይሰንፋሉ ። ሲያስጠላ ! ይሄ ፍቅር ። የሰው ልጅ ተጫውቶ የሚሸነፍበት ካርታ ። ጦር ያለው ። የሚዋጋ ። የሚያቃጥል ...''3

"ካነበብሁት ቆዬሁ ። በለኮስሽኝ ... እስካልበርድ : እስካልረግብ : በትውስታ ምሪት እንደ አጥቢያ ኮከብ እንዳልበርቅ ፈራሁ ። ሃሃሃ ... "

'' ጥሩ ታወራለህ ። ድምፅህ መግራት አለው ።''

'' መኖርን አታስመስግኝኝ ! ''
.
.
.

ለፀሐይ እንደተተወ ውጥር ቆዳ : የሁሉም ሰው ፊት ሲቃጠል : ዜማም : ግጥምም : እንደ ሌለው ሙዚቃ ነገሮች ዝም ሲሉ : ብልቶች እንቅስቃሴ ሲያቆሙ----- ልቦች በልቦች ሲጎዱ : ቀጭን ሰይጣን ግንባሩ ላይ በለኮሳት እሳት ሲነድ----- በመጽሐፍ መልካ - መልክ ላይ ተዘበራርቆ ተደርሷል። ስለ ቀለም : ማንም... ስለሌላቸው ነፍሶች : ተወግረው እንደጎበጡ አካሎች : እንደተዘበራረቀው ተፈጥሮ : መኪናው ጥሎ እንዳለፋቸው የትላንት መንገዶች : እንዳልተከፈተ ሙዚቃ : ቅላጼ እንደሌለው ሕመም : በውስጥ እንደሚመላለስ : የሚንሴጠሰጥ ጩኸተ - ራስ : የማይያዝ : የማይጨበጥ : የማይደረስበት : የራቀ : በጣቶቼ ልጨብጠው ስል ...ሲያዳልጠኝ : በቃ! በቃ ! ይሄም ...ትንሽ ትንሽ ያማል።''---4

"የት ደረስን?"

"አዋሽ 40"

ካንቀላፉ ትላንቶች ቅዠት ...ቀለም ሲውለበለብ...! ረጋ ካለ የአዋሽ ተንሳፋፊ ሐይቅ : ሙቀት የሚያነጥባቸው ላቦች... በገላ : በገጻችን ሲሰፉ : በቃ! ----አይኗ ተስለመለመ ። ቅንድቧ ስር ላብ አቸፈ---።

"እምልሽ ለምን ሮዛን ወደድሽ ?"

"እኔ እንጃ ! ምናልባት ታሪኬን ስለሚነግረኝ ?።"

" ብዙ ኖርሽለት ለሃዘን ? ተጎናበስሽለት ለደስታ ?"

ምኑ ይነገራል ብለህ ?

እዚህ ጥያቄ ምልክት ላይ! ብዙ አዳፋ ታሪኮች አሉ ። ቢጻፉ የማይጠሩ ። ሸፋፋነታቸው በጫማ የማይሸፈን ። መንገድ የጠፋባቸው የታሪክ እግሮች : አቅጣጫ የሌላቸው : ቀለም የሌላቸው : ስሜት የሌላቸው : ብዙ ምንም የለሾች -----ያልተሞሸሩ ሕመሞች : ማንም ያልካደመላቸው : የበለዘ ወዝ : ጠረን የሌለው ሰመመን : ምጽአት የራቀው በድን : በአይን ቆብ ተጠቅልሎ ያሸለበ አይን : በጨረር የተጠቀጠቀ አይን ... ለህመሟ ስታሸልብ እያያሁዋት ...! ---- ከተከፈተው ጭኗ ጠባሳዋን ማዬት : ለአዋሽ እንደ ገባር የገባ ዕንባዋን ማለቂያውን ማዬት ፈለግሁ ። ኦ ! አንተ አላህ ። ኦ ! ያንተ ያለህ ...።

