tgoop.com/sratebetkrstyane/6963
Last Update:
ኪዳነ ምህረት
🤲 #ኪዳነምህረት ስንል የምህረት ቃልኪዳን ማለት ነው፡፡በዚህ ውስጥም ምህረት አድራጊው ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሲሆን ምህረት ተቀባይም መላው የአዳም ዘር ነው፡፡
🤲 #እናታችን_ቅድስት_ድንግል_ማርያም በምድራዊ ቆይታዋ ዘውትር ወደ #ክርስቶስ መካነ መቃብር ጎልጎታ እየወረደች ትፀልይ ነበር፡፡ #ልጇ እና #ወዳጇ #ጌታችን_መድሐኒታችን_ኢየሱስ_ክርስቶስ ያደረገችው ልመናና ፀሎት ተመልክቶና ሰምቶ የምህረት ቃል ኪዳን ገባለት ፡፡
🤲 እንኳን #የእናቱን ፀሎት እና ልመና ቀርቶ ዘውትር በሀጥያት የምንዘፈቀውን እኛን ክፉዎቹን የሚሰማ #አምላክ ስለ አንቺ ፣ ስለ #እናቴ ክብርና ፀጋ ስል ይኸው ቃሌ ብሎ ቃልኪዳን አደረገ፡፡
« #ከመረጥሁት_ጋር_ቃል_ኪዳኔን_አደረግሁ።»_መዝ89:3 እንዲል መፅሐፉ፡፡
🤲 ስሟን ለሚጠሩ፣ በእርሷ አማላጅነት ለሚታመኑ በምድር በረከትን በሰማይ የዘለዓለም መንግስትን እንደሚወርሱ የምህረት እና የቸርነት ቃልኪዳን ሰጥቷታል ፡፡
🤲 ታላቁ መፅሐፍ እንዲህ ይላል፦
". . .#ቀስቲቱም_በደመና_ትሆናለች_በእኔና_በምድር_ላይ_በሚኖር_ሥጋ_ባለው_በሕያው ነፍስ_ሁሉ_መካከል_ያለውን_የዘላለም_ቃል_ኪዳን_ለማሰብ_አያታለሁ። "_ኦሪት_ዘፍ.9:16
🤲 በዚህም መሠረት ቃልኪዳኗን ምክንያት በማድረግ #ኪዳነ_ምህረት እያልን እንጠራታለ
እንኳን ለ«#ኪዳነምህረት» ወርሀዊ ክብረ በአል በሰላም አደረሳችሁ። #የእመቤታችን ምህረት እና ረድዔት፤በረከት ከሁላችን ጋር ይሁን አሜን!!!
BY ✝️ስርዓተ ቤተክርስቲያን መመሪያ ✝️
Share with your friend now:
tgoop.com/sratebetkrstyane/6963