ከታሪኳ : ከነካካችው ገላዋ : ከነኳት ገላዎች : የሚነሱ ታሪኮች ታሪክ ለመሆን ሲጣጣሩ : ሲጥሩ : ሲፈጉ : ዝም ብለው ዝም አስባሏት ። የወገገ ታሪኳን ሲያርመጠምጡት : በጣታቸው ሲያጨማልቁት---- የማያውቋት : የማታቃቸው : ደሟን : ደም ግባቷን : ከደምስሯ ሰርገው ሲጠቡት : አያውቁ ይሄን መከራ---- አያውቁ ይህንን ሕይወት ---- ልስልስ ሞትና ---ከራስ መለየት ነው የሕይወት ኋላና ፊቷ ።

"እኔ እምልሽ ድሬ ዳዋ ለምን ነው ምትሄጅው!"

"ቁልቢ ነኝ"

" ኧረ ? ዘመድ ጥዬቃ ? ወይስ... ?"

" አይ ! ለንግስ... ስዕለት አለብኝ ። ዘቢብ መልኬን : ፀጋ ወዜን አደርሳለሁ ። "

" ስለ ቀደስሻት ቀኔ : ሌሊቶቼን ሰዉቼ እጎናበስልሻለሁ ። ሃሌታን እወጣልሽም ዘንድ አስብሻለሁ ። ''

'' ሃዘን ተቃመስን አይደል ? በደስታህ በኩል ተጋደምኩ ?''

'' የዕንባ መና የሕይወት ችሮታም ነው :: ''

ከተሳፈርኩበት ወረድኩ :: የሳን ሚጎኤልን መጽሐፍ ጨርሼ እጄላይ ተዝረክርኳል :: ጨረቃ ... ከርቀት ተቀበለችኝ ። ባለንጀራዬ ከሩቅ ጨረቃዋን ቀድሟት ይመጣል። የምናየው የማይታየውን ቀለም ነው ? የምናየው የኛ ቀለም ነጸብራቁ አይናችን እንዳልሆነስ ? የደም ዝውውራችን የተደበቀ ሌላ ቀይ ቀለም ይሰጣል ። የኖርነው ዛሬ : የዛሬ ቀለም ነው ። የናፍቆት ቀለሙ - መለያዬት ነው ? የተለዬኋትን ? የተነጠልኳቸውን አሰብሁ ።

ዞር ብዬ መኪናውን አየሁት ። የተጫነበት ሃሳብ እንደሚያንገዳግደው : ወደ ቀኙ : ወደ ግራው እንደሚያስዘምመው ይሆናል ::

1.The color introduced by daylight ግጥም ፓሬ
2.ግራ ገብ በሆነ ዓለም አንዳንዴ ክምችት(restኸ mass) በሐዘን ሊፈጠር ይችላል አካልም
3. እንቅልፍ አሸለብ አረጋት የሚዘንበው የኃዘን ዝናብ ቆመ
4.የመንገድ ኃሳቦቸ
6.የሚቀጥ[...]
:

ቀና አለ ። ግራጫው ሰማይ ላይ የተሰመሩት ወፎች ቁልቁል : ወደ ታች : ይወርዳሉ ። ዝቅ ሲል ...ከከንፈሩ የሚያፈተልከው የሲጋራ ጢስ ፊቱ ላይ ብን : ብን : ይላል ። አእምሮው ውስጥ ቀይ - ቢጫ - ነጭ - ቀለሞች ተፈጥረዋል:: -----1

BY ሳሙኤል በለጠ(ባማ)


Share with your friend now:
tgoop.com/samuelbelete/1662

View MORE
Open in Telegram


Telegram News

Date: |

Avoid compound hashtags that consist of several words. If you have a hashtag like #marketingnewsinusa, split it into smaller hashtags: “#marketing, #news, #usa. “Hey degen, are you stressed? Just let it all out,” he wrote, along with a link to join the group. Ng was convicted in April for conspiracy to incite a riot, public nuisance, arson, criminal damage, manufacturing of explosives, administering poison and wounding with intent to do grievous bodily harm between October 2019 and June 2020. Each account can create up to 10 public channels The visual aspect of channels is very critical. In fact, design is the first thing that a potential subscriber pays attention to, even though unconsciously.
from us


Telegram ሳሙኤል በለጠ(ባማ)
FROM American